Author Archive

ዓመት እንደ ዋዛ

Tuesday, February 15th, 2011

ዓመት እንደ ዋዛ


የቅዱስ ሲኖዶስ
ክብር ግርማ ሞገስ
ጻድቅ ዜና ማርቆስ
ባርኩን በአጸደ ነፍስ።
      
ቀን ሲቆጠር ጊዜ
የመሮጡ አባዜ
ግባ መሬት ምሡ
አፈርን ሳይቀምሱ።
ሳምንት ሁለት ሳምንት ወራት እየበዛ
ያሉ እየመሰለን ዓመት እንደ ዋዛ።
ከእኛ ጋራ ሆነው ዘውትር ስናያቸው
አብረን ውለን አድረን ከቶ ማን ጠግቧቸው።
           
ቅዱስ አባታችን የተዋሕዶ ቤዛ
ዜና ከተለዩን ዓመት እንደዋዛ።
ብሩህ ገጽታዎን ሳናየው ብንቀር
እናት እንደ ሞተው ብሎናል ቅር ቅር።
ሺህ ዓመት ቢቆጠር ፍቅርን ድል አይነሳም
ዜና አባታችንን ምን ጊዜም አንረሳም።
እውነተኛ ባርያ ለጌታ የተገዛ
በቅፉ ካፈሩ ዓመት እንደዋዛ።

ከልጃቸው ከሰባኬ ወንጌል ሽመልስ ተሊላ

ሰበር ዜና – ከቤተ ክርስቲያን የሰላምና የአንድነት ኮሚቴ

Sunday, January 9th, 2011
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰላምና የአንድነት ኮሚቴ በሜሪላን ከተማ ባለፈው ሳምንት መጀመሪያ ላይ አድርጎት በነበረው ስብሰባ ለመጪው የሰላምና የእርቅ ውይይት አስፈላጊ በሆኑ ቅድመ ዝግጅቶች ላይ እንደሚወያይና ውሳኔ እንደሚያስተላልፍ ተጠብቆ ነበር። በዚህም መሠረት የደረሰን ዘገባ እንደሚያመለክተው የእርቅ ውይይቱን ስፍራ እና ጊዜ በተመለከተ ኮሚቴው ጥልቅ ውይይት ካደረገ በኋላ ስብሰባው በአሜሪካን ሀገር ከዐብይ ጾም መግቢያ በፊት እንዲሆን ወስኗል።  ባለፈው ዓመት ተደርጎ በነበረው የእርቅ ስብሰባ ዙሪያ የታዩትን ችግሮችን ለማስወገድ ይቻል ዘንድ ኮሚቴው የስብሰባውን ከተማና ቦታ እንዲሁም የስበሰባውን ጊዜ በዝርዝር እንደማይገለጽ ለመረዳት ችለናል። በአባቶች ስብሰባ ጊዜ ግራ አጋቢና ሃሳብ ከፋፋይ ግለሰቦች ድርሻ እንዳይኖራቸው አስፈላጊው ሁሉ ጥረት እንደሚደረግም የደረሰን ዘገባ ጨምሮ ያስረዳል።
ከዚህ ጋር አያይዞ የደረሰን ዜና እንደሚያመለክተው የእርቁን ስበሰባ በሚገባ ለማካሄድ ያመች ዘንድ ወጪውን ለመሸፈኛ የሚሆን የገንዘብ ማሰባሰቢያ ዝግጅቶች በተለያዩ ከተማዎች ይደረጋሉ። ከዚህ ቀደም ተደርጎ ለነበረው ስብሰባ አስፈላጊው ወጪ በሰላምና አንድነት ጉባኤው አባላትና በጥቂት የቤተ ክርስቲያን ወዳጆች የተሸፈነ ቢሆንም ይህ ኃላፊነት የጥቂቶች ብቻ ሳይሆን የቤተ ክርስቲያንን ሰላም ለማየት የሚፈልጉ ሁሉ የጋራ ድርሻ እንደሆነ ጥርጥር የለውም። ከሥራቸው ፈቃድ በመውሰድ ለስብሰባ ዝግጅት አስፈላጊውን ጊዜ ከመሰዋት ባሻገር ብዙዎቹ የኮሚቴ አባላት የቤተ ክርስቲያን አባቶችን በጠረጴዛ ዙሪያ ለማገናኘት የሚያስፈልገውን ወጪ ከኪሳቸው አውጥተው ለመሸፈን እንደሚቸገሩ ለሁላችንም ግልጽ ነው ለመረዳት ችለናል። በመሆኑ እያንዳንዱ ምእመን ለዚህ ታሪካዊና መንፈሳዊ የእርቅና የሰላም እንቅስቃሰየ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ኮሚቴው ጥሪውን አስተላልፏል።  
ከዚህ በታች ያለው የኮሚቴው ደብዳቤ አስፈላጊውን መረጃ እንደሚሰጣችሁ እምነታችን ነው።
 

የልደት በዓል ቡራኬ በስደት ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ

Sunday, January 9th, 2011

ብጹዕ አቡነ መልከጼዲቅ – ሊቀ ጳጳስ
በስደት የሚገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ