<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?>
<rss version="2.0"
	xmlns:content="http://purl.org/rss/1.0/modules/content/"
	xmlns:wfw="http://wellformedweb.org/CommentAPI/"
	xmlns:dc="http://purl.org/dc/elements/1.1/"
	xmlns:atom="http://www.w3.org/2005/Atom"
	xmlns:sy="http://purl.org/rss/1.0/modules/syndication/"
	xmlns:slash="http://purl.org/rss/1.0/modules/slash/"
	>

<channel>
	<title>Ethiopian Review</title>
	<atom:link href="http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2" rel="self" type="application/rss+xml" />
	<link>http://www.ethiopianreview.com/amharic</link>
	<description>Amharic News</description>
	<lastBuildDate>Sun, 19 May 2013 22:56:39 +0000</lastBuildDate>
	<language>en-US</language>
	<sy:updatePeriod>hourly</sy:updatePeriod>
	<sy:updateFrequency>1</sy:updateFrequency>
	<generator>http://wordpress.org/?v=3.4.2</generator>
		<item>
		<title>ኢትዮጵያዊነት እያበበ ነው ወይስ እየጠወለገ?</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3361</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3361#comments</comments>
		<pubDate>Sun, 19 May 2013 22:56:39 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3361</guid>
		<description><![CDATA[ያለንበት ጊዜ ኢትዮጵያዊ ዜጋ መሆን ትረጉመ-ቢስ የሆነበት ደረጃ ላይ እየደረሰ እንዳይሆን የሚያሰጋበት ወቅት ነው። ኢትዮጵያዊያን በኢትዮጵያዊነታቸው ሊከበርላቸው የሚገባውን የዜግነት መብት እየተነፈጉ ነው። መንግሥት የዜጎችን መብት ማስከበር ተስኖታል። ይህንን አስመልክቶ የኢሮብ መብት ተማጓች ማህበር (ኢ.መ.ተ.ማ) ተደጋጋሚ እሮሮዎችን ሲያሰማ የቆየ ቢሆንም አድማጭ ጆሮ ተነፍጎት ቆይቷል። ከአንድ መቶ በላይ የኢሮብ ተወላጅ ኢትዮጵያዊያን በሻዓቢያ ታግተው ከተወሰዱ ይኸው አሥራ ሶስት [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1590">ባሁኑ ሰዓት በአማራው ወገናችን ላይ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2187">የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1540">መኢአድ ከቤኒሻንጉል ክልል&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/444">ወንጀለኛ የህወሃት ጀሌዎችን በህግ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1110">“መንግሥት የለም ወይ?!”- የማንና&#8230;</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/Ethio-Flag.jpg"><img src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/Ethio-Flag-150x36.jpg" alt="Ethio Flag" width="150" height="36" class="alignnone size-thumbnail wp-image-3037" /></a></p>
<p>ያለንበት ጊዜ ኢትዮጵያዊ ዜጋ መሆን ትረጉመ-ቢስ የሆነበት ደረጃ ላይ እየደረሰ እንዳይሆን የሚያሰጋበት ወቅት ነው። ኢትዮጵያዊያን በኢትዮጵያዊነታቸው ሊከበርላቸው የሚገባውን የዜግነት መብት እየተነፈጉ ነው። መንግሥት የዜጎችን መብት ማስከበር ተስኖታል። ይህንን አስመልክቶ የኢሮብ መብት ተማጓች ማህበር (ኢ.መ.ተ.ማ) ተደጋጋሚ እሮሮዎችን ሲያሰማ የቆየ ቢሆንም አድማጭ ጆሮ ተነፍጎት ቆይቷል።<br />
ከአንድ መቶ በላይ የኢሮብ ተወላጅ ኢትዮጵያዊያን በሻዓቢያ ታግተው ከተወሰዱ ይኸው አሥራ ሶስት ዓመት ሊሞላ አንድ ወር ቀርቶታል። ኢ.መ.ተ.ማ የነዚህ ዜጎች እጣ ፈንታ እንዲጠይቅ እንዲሁም የኢሮብ ሕዝብና ሌሎች ኢትዮጵያውያን ለሺ ዓመቶች የኖሩበት መሬታቸው ለኤርትራ መከለሉን በተመለከተ ለኢትዮጵያ መንግሥት ተደጋጋሚ አቤቱታ ቢያቀርብም፤ መንግሥት ጆሮ ደባ ልበስ ብሎ መቀመጥን መርጧል። ቀጥሎም በ2003 ዓ.ም ሻዓቢያ እንደገና በወርቅ ማምረት ላይ ተሠማርተው የነበሩ ከ260 በላይ ኢትዮጵያዊያን የትግራይ ተወላጆችን ከምእራብ ትግራይ ጠልፎ በመውሰድ ድኳቸው አጥፍቷል። ሆኖም፤ መንግሥት የነዚህን ዜጎች ደህንነት ለማረጋገጥና የሚገኙበት ሁኔታን ለማጣራት የወሰደው አንዳችም እርምጃ የለም። በተቃራኒው፤ አንዳንድ የኢህአዴግ የፖለቲካ ተቀናቃኝ ኢትዮጵያዊ የፖለቲካ ኃይሎች በክስተቶቹ መንግሥት የመረጠውን ዝምታ በማውገዝ የአቋም መግለጫዎችን አውጥቷል። በውጭ ዜጎች መጠለፍ ወታደራዊ እርምጃ እስከመውስደ የተሯሯጠ መንግሥት ታግተው ደብዛቸው ስለጠፉ ዜጎቹ ምንም ዓይነት የሀላፊነት ስሜት አላሳየም የወሰደው እርምጃም የለም።<br />
ዛሬ ደግሞ ኢትዮጵያዊ ዜጎችን የማፈናቀል አባዜ እጅግ አስከፊና ዘግናኝ በሆነ መልኩ እየተካሄደ ይገኛል። መፈናቀሉ መልከ ብዙ መሆኑ መዘንጋት የለበትም። ለም የእርሻ መሬቶችን ለህንድና ለዓረብ ባለሀብቶች በስመ-ኢኒቨስትመንት ለመስጠት በሰበብ አስባቡ ከኖሩበት ቀዬ የሚፈናቀሉ ወገኖች ቁጥር እጅጉን ተበራክቷል። የከተማ ነዋሪ ኢትዮጵያዊያን ዜጎች በሰበብ አስባቡ ያለምንም ቅድመ ዝግጅት በዓቅማቸው ቀልሰው ለዓመታት ከኖሩበት ቀዬ በማፈናቀል፤ ያለ ምንም ካሳ ቤቶቻቸውን በማፍረስ ሕጻናት፤ ነብሰ-ጡሮች፤ አሮጊት እናቶች፤ ሽማግሌ አባቶችና አቅመ ደካሞች ለሜዳ ኑሮ መዳረጋቸውን ታዝበናል። በተቃራኒው፤ መቐለ ውስጥ እንደታዘብነው ቤት እንዳይሠራባቸው በሕግ የተከለከሉና ለመናፈሻና ለደን እንዲጠበቁ በከተማው አስተዳዳሪዎች የተወሰኑ ቦታዎች ላይ የሥርዓቱ ባለሥልጣናትና የሥርዓቱ ታማኞች ሕግ ተላልፈው ፎቆችና ቪላዎችን ሲያሰሩ፤ በሕገ-ወጥ መንገድ የተሰሩ ናቸውና መፍረስ አለባቸው ብሎ የሚያፈርስ ቀርቶ፤ ሕግ ተላልፋቹሀል ብሎ የሚናገር ባለሥልጣንን ለመስማት አልታደልንም። ይህ በመቐለ የተከሰተው ዓይነት አሠራር በሌሎች አከባቢዎችም ተፈፅሞ ሊሆን ይቻላል። ሆኖም ለጊዜው መቐለ ላይ የተጣሰ ሕግ በሌሎች የኢትዮጵያ ከተሞች ውስጥም እንደተጣሰ ለማመሳከር የሚያስችል ጭብጥ ስለሌለን በዚሁ ልናልፈው መርጠናል። እነዚህ ከላይ ያነሳናቸው ጭብጦች ላይ ተመርኵዘን በመከሰት ላይ ያለውን ህዝብን የማፈናቀል ተግባር አስፈላጊ ሆኖ እንኳ ቢገኝ ብቁ ቅድመ ዘግጅት ተደርጎ እንዲካሄድ የማድረግ ሓላፊነት ለመሸከም የሚችል መንግሥት እንደሌለን የሚያመላክት ሆኖ እናገኘዋለን። በየጊዜው በሻዓቢያ እየታገቱ ለሚወሰዱና ደብዛቸው ለጠፋ ዜጎች መቆም ያቃተው መንግሥት እንዳለን ከታዘብንም ሰነባብተናል።<br />
አሁን ይህንን አጭር መግለጫ ለማውጣት ያስገደደን እጅግ አስደንጋጭና በዓይነቱም ለየት ያለ ኢትዮጵያዊያንን ለዓመታት ከኖሩበት መሬት የዘር ሐረጋቸው እየተመረጠ አፈናቅሎ የማባረር ኢትዮጳዊነትን የሚፈታተን ተግባር ሲፈጸም መታዘባችን ነው። ከዚህ በፊት ኢትዮጵያውያን ዘራቸው እየተጠና ከጉራ ፈርዳ ተፈናቅለው መባረራቸውን ሰምተናል አንብበናል። ያንን ስንሰማና ስለዛ ስናነብ እጅጉን የደነገጥን ቢሆንም፤ አገዛዙ ከዚህ ስሕተት ተምሯል የሚል ግምት አሳድረን ነበር። እንዳለመታደል ሆኖ ግን ተመሳሳይ ስሕተት እንደገና በተመሳሳይ መልኩ ተደግሞ ተከስቷል። አማርኛ ተናጋሪ ኢትዮጵያዊያን ከበንሻንጉል ጉምዝ ፍጹም ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ እንዲባረሩ ተደርጓል። በዚህም፤ የኢህአዴግ መንግሥት በጉራፈርዳ የፈጸመውን ኢሰብአዊ ግፍ ከመድገም ወደ ኋላ እንደማይል በሚገባ እንድንረዳ አስችሎናል። ስለሆነም፤ ሁኔታው እጅጉን አሳስቦናል። ኢትዮጵያዊያን በዘር ሐረጋቸው ምክንያት ከተወሰነላቸው ክልል ውጭ መኖር የማይችሉበት ሁኔታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየባሰበት ሲቀጥል ታዝበናል። ይህ ዛሬ በአማርኛ ተናጋሪ ኢትዮጵያዊያን ላይ እየተፈጸመ ያለው ዘግናኝና አሳፋሪ የማፈናቀል ተግባር፤ ነገ በሌሎች ኢትዮጵያዊያን ላይ ላለመቀጠሉ ምንም ዓይንት ዋስተና የለም። ይህ በእንዲህ ከቀጠለ ደግሞ ኢትዮዽያና ኢትዮዽያዊነት ምን ትርጉም ሊኖረው እንደሚችል ህሊና ያለው እያንዳንዱ ኢትዮዽያዊ ቆም ብሎ ራሱን መመርመር ይኖርበታል ብሎ መኢተማ ያምናል። በመሆኑም፤ በሥልጣን ላይ ያለው አገዛዝ፤ ኢትዮጵያዊያንን ከቅያቸው የማፈናቀል ተግባር እንዲያቆም ኢትዮጵያዊያን ተባብረን የሚቻለውን ሁሉ ማድረግ ይኖርብናል። የኢህአዴግ አገዛዝም፤ ህዝብን የማፈናቀል ተግባር የሚያስከትለው መዘዝ ምን ያህል አስከፊና አውዳሚ ሊሆን እንደሚችል በወጉ ለመገንዘብ ያለመፈለግን እልህ ማቆም ይጠበቅበታል። ካልሆነ ግን በሂደት ላገሪቱም ሆነ ለራሱ ለኢህአዴግ አላስፈላጊ ጥፋት ሊያስከትል እንደሚችል በወቅቱ ቢገነዘበው የተሻለ ይሆናል።<br />
ኢትዮጵያዊያን ኢትዮጵያ ውስጥ እንደፈለጉ በፈለጉበት ቦታ ተዘዋውረው ሠርተው ሀብት ለማፍራት፤ ወልደው ከብደው ለመክበርና በገዛ አገራቸው ውስጥ ያለምንም መሳቀቅና መፍራት የመኖር ሕገ-መንግሥታዊ ዋስትና ከሌላቸው ኢትዮጵያ የምትባል አገርና ኢትዮጵያዊ የሚባል ዜጋ ሊኖር ይችላል ብሎ ለማሰብ የሚቻል አይሆንም። ይህ ማለት ግን መንግሥት በከተማም ሆነ በገጠር የሚኖረውን የመሬት ይዞታ መልክ ለማስያዝ የሚረዳ ፖሊሲ መንደፍ የለበትም ለማለት እንዳልሆነ ግልጽ ሊሆን ይገባል። ለደን ልማት፤ ለመናፈሻ፤ ለዱር አራዊት፤ ለእርሻ፤ ለኢንዳስትሪ፤ ለመኖርያ፤ …….ወዘተ የሚሆኑ ቦታዎች ተለይተው አይከለሉ ለማለት አይደለም። መከለል አለባቸው። አሠራራችንም ሆነ የአመራረት ዘየቤያችን ዘመናዊ ማድረግ ላይ ተቃውሞ የለንም ብቻ ሳይሆን የምንደግፈው ጉዳይ ይሆናል። ሆኖም፤ የድሀው ህዝባችን ኑሮ በማያመሰቃቅልና ዜጎችን በማይለያይ መልኩ በጥናትና በጊዜ እየተለየ መከናወን አለበት ብለን እናምናለን። የማናምነውና ፍጹም የማንቀበለው ጉዳይ ቢኖር ግን የተለያዩ የክልል ትናንሽ ንጉሶችን በመፍጠር ኢትዮጵያዊንን ከኛ ዘር ስላልተወለዳችሁ፤ ይህ ክልል የነ እገሌ ዘሮች የትውልድ ክልል ስለሆነ ወይም ስላልሆነ ከሌላ ቦታ የመጣቹህ ወይም ከሌላ ዘር፤ ወገን የሆናቹህ በዚህ ክልል፤ መንደር፤ ሰፈር…ወዘተ መኖር አትችሉም የሚለው አካሄድ ኢትዮጵያዊነትን የሚንድ አደጋ አለው ብለን በጽኑ እናምናለን። አንድ ኢትዮጵያዊ በአንድ ክልል ውስጥ መጥቶ መኖር ሲጀምር፤ መኖርያውን በሚቀይስበት ጊዜ የመፍቀድም ሆነ የመከልከል ሥልጣን በሕግ የተሰጠው ኣካል ሲከለክልም ሆነ ሲፈቅድ የተገልጋዩን የዘር ሐረግ መስፈርት እንዳይጠቀም በሕግ መከልከል ይኖርበታል እንላለን። አንድ ኢትዮጵያዊ በተወሰነ ቦታ ላይ የተወሰነ ሥራ ለማከናወን ሲፈልግ፤ ያ ቦታ እንዲሰጠው ለመፍቀድም ሆነ ላለመፍቀድ አስቀድሞ በተቀመጠው ፕላን መሠረት በሚቀመጥ መስፈርት እንጂ ግለሰቦች በዘፈቀደ በሚዘውሩት መስፈርት ሊሆን ፈጽሞ አይገባም። ከዚህ ውጭ በሆነ መንገድ ዘርና ወገን እየተለየ ኢትዮጵያዊያንን ማፈናቀል እየገፋ ሲሄድ ማቆምያ ድንበር ሊበጅለት የማይቻልበት ደረጃ ሊደርስ እንደምችል መታወቅ አለበት። የዚህ ድምር ውጤት በጋራ መልማትና ማደግ ሳይሆን ተያይዞ መጥፋትን እንደሚያስከትል መጠርጠር የለበትም። የኢትዮጵያ ህዝብ በየክልሉና በየመንደሩ ተከልሎ እንዲኖር የተወሰነ ዕለት እንደዚህ ዓይነት ችግር እንደሚከተል በግልጽ የሚታወቅ እንደመሆኑ መጠን፤ የሚያስከትለውን ችግር ለመረዳት የሚከብድ አልነበረም። በመሆኑም፤ አሁን እያየነው ያለ በቋንቋ ላይ የተመሰረተ መፈናቀል እንዲከሰት ሆን ተብሎ የታቀደ ፀረ አንድነትና ኢትዮዽያዊነት ተግባር መሆኑም ግልጽ ነው።<br />
በየክልላችን ተወስነን እንድንኖር የተደረገ ዕለት አብሮና ተማምኖ የአገራችንን ዳር ድንበር ለማስከበር የሚቆም ብሔራዊ ሠራዊት አይኖረንም። ለይስሙላ የሚቋቋም ብሔራዊ መከላከያ ኃይል ሊኖረን ይችል ይሆናል። ያ ግን መለዮ የለበሱ ሰዎች ስብስብ እንጂ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሠራዊት ሊሆን አይችልም። በኢትዮጵያዊነት ብሔራዊ ስሜት ተኮትኵቶ፤ የችግሯን ገፈት አብሮ ለመቅሰም አብሮ የመሰለፉን ያህል ከጥቅምዋም አብሮ እኩል ለመቋደስ የማይችል ወታደር ብሔራዊ ወታደር ሊሆን አይችልም። ይህ ደግሞ ኢትዮጵያን በመሳሰሉ በቅራኔ በተወጠረ ቀጠና ውስጥ ላሉ አገሮች ቀርቶ አንጻራዊ ሰላም አላቸው በሚባሉ አገሮች ውስጥም ቢሆን ተቀባይነት የለውም። የሠራዊቱን ጉዳይ አነሳን እንጂ በየመስኩ ብንዘረዝረው ሊያስከትለው የሚችለው ውድቀት የት የሌለ ጥፋት እንደሚሆን ለመገመት የሚከብድ አይደለም። በመሆኑም፤ አሁን አማርኛ ተናጋሪ ኢትዮጵያዊያን ወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለውን ግፍ መጀመርያ በኢትዮጵያዊ ወገንተኝነታችን እንዲሁም ሰው በመሆናችን እጅጉን አሳዝኖናል። በመሆኑም፤ ይህንን አስነዋሪ ተግባር እያወገዝን የነዚህ ዜጎች ጉዳይ ከግብር ይውጣ አሠራር በዘለለ ወደ ተፈናቀሉበት ቀዬ ተመልሰው እንዲኖሩ እንዲደረግና ለደረሰባቸው የአካል፤ የንብረትና የሥነ-አእምሮ ድቀት ተገቢ ካሳ እንዲያገኙ እንዲደረግ ጥሪያችንን እናቀርባለን።<br />
ከዚህም በተጨማሪ፤ የተከበሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ለኢፈዴሪ ፓርላማ በሰጡት መግለጫ ተግባሩን ማውገዛቸው የሚያስመሰግናቸው ቢሆንም፤ ማውገዝ ብቻውን የሚፈለገው ውጤት ሊያስጨብጠን እንደማይችልና የኢትዮጵያ ህዝብም ሆነ ዓለም አቀፉ ማህበረ-ሰብ በቀላሉ የሚቀበሉትና የሚጃጃሉበት እንደማይሆን ይረዱታል ብለን እንገምታለን። ስለሆነም፤ ኢትዮጵያዊያን በዜግነታቸው ተማምነው ሕጋዊ ዋስትና እንዳላቸው እርግጠ ኛ እንዲሆኑና አገራችን በዓለም አቀፉ ህብረተ-ሰብ የተሰጣትን ገጽታ ወደ በጎነት ለመቀየር ይቻል ዘንድ ባስቸኳይ ሕጋዊ የእርምት እርምጃ መወሰድ ይኖርበታል። በኢ.መ.ተ.ማ እይታ ይህ ጉዳዩ ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደገለጹት “የተወሰኑ ኪራይ ሰብሳቢ የወረዳ አስተዳዳሪዎች” የፈጸሙት ነው የሚለው አባባል በአመክንዮ ሊደገፍ የሚችል አይደለም። ቢያንስ ከፍተኛ የፈደራል የመንግሥት ባለሥልጣኖች በወንጀሉ ውስጥ አለመሳተፋቸው በእርግጠኝነት ከታወቀ፤ በጥልቀት ሊመረመር የሚገባው የሕግ ሕፀፅ መኖር አለበት። ካልሆነ ግን ማንም የወረዳ አስተዳዳሪ ከባዶ ተነስቶ ይህን ያህል ህዝብ የማባረር ሥልጣን ይኖሯል ብሎ ለማሰብ እጅጉን ይከብዳል። ስለሆንም፤ ችግሩን ከሥሩ በማጥራት በነዚህ ኢትዮጵያዊያን ወገኖቻችን ላይ የደረሰው አስከፊ በደል በማያዳግም መንገድ እልባት እንዲያገኝና ኢትዮጵያዊነት ከመጠውለግ ድኖ እንዲያብብ ሁሉም እጅ ለእጅ ተያይዞ አንዲታገል አጥብቀን እንጠይቃለን።<br />
ኢትዮጵያዊነት በኢትዮዽያዊያን የጋራ ትግል ይለመልማል!!!<br />
የኢሮብ መብት ተማጓች ማኅበር (ኢ.መ.ተ.ማ)<br />
ግንቦት 2005 ዓ.ም</p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1590"     class="crp_title">ባሁኑ ሰዓት በአማራው ወገናችን ላይ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2187"     class="crp_title">የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1540"     class="crp_title">መኢአድ ከቤኒሻንጉል ክልል&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/444"     class="crp_title">ወንጀለኛ የህወሃት ጀሌዎችን በህግ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1110"     class="crp_title">“መንግሥት የለም ወይ?!”- የማንና&hellip;</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=83102</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>ታሪክን የኋሊት፤ የአቶ መለስ ድንጋጤ! (አቤ ቶኪቻው)</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3344</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3344#comments</comments>
		<pubDate>Sun, 19 May 2013 20:36:32 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3344</guid>
		<description><![CDATA[እንግዲህ ይህ ከሆነ አመቱ ሆነ አይደለ… ቅዳሜም ቅዳሜ፣ እሁድም እሁድ ነው እና ምናልባት ካልተገናኘን… እንዳንረሳው፤ ከወዲሁ ቀኑን እንደሚከተለው እንዘክረው… (በቅንፍም ኤድያ እነ እንትናዬ ደግሞ ሊበሳጩብኝ ነው… (በሌላ ቅንፍ እንግዲህ ይቻሉት እኛ ስንቱን ችለነው የለ…)) በመጀመሪያም፤ ብስጭቴ እኔ እኮ የምለው ሰው አይኑ እያየ የሰራውን ስራ እያወቀ ወደ አሜሪካ ለዛውም ወደ ዋሽንግተን ዲሲ ይሄዳል እንዴ!? እውነቱን ለመናገር [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/22">ጂሃዳዊ እርምጃን በኢትዮጵያ ላይ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/24">የኢሕአፓ ወጣት ክንድ በክርሥትና&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2827">የአቶ መለስ መታሰቢያ ተቋም (Foundation)! </a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1265">የኢህአዴግ መተካካት ፖለቲካ &#8211;&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2811">ግርማዊነታቸው የአቡነ ጴጥሮስን&#8230;</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p>እንግዲህ ይህ ከሆነ አመቱ ሆነ አይደለ… ቅዳሜም ቅዳሜ፣ እሁድም እሁድ ነው እና ምናልባት ካልተገናኘን… እንዳንረሳው፤ ከወዲሁ ቀኑን እንደሚከተለው እንዘክረው… (በቅንፍም ኤድያ እነ እንትናዬ ደግሞ ሊበሳጩብኝ ነው… (በሌላ ቅንፍ እንግዲህ ይቻሉት እኛ ስንቱን ችለነው የለ…))</p>
<p><strong>በመጀመሪያም፤</strong></p>
<p><strong>ብስጭቴ</strong></p>
<p>እኔ እኮ የምለው ሰው አይኑ እያየ የሰራውን ስራ እያወቀ ወደ አሜሪካ ለዛውም ወደ ዋሽንግተን ዲሲ ይሄዳል እንዴ!? እውነቱን ለመናገር እኔ አቶ መለስ ዜናዊን ብሆን ኖሮ ዲቪ እንኳ ቢደርሰኝ ሀገር ይቀየርልኝ እላለሁ እንጂ አሜሪካ አልሄድም። እነ ቻይና ባሉበት አለም እነ ሰሜን ኮሪያ በሚኖሩበት ምድር ሰው እንዴት ወደ አሜሪካ ይሄዳል? (ይቅርታ ሰው በሚል የተጠቀሱት ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችንን ነው)</p>
<p><strong>ዋናው ወሬ፤</strong></p>
<p>የሆነው ሆኖ ትላንት በዋሽንግተኑ ስብሰባ አቶ መለስ ዜናዊ ሲመጡ ከውጪ ያለውን የተቃውሞ ድምፅ በመከራ አልፈው የስብሰባ አዳራሽ ውስጥ ከገቡ በኋላ ደግሞ ጋዜጠኛ አበበ ገላው ተሰብሳቢው ፊት፤ ከውጪ ያለው ህዝብ በሰላማዊ ሰልፍ፣ እንዲሁም አዲሳባ ያለው ህዝብ ደግሞ በሰላማዊ ዝምታ በሆዱ ምን እያላቸው እንደሆነ ነጥብ ነጥቡን ነግሯቸዋል። እንደው ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነውብኝ እንጂ “እስከ ዶቃ ማሰሪያቸው ድረስ ነግሯቸዋል!” ብል የበለጠ ይገልፀዋል መሰል!</p>
<p>የጋዜጠኛ አበበ ገላው ድርጊት ከዚህ በፊት ጆርጅ ቡሽ ላይ ጫማ ከወረወረው ጋዜጠኛ ጋር የሚቀራረብ ይመስላል። እንደውም በቪዲዮ እንዳየኋቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ላይ የደረሰው የቅስም ስብራት “በጫማ መመታት በስንት ጣዕሙ!” ያሰኛል።</p>
<p>ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በስፍራው የተገኙት በባራክ ኦባማ ጋባዥነት ከቡድን ስምንት ሀገሮች ጋር ስብሰባ ሊቀመጡ እንደሆነ ባለፈው ግዜ አውርተናል፤ ከቡድን ስምንቱ ስብሰባ አንድ ቀን ቀደም ብሎ ታድያ  “ግሎባል አግሪካልቸር ኤንድ ፉድ ሴኪዩሪቲ” በተባለው ስብሰባ ላይ ቁጭ ብለው እንደተለመደው ፐርሰንታቸውን እየጠቀሱ ሳለ ድንገት አበበ ገላው፤ “መለስ ዜናዊ…” ብሎ ሲጠራ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን “የደነገጡት መደንገጥ… ከአንድ ታጋይ የሚጠበቅ አይደለም” ሲሉ አስተያየት የሰጡ አሉ። እኔም እንዳየሁት ጆሯቸውን ማመን አቅቷቸው “የድርጅቴን ብቅል እየፈጨሁ ነው…” ብለው ሊያልፉት የከጀሉ ሁሉ መስሎኝ ነበር።</p>
<p>ብቻ በጣም ክው ማለታቸውን ፊታቸው አሳበቀባቸው። ከዛ እንደምንም ተረጋግተው…“ሰበንቲ….ፐርሰንት” ብለው ንግግራቸውን ሊቀጥሉ ሲሉ የጋዜጠኛ አበበ ገላው ድምፅ ከመጀመሪያው ከፍ ብሎ “መለስ ዜናዊ ኢዝ ኤ ዲክታተር…” ማለቱን ቀጠለ አሁን ትንፋሽም ቃልም አጠራቸው። አስተያየታቸው “ምነው ዛሬ እግሬን በሰበረው!?” የሚሉ ይመስላሉ። ግን እንደምንም ብለው ለመቀጠል ሞከሩ። ድምፃቸውን ከአበበ ድምፅ ከፍ ለማድረግ እየጣሩ “ሰበንቲ…ፐርሰንት” አልቻሉም። “ምን ላይ ነበር ያቆምኩት…?” ለማለት የፈለጉ ይመስላሉ ባልንጀሮቻቸውን ቃኘት ቃኘት አደረጉ። እነርሱቴ “ራስህ ተወጣው!” ሳይሏቸው አይቀሩም… አበበ ቀጥሏል። “መለስ ዜናዊ ኢዝ ኤ ዲክታተር….” አሁን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከኛ በላይ ድምፅ ላሳር በሚመስል መልኩ ከአበበ በላይ ጮክ ብለው እና ድፍረታቸውን አሰባስበው፤ “ሰበንቲ ፐርሰንት ኦፍ ዘ ፖፕሌሽን ኢን አፍሪካ….” አሉ። ብሽሽቅ ነው የሚመስለው እንጂ የንግግራቸው አካል አይመስልም!</p>
<p>ድጋሚ አቋረጡ አበበ ግን የሚያቋርጥ አይመስልም በእንግሊዝ አፍ “እስክንድር ነጋ እና ሁሉም የፖለቲካ እስረኞች ይፈቱ፤ ምግብ ያለ ነፃነት ዋጋ የለውም! መለስ ዜናዊ አምባ ገነን ነው!” ብሎ እንቅጩን ነገራቸው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁና ቁና ሲተነፍሱ ኮምፒውተሬን አልፎ ሁሉ ይሰማ ነበር። በሆዴ “ይበልዎት አይሂዱ አላልኮትም ነበር!?” ብልም እውነቱን ለመናገር ግን አንጀቴን በልተውታል።</p>
<p>አቶ መለስ ከትላንትናው የበለጠ  ቅዳሜ ደግሞ ሌላ ተቃውሞ እንደሚጠብቃቸው ጭምጭምታ ሰምቻለሁ። ከዋሽንግተን ዲሲ ወጣ ብሎ የሚገኘው ካምፕ ዴቪድ ድረስ ህዝቡን ለማመላለስ የተሰናዱ አውቶቡሶች መኖራቸውን የደረሰኝ ጭምጭምታ ያስረዳል።</p>
<p>እኔማ የሚሰማኝ አጣሁ እንጂ ቀድሞውኑም ይሄ ስብሰባ ይቅርብዎ ብዬ ነበር። ይሄን ግዜ እርሳቸውም በሆዳቸው “ምነው ምነው ምነው በቀረብኝ” የሚለውን ሙዚቃ ሊያዜሙ እንደሚችሉ እጠረጥራለሁ። ምንም ጠቅላይሚኒስትር ቢሆኑ ሰው አይደሉ እንዴ…!? ምክሬን ባለመስማታቸው መፀፀት ካልቻሉ እውነትም ሰውየው ጠቅላይ ሚኒስትር እንጂ ሰው አይደሉም ማለት ነው!</p>
<p>ይህንን የጠቅላይ ሚኒስትሩን ቅስም ስብራት የሰማ አንድ ወዳጄ “ይሄኔ ጥሩ አዝማሪ ቢገኝ ይቺን ግጥም በል እስቲ ተቀበል ብሎ ማቀበል ነበር” ብሎኛል…</p>
<p>“አፄ መለስ ዜና እጅግ ተዋረዱ</p>
<p>ምግብ ብለው መጥተው አንጀት በልተው ሄዱ</p>
<p>አንተ አበበ ገላው እንደምን ቻልካቸው</p>
<p>መለስ ቀለስ ሲሉ ጎንበስ አረካቸው”</p>
<p>(አረ ጎበዝ ዜማ ፈልጉና ይችን ነገር ነጠላ ዜማ አደርገን እንልቀቃት በስንት ግዜ የተገኘ የግጥም አዚምን እንጠቀምበት እንጂ!)</p>
<p>በነገራችን ላይ ከዚህ ጋር በተያያዘ አንዳንድ የህብረተሰብ ክፍሎች እንደሚሰጡት አስተያየት ከሆነ አቶ መለስ አዲሳባ ሲገቡ ወይ በጭፈራ ሞቅ ደመቅ አድርገን ካልተቀበልናቸው ወይ ደግሞ ለጥ ብለን ተኝተን ካልጠበቅናቸው በብስጭት ሊጨርሱን ይችላሉ ሲሉ ስጋታቸውን ገልፀዋል።</p>
<p><script type="text/javascript"><!--
google_ad_client = "ca-pub-8555893555560582";
/* Post  336 x 280 */
google_ad_slot = "9157038725";
google_ad_width = 336;
google_ad_height = 280;
//-->
</script><br />
<script type="text/javascript"
src="http://pagead2.googlesyndication.com/pagead/show_ads.js">
</script></p>
<p><strong>በመጨረሻም</strong></p>
<p>ኦባማ ግን አራዳ መሆናቸው ነው ሰውየውን ጠርተው ልክ ልካቸውን የሚያስነግሯቸው!? የምር ሽምቅቅ አደረጓቸውኮ! (እኔ ልሸማቀቅ… ልላቸው ነበር አሁንማ አንዴ ጀምረውታል… ይወጡት እንግዲህ!)</p>
<p><iframe src="http://www.youtube.com/embed/MPZw49-1h-0" height="315" width="560" allowfullscreen="" frameborder="0"></iframe></p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/22"     class="crp_title">ጂሃዳዊ እርምጃን በኢትዮጵያ ላይ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/24"     class="crp_title">የኢሕአፓ ወጣት ክንድ በክርሥትና&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2827"     class="crp_title">የአቶ መለስ መታሰቢያ ተቋም (Foundation)! </a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1265"     class="crp_title">የኢህአዴግ መተካካት ፖለቲካ &#8211;&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2811"     class="crp_title">ግርማዊነታቸው የአቡነ ጴጥሮስን&hellip;</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=83082</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>ስድስት:- ቃል ኪዳን፤ ደፋርና ጭስ መውጫ አያጣም! የኢትዮጵያ ሳታላይት ቴሌቪዢንና ራድዮ (ከፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም)</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3339</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3339#comments</comments>
		<pubDate>Sun, 19 May 2013 12:51:37 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3339</guid>
		<description><![CDATA[መስፍን ወልደ ማርያም መጋቢት 2005 እንግዲህ ኢሳት በነገረኛነትም ሆነ በጠመንጃ-ያዥነት በኩል ከሎሌነት ጠባይ ጋር የተያያዘውን ኢትዮጵያውያን ያለንን አጉል ባህል ሁሉ እየነቀስን እየጣልን በዘመናዊና ሳይንሳዊ አስተሳሰብ መሠረት ለመጣል ዋና መሣሪያ ሊሆነን ይችላል ብሎ ማመን መነሻ ይሆናል፤ ይህ እምነት ከሌለ የእምቧይ ካብ ነው፤ ይህ እምነት ራስን ማጽዳትንም ይጠይቃል። ማክሸፍ እንደምንችልበት ከማመን እንጀምር፤ ስለዚህም ኢሳት ሊከሽፍ የሚችልበትን እያንዳንዱን መንገድ [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/549">መርዝ ከውጭ ይረጫል ወይም ከውስጥ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/843">ፍሬ-አልባ ጩኸት &#8211; ከፕ/ር መስፍን&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3109">የአቶ አስገደ ልጆች ምን ወንጀል ሠሩ?</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1677">ዳምጠው ወያኔ/ኢሕአዴግና አፈና&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2276">እዉነተኛና ዘላቂ ግንባታ</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p><b>መስፍን ወልደ ማርያም</b><br />
<b>መጋቢት 2005</b></p>
<p><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/02/Pro-Mesfin.jpg"><img class="alignleft size-medium wp-image-550" alt="Pro Mesfin" src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/02/Pro-Mesfin-300x200.jpg" width="300" height="200" /></a>እንግዲህ ኢሳት በነገረኛነትም ሆነ በጠመንጃ-ያዥነት በኩል ከሎሌነት ጠባይ ጋር የተያያዘውን ኢትዮጵያውያን ያለንን አጉል ባህል ሁሉ እየነቀስን እየጣልን በዘመናዊና ሳይንሳዊ አስተሳሰብ መሠረት ለመጣል ዋና መሣሪያ ሊሆነን ይችላል ብሎ ማመን መነሻ ይሆናል፤ ይህ እምነት ከሌለ የእምቧይ ካብ ነው፤ ይህ እምነት ራስን ማጽዳትንም ይጠይቃል።</p>
<p>ማክሸፍ እንደምንችልበት ከማመን እንጀምር፤ ስለዚህም ኢሳት ሊከሽፍ የሚችልበትን እያንዳንዱን መንገድ ማጥናትና በቅድሚያ ፈውሱን ማዘጋጀት የሚጠቅም ይመስለኛል፤ ይህንን ጉዳይ በትጋት ለመከታተል የኢሳትን አማራጭ የማይገኝለት የአገር ጥቅም በእውነትና በትክክል መገንዘብ ያሻል፤ ዘመን-አመጣሽ ነገር ብቻ አድርጎ መመልከቱ ለወረት ይዳርገዋል፤ ወረትን ማክሸፍ ቀላል ነው፤ ከከሸፈ በኋላ እንዲያንሰራራ ለማድረግ በጣም ከባድ ሥራን ይጠይቃል፤ ስለዚህ ከወዲሁ ኢሳት ጠንካራ መሠረት ላይ እንዲተከል የተቻለውን ሁሉ ማድረግ ዘለቄታ እንዲኖረው ማረጋገጫ ይሆናል።</p>
<p>የኢሳት መክሸፍ የኢትዮጵያውያንን ተስፋ ያጨልማል፤ አንፈራጥጠው ከላይ ቤት እታች ቤት እየቀላወጡ አካላቸውን፣ አእምሮአቸውንና መንፈሳቸውን የሚያባልጉ ሰዎችን ያበራክታል፤ የድብቅብቆሽ ዓለምን እየፈጠሩ የጠራውን ከደፈረሰው፣ የጸዳውን ከአደፈው፣ ሳይለዩ ለሚያወሩት ደካሞች ሜዳውን ያሰፋላቸዋል፤ የወያኔ/ኢሕአዴግን ፍርሃት ወደመርበድበድ ይለውጠዋል፤ የጦርነት ጥሩምባ ለሚነፉትም ሜዳውን እያሳየ  የቀረርቶ በር ይከፍትላቸዋል፤ ይህ ሁሉ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ሰላምንና ስምምነትን፣ እድገትንና ብልጽግናን፣ ኩራትንና ክብርን አያስገኝም።</p>
<p>ንስሐ ለመግባት ወኔ ለሌላቸው፣ በሠሩት ጥፋት አገርን ወይም ወገንን በመበደላቸው ዛሬም ለመኩራራት ለሚፈልጉት፣ አርበኛውንና ባንዳውን ባንድ ሚዛን አስቀምጠው ለሚተቹት፣ የኢትዮጵያውያንን ሰውነት አራክሰው ጊዜያዊ ጥቅማቸውን ለሚያከማቹ፣ ኢትዮጵያዊ ዜግነትን በተንኮል እየመነዘሩ የሥልጣን መሰላል ለሚያበጁ ሁሉ ፊት-ለፊት ቆሞ ለሚጋፈጣቸው ኢሳት መድረክ ይሆናል፤ የኢሳት ዋና ጥቅሙ እዚህ ላይ ነው፤ ይህንን ተግባር ለመፈጸም ኢሳት የኢትዮጵያ፤ ኢሳት የኢትዮጵያውያን ሁሉ እንዲሆን መንገዱን እንጥረግ፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ በባለቤትነት የሚመራውና የሚያካሂደው እናድርገው፤ ይህ የኢትዮጵያ ሕዝብ በኢሳት ላይ ያለው መብት ነው ከተባለ፣ ግዴታውንም አብሮ መቀበል ሳይታለም የተፈታ ይሆናል፤ ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚል ሁሉ ግዴታውን በቃል ኪዳን መቋጨት ከቻለ ኢሳት ከቀፈፋና ለመክሸፍ ይድናል።</p>
<p>የእኔ ምኞት ኢሳት በኢትዮጵያውያን ቃል ኪዳን ተገንብቶ በሕገ ኀልዮት እየተመራ አዲስ ዓላማ፣ አዲስ የአሠራር ዘዴ፣ ታሪካዊና ባህላዊ ጉድለቶችን ሁሉ አውቆ በጥንቃቄ እየነቀሰ አዲስ የመተማመንና የመተባበር ባህል ይፈጥራል የሚል ነው፤ (እኔ ቃል ኪዳን የምለው ሁለት ቁም-ነገሮችን የያዘ ነው፤ በአንድ በኩል እውነትን አለመፍራት (ወይም በጥሩ መልኩ ለእውነት መቆም፣) በሌላ በኩል ለአንድ የጋራ ዓላማ የራስን ግዴታ ሳያስተጓጕሉ ለመወጣት በቆራጥነት መቆም፤ ስንት ልጆች አሉህ ተብሎ ሲጠየቅ ሁለት ወይም ሦስት እያለ አጥር ላይ ተንጠልጥሎ የሚመልስ ለቃል ኪዳን አይበቃም፤) ከሩቅ እንደማየው ጥቂት ሰዎች ኢሳትን በቃል ኪዳን ተይዘው ሲጥሩ አብዛኛው ደግሞ በአጋጣሚ እንደተመቸውና እንደፈለገ የተቻለውን የሚያደርግ ምንም ዓይነት ቃል ኪዳን የሌለው ነው፤ ከተሳሳትሁ ደስ ይለኛል፤ አስተያየቴ ትክክል ከሆነ ኢሳት አይዘልቅም፤ መክሸፍ ዕጣ-ፋንታው ይሆናል።</p>
<p>ዓላማውን ሳይመታ እንዳይከሽፍ ኢሳት በቃል ኪዳን መታሰር አለበት፤ እንዴት? ቢባል፣ አንድ ሚልዮን ኢትዮጵያውያን ለኢሳት በአማካይ በወር አሥር ዶላር ለመስጠት ቃል ኪዳን ቢገቡና የየዓመቱን ግዴታቸውን በአንዴ ቢወጡ፣ በወር አሥር ሚልዮን ዶላር (በዓመት አንድ መቶ ሃያ ሚልዮን ዶላር) ኢሳትን  ኢትዮጵያዊነትን የሚያስከብር የሰላምና የፍቅር፣ የብልጽግናና የተስፋ መድረክ ሊያደርገው ይችል ነበር፤ አብዛኛዎቹ ችሎታው ያላቸው ኢትዮጵያውያን ለኢሳት የሚገቡት ቃል ኪዳን ለጥሬ ሥጋና ለመጠጥ የገቡትን ቃል ኪዳን ካላሸነፈ ታማኝ በየነን በያገሩ እየላከ በሚያደርገው ዓመታዊ ቀፈፋ ኢሳት ይገነባል ብዬ ለማመን ያሰቸግረኛል፤ በኢሰመጉ አይቼዋለሁ።</p>
<p>ቀፈፋ ወይም ልመና አንዱና ዋናው የባህል ሕመም ነው፤ እያንዳንዳችን ከዚህ ሕመም ለመዳን በራሳችን ላይ መዝመት የሚያስፈልገን ይመስለኛል፤ በተለይ በአገር ጉዳይ፣ በወገን ጉዳይ ማን ነው ለማኝ? ተለማኙስ ማን ነው? ስለአገሩና ስለወገኑ ችግር የማያውቅ አለ? ለማወቅ የማይፈልግ ይኖራል እንጂ የኢትዮጵያና የኢትዮጵያውያን ችግር ገሀድ ነው፤ በአስከፊ መልኩ ለመረዳት የሚፈልግ በመረረ ቋንቋ የተጻፈውን የዶር. በድሉ ዋቅጅራን ሀገሬ ገበናሽ <a href="http://wp.me/p2jGCk-6d">(ክፍል አንድ</a>፣  <a href="http://wp.me/p2jGCk-6g">ክፍል ሁለትና</a> <a href="http://wp.me/p2jGCk-6k">ክፍል ሦስትን</a>)  ያንብብ።  አንብቦ ካላለቀሰ፣ አልቅሶ ‹‹ምን ላድርግ!›› የሚል ቁርጠኛነት ያላደረበት በዓመት አንድ ጊዜ በታማኝ ቀፈፋ አገሩንና ወገኑን መርዳት አይችልም፤ እምነቱ ካለ፣ ስሜቱ ካለ በገንዘብ የሚደረግ ማናቸውም እርዳታ የመጨረሻው፣ መናኛው ነው፤ መናኛ የሚያደርገው የገንዘቡ መብዛት ወይም ማነስ አይደለም፤ ለአገርና ለወገን ከዚያ በጣም የበለጠ የሚከፈል ዋጋ በመኖሩ ነው፤ አያቶቻችንና ቅምአያቶቻችን የከፈሉት ዋጋ በገንዘብ አይመነዘርም፤ እነሱ በሕይወታቸው ያስገኙልንንና እኛ በገንዘብ የሸጥነውን ኩራትና ክብር በገንዘብ ብቻ አናስመልሰውም፤ ቃል ኪዳን እንግባ!</p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/549"     class="crp_title">መርዝ ከውጭ ይረጫል ወይም ከውስጥ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/843"     class="crp_title">ፍሬ-አልባ ጩኸት &#8211; ከፕ/ር መስፍን&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3109"     class="crp_title">የአቶ አስገደ ልጆች ምን ወንጀል ሠሩ?</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1677"     class="crp_title">ዳምጠው ወያኔ/ኢሕአዴግና አፈና&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2276"     class="crp_title">እዉነተኛና ዘላቂ ግንባታ</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=83025</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>በአካል ቅኝ ሳንገዛ፣ ለምን የኅሊና ቅኝ ተገዥዎች ሆን? – ከተክሌ የሻው</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3327</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3327#comments</comments>
		<pubDate>Sun, 19 May 2013 00:25:56 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3327</guid>
		<description><![CDATA[ከተክሌ የሻው በዘመነ ቅኝ አገዛዝ፣ በአውሮፓውያን ቅኝ ገዥ ኃይሎች ያልተገዛች፣እንዲያውም የቅኝ ገዥዎችን ቅስም በመስበር ነፃነቷንና ማንነቷን አስከብራ የኖረች ብቸኛ አገር ኢትዮጵያ መሆኗን የዓለም ታሪክ የሚያውቀው ብቻ ሳይሆን፣የሚደነቅበት ጭምር እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ከዘመነ ቅኝ አገዛዝ ቀደም ባሉት ዓመታትም የግዛት ማስፋፋት ዓላማን ተከትለው ኢትዮጵያን በተፅዕኖዋቸው ሥር ለማድረግ የተነሱ ወራሪና ተስፋፊ ኃይሎችን ማለትም ፡- • ከ1521 እስከ 1535 በቱርኮች [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1214">የኢትዮጵያ ሙዚቃ ከየት ተነስቶ ምን&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1575">“አይቴ ብሔሩ ለአማራ . . . የአማራ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1590">ባሁኑ ሰዓት በአማራው ወገናችን ላይ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1761">የአማርኛ ተናጋሪ ኢትዮጵያውያን&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/549">መርዝ ከውጭ ይረጫል ወይም ከውስጥ&#8230;</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/freedome.jpg"><img src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/freedome.jpg" alt="freedome" width="500" height="195" class="alignleft size-full wp-image-3332" /></a><br />
<strong>ከተክሌ የሻው</strong></p>
<p>በዘመነ ቅኝ አገዛዝ፣ በአውሮፓውያን ቅኝ ገዥ ኃይሎች ያልተገዛች፣እንዲያውም የቅኝ ገዥዎችን ቅስም በመስበር ነፃነቷንና ማንነቷን አስከብራ የኖረች  ብቸኛ አገር ኢትዮጵያ መሆኗን የዓለም ታሪክ የሚያውቀው ብቻ ሳይሆን፣የሚደነቅበት ጭምር እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ከዘመነ ቅኝ አገዛዝ ቀደም  ባሉት ዓመታትም የግዛት ማስፋፋት ዓላማን ተከትለው ኢትዮጵያን በተፅዕኖዋቸው ሥር ለማድረግ የተነሱ ወራሪና ተስፋፊ ኃይሎችን ማለትም ፡-<br />
•	ከ1521 እስከ 1535 በቱርኮች ሁለንተናዊ ትብብር ብቻ ሳይሆን፣ በቀጥተኛ የጦር መሣሪያና የሰለጠነ ወታደር ለግራኝ መሐመድ በማቅረብ አገሪቱን በቱርኮች አገዛዝ ሥር ለማዋል የተደረገውን እልህ አስጨራሽ ጦርነት፣<br />
•	በ1571 የቱርኮችን ቀጥተኛ ወረራ ድሆኖ ላይ፣<br />
•	በ1824፣ በ1826፣ በ1829፣ በ1830፣ በ1832፣ ግብፆችን በተደጋጋሚ በባሕረ-ነጋሽ እና በትግራይ ሜዳና ሸንተረሮች ላይ፣<br />
•	በ1867 እና በ1868 ግብፆችን ጉንዳጉንዲትና ጉራዕ ላይ፣<br />
•	በ1877 ድርቡሾችን ኩንፊት ላይ፤ የወራሪዎችና የተስፋፊዎችን አከርካሪ በመስበር አይደፈሬዎቹ አባቶቻችን ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነትን አስከብረው ለትውልድ በኩራት ማሸጋገራቸውን እናውቃል፡፡ ዓለምም በዚህ አኩሪ የማንነት ተጋድሎ ኢትዮጵያውያንን ሲያደንቅና ሲያከብር መኖሩ ሐቅ ነው፡፡(ተክሌ የሻው፣2003፡16)<br />
በኋላም በዘመነ ቅኝ አገዛዝ ጀግኖች አባቶቻችን በ1896 ጣሊያንን አምባላጌ፣ መቀሌና ዐድዋ ላይ፣ ከ1928 እስከ 1933 የጣሊያንን ፋሽስት ጦር በኢትዮጵያ ዱር ገደሎች ባካሄደው ተከታታይ የነፃነትና ማንነትን የማስከበር ጦርነት፣ በዚህም በከፈሉት ወድር የለሽ ሁለንተናዊ መስዋዕትነት አገራችን የቅኝ ገዥዎች  ፍላጎት ተሸካሚ እንዳትሆንና ማንነቷን አስከብራ እንድትዘልቅ ሆኗል፡፡ ይህ የነፃነትና ማንነትን አስጠብቆ የመዝለቅ ተጋድሎ አገራችን ኢትዮጵያ “የነፃነት ምሽግ” የተሰኘ ውድ ስም እንድታተርፍ አድርጓታል፡፡ ይህን የነፃነት ምሽግነቷን በተመለከተ በ17ኛው ምዕተ ዓመት የኖረው ፖርቹጋላዊው የታሪክ ሊቅ ሉዊስ ኡሬታ ሐበሻ የሚለውን ቃል በአረብኛ፣በቱርክ፣ እና በኢትዮጵያ ቋንቋዎች ትርጉሙ የባዕድ ንጉሥ ግዛት የማታውቅ ነፃና ራስ ገዝ ማለት ነው፤ኢትዮጵያ የምትባለውም ልክ እንደምነግራችሁ ናት፤(ሚሊዮን ነቅንቅ 1993፡13) በማለት የነፃነት ምሽግነቷን መስክሮላታል፡፡<br />
ይህን ተከታታነት ጠብቆ የዘለቀን የነፃነት ምሽግነት የናይጀሪያ መሪ የነበሩት ናምዲ አዚክዊ “ኢትዮጵያ በዓለም ገጽ ከጠፉ የጥቁር ግዛቶች የተረፈች ብቸኛ የተስፋ ችቦ ነች፡፡ የአፍሪካውን አባቶችና አያቶች በዚህ አህጉር አቋቁመውት ለነበረው ሥርዓተ-መንግሥት ሀውልት ነች፡፡ ጓደኞቿ አገሮችና ወራሾቻቸው ከፖለቲካ ታሪክ ገጽ ከተሰረዙ በኋላ ፣ኢትዮጵያ በነፃነት መቆየቷ እጅግ የሚያስደንቅ ነው” (ሚሊዮን ነቅንቅ፣ 1993፡14) በማለት የአባቶቻችን የነፃነት ተጋድሎ አኩሪ ብቻ ሳይሆን፣ ለጥቁሮች ማንነት ምሳሌ መሆኗን ገልጠውታል፡፡<br />
በተመሳሳይ ሁኔታ ጆርጅ ኤድመንድ ሄይንስ የተባሉ ጥቁር አሜሪካዊ የኢትዮጵያን በነፃነት ተጠብቆ መዝለቅ እንዲህ በማለት ገልጸውታየመል፡፡ “ኩሩዋና ነፃዋ ኢትዮጵያ አፍሪካዊ ደም ላላቸው ጥቁሮች የነፃነት፣የራስ መቻል፣ከዘመናዊ ሥልጣኔ መልካም መልካሙን  የመቅሰምና የንቃተ-ኅሊና ምልክት ሆናለች፡፡”( ሚሊዮን ነቅንቅ፣1993፡15)  ከዚህ ሁሉ በተጨማሪ ኢትዮጵያ፣ ከቅኝ ገዥዎች ነፃ የወጡ የአፍሪካ አገሮች የባንዲራዎቻቸውን ቀለሞች አረናጓዴ፣ ብጫና ቀይ ቀለማት ያደረጉት፣ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት( የአፍሪካ ኅብረት) እና የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ጽ/ቤቶች አዲስ አበባ ላይ የተመሠረቱትና ኢትዮጵያ የአፍሪካ መዲና ለመባል ያበቃት ነፃተቷን ጠብቃ በማቆየት ለአፍሪካ የነፃነት ተጋዮች ባበረከተችው የቁሳቁስና የሞራል ድጋፍ መሆኑ ነው፡፡ ይህም ያለፈ መልካምሙና አኩሪው ታሪካችን  ነው፡፡<br />
ቅኝ ገዥ ኃይሎች የቅኝ ግዛት ዓላማቸውን ያስፋፉት በቀጥተኛ የኃይል ወረራና ጦርነት ብቻ እንዳልሆነ ይታወቃል፡፡ እንዳውም አብዛኛዎቹን አገሮች በቅኝ ግዛታቸው ቀንበር ሥር ያዋሉዋቸው፣ የየአካባቢውን የጎሣና የነገድ መሪዎችን በመናኛ ጥቅማ-ጥቅሞች በመደለል መሬቶችን በመግዛት የራሳቸው በማድረግ፣ሃይመኖታቸውን በማስቀየርና በአገር አሳሽነት ስም በመግባት የየአገሮቹን ባህል፣ቋንቋና ታሪክ በማጥናት ሥልጣኔን እናስፋፋለን በሚል ሽፋን ማንነታቸውን አስጥለው የሌላቸውንና ከእነርሱም ጋር ሊዋሐድ የማይችል ማንነትን እንዲላበሱ በማድረግ እንደሆነ የቅኝ አገዛዝ ታሪክ ያስረዳል፡፡ ለዚህ አባባል ታማኒነት የቀድሞው የኬንያ መሪና የኬንያ የነፃነት አባት የሚባሉት ጆሞ ኬንያታ “ማኦ ማኦ” በተሰኘው የነፃነት እንቅስቃሴ ወቅት የተናገሩትን መጥቅሱ ተገቢ ነው፡፡ “እንግሊዞች ወደ አገራችን ሲመጡ መጽሐፍ ቅዱስ ይዘው መጡ፤ እነርሱም ዐይናችን ጨፍነን፣ አንገታችን ደፍተን እንድንጸልይ አስተማሩን፣አንገታችን ደፍተን ዐይናችን ጨፍነን ከጸለይን በኋላ ፣ዐይናችን ገልጠን አንገታችን ስናቀና፣ መጽሐፍ ቅዱሱ የኛ፣መሬቱ የነርሱ ሆኖ አገኘነው፡፡”  ሲሉ የተናገሩት ቅኝ ገዥዎች በምን መልክ ሕዝቦችን ቅኝ ተገዥ እንዳደረጓቸው በተጨባጭ ያስረዳል፡፡ አገላለጹ ዕውነኛውን  የአፍሪካን የቅኝ አያያዝ ስልት በሚገባ ያሳያል፡፡<br />
 በርካታ ቁጥር ያላቸው የአፍሪካ አገሮች በቅኝ ግዛት ቀንበር ሥር የወደቁት ከፍሲል ጆሞ ኬንያታ በገለጡትና የጎሣ መሪዎቹ  በሸጡት መሬት ላይ በመቆናጠጥ ይዞታቸውን በልዩ ልዩ መንገዶች በማስፋት ነው፡፡ በእኛም ታሪክ ጣሊያን ኤርትራን ለ50 ዓመታት በቅኝ ግዛት እንዲይዛትና ለተከታታዮቹ የዐድዋና የአምስቱ አመታት የአርበኝነት ትግል የዳረገን  ፣ሡልጣን ኢብራሂም የተባለው የአፋር ባላባት አሰብን ለጣሊያን የቅኝ ገዥ አስፋፊ ቡድን  በመሸጡና ቅኝ ገዥው ኃይል መላዋ ኢትዮጵያን በቁጥጥሩ ሥር ሊያውልበት የሚችልበትን መንገድ ያመቻቸ መቆናጠጫ መሬት በማግኘቱ እንደሆነ በግልጽ ይታወቃል፡፡<br />
በሌላም በኩል ኢትዮጵያውያን ከፍ ሲል በተጠቀሱት በቀጥታ ወረራ ቅኝ ተገዥ ሊያደርጓቸው የቃጡትን ኃይሎች ድል ነስተው የመለሷቸውን ያህል፣በሃማኖት፣ በአገር አሳሽነትና በሥልጣኔ አስፋፊነት ስም የፍላጎታቸው ተገዥዎች ሊያደርጓቸው መጽሐፍ ቅዱስ ይዘው የመጡ አስመሳይ ወንጌላውያንን፣ አባቶቻችን “ መጽሐፍ ቅዱሱም ሊቃውንቱም በአገራችን አሉ፤ ከእናንተ የምንሻው የዕደጥበብ ሙያተኞችን ነው፤” በማለት መልሰዋቸዋል፡፡ ይኸም ብቻ አይደለም፡፡ የክርስቶስን መወለድና መጠመቅ ያልሰሙትንና ሊሰሙም ያልፈለጉትን የአሕዛብ አገር ትታችሁ ከዚህ ምን ልትሠሩ መጣችሁ/የሚሉ አፋጣጭ ጥያቄዎችን በማቅረብ ለአስመሳይ ወንጌላውያኑ ከንቱ ስብከት ኅሊናቸውን ቀርቶ ጆሮአቸውን ባለመስጠት ወደመጡበት እንዲመለሱ ማድረጋቸው ግልጽ ነው፡፡ በአገር አሳሽነትና በሥልጣኔ አስፋፊነት ስም የገቡትንም አገሪቱ ካሏት የከበሩ ነገሮች የተመረጡትን በገጸ-በረከትነት በመስጠት፣ የአገራቸውን አፈር ግን ከምንም በላይ የሚወዱትና በማንም ሊወሰድ እንደማይችል ለማሳየት በጫማቸው አፈር ይዘው እንዳይሄዱ እግራቸውን አሳጥበው እንደሸኙዋቸው ታሪካችን ያስረዳናል፡፡ እነዚህንና መሰል አባቶቻችን ለነፃነትና ማንነትን አስጠብቆ ለመዝለቅ ያደረጓቸው ተጋድሎዎች  ከአካላዊና ኅሊናዊ ቅኝ ተገዥነት ተጠብቀን ፣ማንነታችንና ነፃነታችን አረጋግጠን እንደንቆይ እንዳደረጉን እንረዳለን፡፡ ይህ የታሪካችን እጅግ መልካሙ፣አስደናቂውና አንፀባራቂው ምዕራፍ ነው፡፡ ታሪኩ ኢትዮጵያውያንን ብቻ ሳይሆን፣ መላውን የጥቁር ዘር ያኮራና ያስመካ ነው፡፡<br />
ከዚህ ላይ የሚነሱ ጥያቄዎች አሉ፡፡ ኢትዮጵያውያን ይህን የነፃነት ምሳሌነትና የኢትዮጵያዊነት ምንነት መገለጫ የሆኑ ዕሴቶቻቸውን ምን ያህል ጠብቀው ይዘዋቸዋል? የቱንስ ያህል አዳብረዋቸዋል? ጉዞ አቸው ወደ ፊት ነው ወይስ ወደ ኋላ? የሚሉት ናቸው፡፡  ለነዚህ ጥያቄዎች ተገቢ መልሶች ለመስጠት በአምስት ኣመቱ የአርበኝነት የተጋደሎ ዘመን የነበረውን የሕዝቡን አመለካከትና ከድል በኋላ የተፈጠረውን ትውልድ አመለካከት የተቀረጸባቸውን ነባራዊና ኅሊናዊ ሁኔታዎች በቅጡ ማገናዘብ ይጠይቃል፡፡ ለተነሱት ጥያቄዎች ተገቢ መልስ ለማግኘት ዕውነት እንደሚባለው ኢትዮጵያውያን የኅሊና ቅኝ ተገዥዎች ሆነናል? የሚለውን መሠረታዊ ጥያቄ መመለስ አለብን፡፡ አጭሩ መልስ አዎ! ኢትዮጵያውያን የኅሊና ቅኝ ተገዥዎች ሆነናል የሚል ነው፡፡ ከዚህ ድምዳሜ ላይ ለመድረስ ግን በምን በምን ምክንያቶች ለኅሊናዊ ቅኝ ተገዥነት እንድንዳረግ ያደረጉንን መሠረታዊ ምክንያቶች ማባራራቱ ብዥታ የሌለበት ግንዛቤ እንድንጨብጥ ይረዳናል፡፡<br />
1.	ከድል በኋላ የመንግሥቱ ቢሮክራሲ በስደተኛውና በባንዳው ቡድን ጥምር ጥምረት መዋቀር፤<br />
ማንም የአርበኝነት ትግሉን ዘመን ታሪክ በአግባቡ የተከታተለ ሰው ሊረዳው እንደሚችል፣ያ ወቅት ኢትዮጵያውያን ከሦስት  የተከፈሉበት ነበር፡፡ አርበኛ፣ስደተኛና ባንዳ፡፡ አርበኞቹ እንደጥንት አባቶቻቸው እምነታቸውን ያልለወጡ፣ማንነታቸወን ያልካዱ፣በዕለታዊ ጥቅማ-ጥቅሞች ባንዲራቸውንና አገራቸውን ያልካዱ፣ ሃይማኖታቸውን ያልለወጡ፣ኢትዮጵያ ወይ ሞቴ ብለው በቁርጠኝነት የቆሙና ነፃነታችንን ተጋድለው ያረጋገጡልን ናቸው፡፡ ከነዚህ የቁርጥ ቀን ልጆች መካከል ራስ አበበ አረጋይ፣ ደጃዝማች ደረሱ ዱኬ፣ ደጃዝማች ዑመር ሰመተር፣ ራስ አሞራው ዉብነህ፣ደዝማች በላይ ዘለቀ፣ደጃዝማች ታደሰ ይማም፣ፊታውራሪ ሽፈራው ጌታሁን፣ደጃዝማች አድማሱ ብሩ፣ደጃዝማች ወንደወሰን ካሣ፣ደጃዝማች አበራ ካሣ፣ ራስ ሙሉጌታ ይገዙ፣ራስ እምሩ ኃይለሥላሴ፣  ብጹዕ አቡነ ጴጥሮስ፣ብጹዕ አቡነ ሚካኤል እና አያሌ ስማቸው ተዘርዝሮ የማያልቅ፣ግን ስለተጋድሎአቸው ምንም ያልተባለላቸው ዕውነተኛ ኢትዮጵያውያን ይገኙበታል፡፡<br />
ስደተኞች የሚባሉት በጠላት ከመገዛት መሰደድን የመረጡና በልዩ ልዩ ምክንያቶች  ከኢትዮጵያ ወጥተው በተለያዩ የዓለም ክፍሎች ኑረው፣ ከድል በኋላ ቀድመው ካገር የወጡትን ንጉሠ ነገሥቱን ተከትለው የገቡ ናቸው፡፡  በዚህ ክፍል ውስጥ የንጉሠ ነገሥቱ ቤተሰቦች፣መሣፍንቱና መኳንንቱ ማለትም ፡-<br />
1.	ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ፣<br />
2.	ልዑል አልጋወራሽ አስፋው ወሰን ኃይለሥላሴ፣<br />
3.	ልዕልት ወለተ-እስራኤል ሥዩም የአልጋወራሹ ባለቤት (ከልጆቻቸው ደጃዝማች ዘውዴ ገብረሥላሴና ከእግጋየሁ አስፋወሰን ጋር)<br />
4.	ልዕልት ተናኘወርቅ ኃይለሥላሴ ከአምሰት ልጆቻቸው ጋር፣<br />
5.	ልዑል መኮንን ኃይለሥላሴ የሐረር መሥፍን፣<br />
6.	ልዕልት ፀሐይ ኃይለሥላሴ፣<br />
7.	ልዑል ሣህለሥላሴ ኃይለሥላሴ፣<br />
8.	ብፁዕ እጨጌ ገብረ ጊዮርጊስ፣<br />
9.	ልዑል ራስ ካሣ ኃይሉ ፣<br />
10.	ወይዘሮ ጽጌ-ማርያም በሻህ የልዑል ራስ ካሣ ባለቤት፣ከሁለት ልጆቻቸው ጋር፣<br />
11.	 ልዕልት የሻሽ ወርቅ ይልማ ፣<br />
12.	ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ፣<br />
13.	ጸሐፊ ትዕዛዝ ወልደጊዮርጊስ ወልደ ዮሐንስ፣<br />
14.	አቶ መኮንን ሀብተ ወልድ፣<br />
15.	አቶ አክሊሉ ሀብተወልድ፣<br />
16.	ደጃዝማች ከበደ ተሰማ፣<br />
17.	ደጃዝማች ክፍሌ ዳዲ፣<br />
18.	ልጅ አበበ አርኣያ፣<br />
19.	አባ ሓና ጅማ፣<br />
20.	ደጃዝማች ነሲቡ ዘማኔል፣<br />
21.	ደጃዝማች መኮንን እንዳልካቸው፣<br />
22.	ደጃዝማች አበበ ዳምጠው፣<br />
23.	ደጃዝማች ዐምደ ሚካኤል፣<br />
24.	ፊታውራሪ ታፈሰ ሀብተሚካኤል<br />
25.	ፊታውራሪ ተሰማ ባንቴ ፣ ወዘተ ያካተተ እንደነበር መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡(ገብረወልድ እንድዳ ወርቅ  2000፣105-106)<br />
 ባንደው በቁጥሩ ከሁሉም ከፍተኛ የሆነ፣ ሁለመናውን ለጣሊያን ፍላጎት ያስገዛ፣የአንድነታችንና የማንነታችን አውራ ጠላት የነበረው ነው፡፡ ስም ከነበራቸው ታላላቅ ሰዎች ከሚባሉት ሁለንተናቸውን ለጣሊያን ሰጥተው ማንነታችን በእጅጉ ከጎዱት ባንዳዎች መካከል ለአብነት፣ራስ ኃይሉ ተክለሃይማኖት፣ራስ ሥዩም መንገሻ፣ደጃዝማች አያሌው ብሩ፣ደጃዝማች ኃይለሥላሴ ጉግሳ፣አቶ አምደ ሚካኤል ደሳለኝ፣አቶ አድማሱ ረታ፣አቶ ለማ ወልደ ገብርኤል፣አቶ ተፈሪ ሻውል፣ አቶ ገብረ ወልድ እንግዳ ወርቅ፣ብላት ዳዊት እቁበ እግዚእ፣ደጃዝማች አስፍሃ ወልደ ሚካኤል፣ጄኔራል መኮንን ደነቀ፣አቶ ብርሃኑ ድንቄ፣ሻለቃ አሰፋ ለማ፣ሼክ አል ሆጆሌ፣ሡልጣን መሐመድ ሃንፋሪ፣ ደጃዝማች ሆሣዕና ጆቴ፣ ደጃዝማች ዮሐንስ ጆቴ፣ሡልጣን አብዱላሂ ጂፋር፣ሡልጣን አባ ጆቢር አብዱላሂ፣ ራስ ጌታቸው ናደው፣ነጋድራስ አፈወርቅ ገብረየሱስ፣አቶ ይልማ ዴሬሳ፣ብላታ አየለ ገብሬ፣ነጋድራስ ወዳጆ አሊ፣አቡነ አብርሃ፣አቡነ ይስሐቅ   ( ፕሮፌሰር መሥፍን ወልደ-ማርያም፣2005፣16) ደጃዝማች እጅጉ አያሌው፣ ፊታውራሪ ነገደ ዘገዬ   እና አያሌ ሆድ አደር ባንዳዎች ወዘተ ይገኙበታል፡፡ ልብ በሉ! እነዚህ ሰዎች  ቀደም ሲል የአገርና የሕዝብ ሚስጢሮችን ለጣሊያን በመንገር የማንነታችን አሻራዎች እንዲወድሙ ያደረጉ፣አርበኞች የሚወጡ የሚገቡበትን በመሰለል ያስገደሉ፣ ያሳሰሩ፣የአገርና የሕዝብ ሀብት ያዘረፉ፣ማንነታችን ጥላሸት የቀቡ ፣ ሕዝቡ ኢትዮጵያዊ ማንነቱን ክዶ ጣሊናዊ ማንነትን እንዲላበስ ኅሊናዊ ጫና ሲያሳድሩ የነበሩ የአገርና የትውልድ አውራ ጠላቶች ናቸው፡፡<br />
 ከዚህ ላይ ልብ ልንል የሚገባን ቁምነገር አለ፡፡ ባንዳዎች ወደውና ፈቅደው ነፃነታቸውንና መብታቸውን ለቅኝ ገዥው ኃይል የሰጡ ናቸው፡፡ ማንነታቸውን  ክደው የቅኝ ገዥውን  ሁለንተናዊ ማንነት ለመላበስ የጣሩ ናቸው፡፡ በመሆኑም ከወራሪው ኃይል በላይ የኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት ጠላቶች ናቸው፡፡ የባንዳው ኃይል፣ለፋሽስቱ ቢሮክራሲ በመረጃ አቅርቦት፣በተላላኪነት፣በሹፌርነት፣ በዘበኝነት፣በቤት ውስጥ አሽከርነት፣በአስተርጓሚነት በመሳሰሉት ሥራዎች ተሰማርቶ ይሠራ የነበር ስለነበር፣ የማንበብና የመጻፍ፣ልምድና ችሎታ እንዲያዳብር አድርጎታል፡፡ እግረ መንገዱንም ከአማርኛና ሌሎች ኢትዮጵያዊ ቋንቋዎች በተጨማሪ የቅኝ ገዥ ቋንቋዎችን የማንበብና የመጻፍ ዕውቀት እንዲጨብጥ ሆኗል፡፡ ይህም  የዘመናዊ ቢሮክራሲን አሠራር እንዲለማመድ በር የከፈተለት መሆኑ ግልጥ ነው፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ ስደተኛው ቡድን ተሰዶ በኖረባቸው አገሮች የዘመናዊ ቢሮክራሲን አሠራርና ሌሎች ቋንቋዎችን በተለይም እንግሊዝኛና ፈረንሣይኛን ቋንቋዎች እንዲውቅ ሁኔታዎች ግድ እንዳሉት እንረዳለን፡፡<br />
ከድል በኋላ የኢትዮጵያ ቢሮክራሲ ሲዋቀር፣ ላገር የሠሩ ሰዎች መሾም መሸለም ሲገባቸው፣በአገር ላይ የሠሩት ከሐዲዎቹና ባንዳዎቹ ተሹዋሚና ተሸላሚ ሆኑ፡፡ወሳኝ ለሆኑት ሕግ የማውጣት፣ሕግ የመተርጎምና የወጡትን ሕጎች  የማስፈጸም ኃላፊነቶችን የሚረከቡ ሰዎች መመዘኛ ለኢትዮጵያዊነት ያለ ታማኝነት፣ በነፃነት ትግሉ ዘመን የተከፈለ መስዋዕትነት ሳይሆን፣ ከዘመናዊ ቢሮክራሲ ጋር ያለው ቁርኝት፣የውጭ አገር ቋንቋና  የጽሕፈት ችሎታ ሆነው ቀረቡ፡፡ በዚህም የተነሳ ስደተኛውና ባንዳው ቡድን የአንበሣ ድርሻውን ወሰደ፡፡ የነፃነት ታጋዩና ዕውነተኛው ኢትዮጵዊ የበለል ተጣለ፡፡ ይህ ድርጊት ያሳዘናቸው አርበኞችም ደርጊቱን እንዲህ ሲሉ ገለጡት፡፡<br />
አገሬ ኢትዮጵያ ሞኝነሽ ተላላ፣<br />
የሞተልሽ ቀርቶ የገደለሽ በላ፤<br />
ዳር ድንበር ጠብቀን ባቆየናት አገር፣<br />
ውጤቱ ተረፈን ባፍንጫ መናገር፤<br />
ይህ ስደተኛና ባንዳ ቡድን የቀሰመው ዕውቀት ከኢትዮጵያዊነት ዕሴቶች ፣ማንነት፣ባህል፣ቋንቋ፣ሃይማኖትና አጠቃላይ ሁለንተናዊ መስተጋብር ጋር ምንም ዓይነት ቁርኝት የሌለው ስለነበር የሚያደርጋቸው እንቅስቃሴዎች ከማንነት የሚያፋታ እንጂ፣ማንነትን የሚያዳብር ባለመሆኑ ትውልዱን ቀስ በቀስ ወደ ኅሊናዊ ቅኝ ተገዥነት ቦይ አንኮልኩሎ  እንዳስገባው እናያለን፡፡ ወሳኝ የመንግሥት መዋቅሮች በባንዳዎችና በስደተኞች መያዝ፣ ባንዳነትና አገር ክዳት ወንጀል መሆኑ ቀርቶ እንደመልካም ሥራ እንዲታይ አስገደደ፡፡ ይህም በተተኪው ትውልድ አመለካካት ላይ አርበኝነት፣ለማንነት መቆምና መታግለ እርባናቢስ እንደሆነ፣በኅብረተሰቡ ውስጥ ክብርና ሞገስ የማያስቸር፣ በአንፃሩ ከሐዲነትና ባንዳነት አሹአሚና አሸላሚ መሆኑን በተጨባጭ እንዲያይ በማድረጉ ኅሊናውን ለቅኝ ተገዥነት ማመቻቸት እንዳለበት በአገሪቱ የሚካሄዱት ድርጊቶች ጠጣር ዕውነት ሆነው ታዩት፡፡በአገሪቱና በሕዝቡ አንጡራ ሀብት ወንጀለኞችና ባንዳዎች እንደፈለጉ ሲናኙበት፣ ቤተሰባቸውን ሲያስተምሩበት፣ ልጆቻቸውን ለቀጣዩ ትውልድ ገዥነት ሲያሰለጥኑበት፣ አርበኛው የበይ ተመልካች መሆኑንን  በገሐድ አየ፡፡ የአርበኛው ልጆች በአባቶቻቸው ተጋድሎ የሚያፍሩ እንጂ፣ የሚመኩና የሚኮሩ እንዳይሆን ተመለከተ፡፡ ባንዳነት ማሳፈሩ ቀርቶ መኩሪያ ሆነ፡፡ አርበኝነትና አገር ወዳድነት አዋራጅና የደህነት መገለጫ ሆኖ ታዬ፡፡ ይህ ሁኔታ ትውልዱ ባንዳነትን እንደተገቢ ተግባር እንዲቆጥረው ገሐዳዊ ምሳሌ ሆኖ ቀረበ፡፡ ውጤቱም  ከድል በኋላ የተዋቀረው የንጉሠ ነገሥቱ አስተዳደራዊ መዋቅርና በመዋቅሩ የተካተቱ ሰዎች ማንነት ተከታዩን ትውልድ የኅሊና ቅኝ ተገዥነትን እንዲለማመድ አመቻቸው፡፡<br />
2.	የትምህርት ፖሊስ በኢትዮጵያዊ ማንነት ላይ አለመመሥረት፣<br />
በስደተኛውና በባንዳ የተዋቀረው የንጉሠ ነገሥቱ ቢሮክራሲያዊ  አስተዳደር የቀየሰው የትምህርት ፖሊሲ ትውልዱ በኢትዮጵያዊ ማንነቱ ላይ ተመሥርቶ፣ በሂሳብ  ዕውቀት ላይ መሠረቱን የጣለ፣ለምርምርና አዳዲስ ቴክኖሎጂን አፍላቂ በሚሆንበት መልኩ  እንዲሆን አላደረገም፡፡ የትምህርት ፖሊሲው ትውልዱን ከኢትዮጵያዊ ማንነቱ ፈጽሞ የሚያፋታ፣የራሱን ማንነት እየናቀ የሌሎችን አድናቂና ተከታይ በሚያደርግ መልኩ የተቀየሰ ነበር፡፡ ሥርዓተ ትምህርቱ ለፈረንሣና ለእንግሊዝኛ ቋንቋዎች፣እንዲሁም ለማኅበራዊ ሣይንሶች ልዩ ትኩረት የሰጠና ከኢትዮጵያ ታሪክ፣ ባህልና ለዘመናት ይዛው ከመጣችው አሠራር ጋር የማይገናኝ ስለነበር፣ ትውልዱ ውጭ አምላኪና የራሱን ማንነት ሳያውቀው ቀስበቀስ እያወለቀ እንዲጥል ሠፊ በር ከፈተለት፡፡ ይህም በመሆኑ፣ “የዐዳም ቋንቋ እንደሆነ የሚነገርለት፣እግዚአብሔር ከሙሴ ጋር እንደተነጋገረበት ብዙ” የሚባልለት የግዕዝ ቋንቋ ከትምህርት ቤትና ከመንግሥት ብቻ ሳይሆን በቤተክረስቲያንም አገልግሎት ሊሰጥበት ከማይቻልበት ደረጃ ተደሷል፡፡ ኢትዮጵያዊ ጨዋነት፣ባህል፣ሥነ-ምግባርና አመለካከት በትምህርት ሥርዓቱ ውስጥ ባለመካተቱ ፣ወጣቱ ትውልድ የእርሱ የሆነውን ወርቁን ነገር እየጣለ፣ የርሱ ያልሆነውን ኩበቱን ሙጭጭ ብሎ እንዲያዝ ተነገረው፡፡የኢትዮጵያዊነት ልዩ መታወቂያ የሆነው የጽሑፍ ቋንቋ አማርኛ ቀስበቀስ ከትምህርት መገናኛነቱ እንዲወጣ ተደረ ፡፡ የትምህርቱ ይዘት የኢትዮጵያን ባህል፣ታሪክ፣መልከዐ-ምድር፣ቋንቋ፣ ሥነ-ልቦና፣የሕዝብ አደረጃጀትና የአጠቃላይ ማኅበራዊ ግንኙነት ምንነትን ፈጽሞ ግንዛቤ ያስገባ አልነበረም፡፡<br />
 የታሪክ ትምህርት ስለግሪክ፣ስለአውሮፓ፣ስለሮም ፣ስለሜሶፖታሚያ፣ስለግብፅ፣ ወዘተ እንጂ፣ ስለኛው ረጅምና አኩሪ ታሪክቻችን፣ስለአርበኞቻችን ማንነትና  ተጋድሎ የሚያወሱ ትምህርቶች ለትውልዱ አይሰጡም ነበር፡፡አባቶቻችን ከፖራቹጋሎች፣ከቱርኮች፣ከመሐዲስቶች፣ከግብፆች፣ ከጣሊያኖችና ከአውሮፓ ኃያላን ጋር ስላደረጉት የነፃነትና ማንነትን የማስከበር ተጋድሎ፣የተጋድሎው መሪ ተዋንያን ማንነት ትውልዱ እነዲያወቅ አልተደረገም፡፡ የነካሌብን፣የነኢዛናን፣የነላሊበላን፣ የነዘርዐ-ያዕቆብ፣የነሠርጸድንግል፣የነዐምደ-ጽዮን፣የነልብነድንግል፣የነገላውዲዮስ፣የነቴዎድሮስ፤የነዮሐንስና የነምኒልክ ወዘተ ፖለቲካዊና ወታደራዊ የአመራር ጥበብና ችሎታ፣የነገብርዬ፣የነአሉላ አባነጋ፣የነሀብተጊዮርጊስ ዲነግዲ፣የነገበየሁ ተክሌ የነኮሎኔል አቢሳ አጋ የጦር ሥልትን ዲፕሎማሲያዊ ጥበብ ወዘተ  ታሪክ ትውልዱ በቅጡ እንዲያውቀውና እንዲመካበት አልተደረገም፡፡ እንኳን ያን ጊዜ ዛሬም የለም፡፡<br />
የመልከዐ-ምድሩ(ጂኦግራፊ) ትምህርት ስለዓለምና አሕጉሮች እንጂ ፣ስለኢትዮጵያ ወንዞችና ተራሮች፣ ማዕድን፣የውኃ ሀብት፣ የአየር ጠባይ፣የእንስሳት ሀብት፣የመንግሥት ኃላፊነትና ግዴታ፣የሕዝብ መብትና ግዴታ፣ ወዘተ በየደረጃው የሚሰጡ አልነበረም፡፡ የትምህርቱ አጠቃላይ ዓላማ ወደ ውጭ የሚያይ እንጂ፣ ወደ ውስጥ ማሳየት የማይችል ስለነበር፣ትውልዱ ወደ ውጭ እንጂ ወደ ውስጥ እንዲመለከት አላስቻለውም፡፡ ወደ ውጭ መመልከት ደግም፣ማንነትን ጥያቄ ውስጥ በማስገባት ሌላ ማንነትን ለመላበስ የሚያመቻች በገዛ ፈቃድ ለቅኝ ተገዥነት ራስን ማመቻቸት እንደሆነ በተጨባጭ እያን ነው፡፡ በትምህርቱ ውስጥ የሚካተቱት የመልካም ነገሮች ማመላከቻዎች  ኢትዮጵያዊ አለመሆን፣ትውልዱ የራሱ የሆነ፣የተሻለ ነገር እንዳለው ሊገነዘብ ባለመቻሉ፣በተነገረው ምሳሌና ማነፃፀሪያ መሠረት አሻግሮ እንዲመለከት ግድ አለው፡፡  በመሆኑም የ1960 ዎቹ ለውጥ ናፋቂ የነበረው ትውልድ የሽምቅ ውጊያን ከቴዎድሮስ ፣ከምኒልክ፣ከዮሐንስ ከነአሉላ፣ገብርዬ አቢሳ አጋነ፣ አበበ አረጋይ ወዘተ ለመቅሰም ባለመቻሉ የተከተለው የማኦን፣የሆቺሚንንና የቼጉቬራን የሽምቅ ውጊያ ስልት ነበር፡፡ የዘመረውም “ፋኖ ተሰማራ ፣እንደነ ሆቺሚን እንደቼጉቬራ” ሲል ነበር፡፡ የአገሩን ፋኖዎች ልዩ ዕውቀትና ችሎታቸውን ባለማወቁ በቃል በተነገረውና ተጽፎ ባገኛቸው በውጭዎቹ ሰዎች ማንነት ተከታይ ለማፍራት ቀሰቀሰባቸው፡፡ይህም ለኅሊና ቅኝ ተገዥነት ራሱን እንዲያመቻች እንዳደረገው መገንዘብ ይቻላል፡<br />
በሌላ በኩል፣ለከፍተኛ ትምህርት ወደ ውጪ የሚላኩት ፣ ወጥ በሆነ መንገድ ላገሪቱ የሚያስፈልጓትን ሙያተኞች ከራሷ ፍላጎት አኳያ በምትፈልገው የዕውቀት መሥክ የሚሰለጥኑ አልነበሩም፡፡ የሚሰለጥኑት በየግለሰቦቹ ፍላጎትና የትምህርቱን ዕድል በፈቀደው መንግሥት ፕሮግራም መሠረት እንደነበር ይታወቃል፡፡ ይህም በመሆኑ፣ሰልጣኞቹ የሚሰለጥኑት ከአገራቸው ነባራዊ ሁኔታ ጋር ግንኙነት በሌላቸው፣የትምህርቱን ዕድል በሰጡ አገሮቸ የትምህርት ፖሊሲ ላይ የተመሠረቱና ከነዚያ አገሮች ታሪክና ባህል፣እንዲሁም ሊደርሱበት ወደ አለሙት ግብ ሊያመራ በሚችል መልኩ እንደነበር ይታወቃል፡፡ ስለሆነም ሠልጣኞቹ ወደ አገር ቤት ሲመለሱ ተመሳሳይ የፖሊሲ አቅጣጫ ለመንደፍም ሆነ ለማስተማር ግብቡ አልነበሩም፡፡ ፈረንሣይ፣ምዕራብ ጀርመን፣እንግሊዝ፣አሜሪካ፣ሶቭዬት ኅብረት፣ምሥራቅ ጀርመን፣ቼኮዝሎቫኪያ፣ቡልጋሪያ፣ሀንጋሪ፣ዩጎዝላቪያ፣ጣሊያን፣ ወዘተ የተማሩት ለየቅል ቆሙ፡፡ ልዩነታቸው በተማሩበት አገር ብቻ ሣይሆን፣በተማሩበት ተቋምና በተማሩት የትምህርት ዓይነት ጭምር ሆነ፡፡ ይህ ልዩነት ደግሞ እንደ ኢትዮጵያዊነት፣ከኢትዮጵያዊነት ዕሴቶች ተነስቶ፣ኢትዮጵያ ጠቀም ወደ ሆነ አስተሳሰብ ለማምራት መንገዱን ዘጋው፡፡ ከዚህ ላይ ርዕዮተዓለማዊ ልዩነት ተርከፍክፎበት ከድል በኋላ ቀለም የቆጠረው ትውልድ ኢትዮጵያን በየራሱ ፍላጎት በመሳል፣ “እኔ ለኢትዮጵያ የተሻለ አስባለሁ፣ከእኔ ውጭ ያሉት ትክክል አይደሉም” ብለው እንዲያስቡና እርስ በራሱ እንዲጠፋፋ መንገዱን አመቻቸ፡፡ የመጠፋፋቱ ግብግብ በከፋ መልኩ መቀጠል ትውልዱ የእርሱነቱ መታወቂያ የሆነች አገሩን እየሸሸ በመገደድና በመውደድ ለኅሊና ቅኝ ተገዥነት ራሱን እንደዳረገ በገሀድ እያየን ነው፡፡<br />
3.	   የአዲስ ገብ ሃይማኖቶች መሥፋፋት፣<br />
ማንም የኢትዮጵያን ሕዝብ ታሪክ የመረመረ ሰው ሊገነዘበው እንደሚችል፣የሕዝቡ መሠረታዊ ሃይማኖቶች፣ኦርቶዶክስ ተዋህዶ፣ሱኒ እስልምና፣አይሁድና ባህላዊ እምነቶች ናቸው፡፡ እንዚህ ሃይማኖቶች አንዱ በሌላው ውስጥ ያለ በመሆኑ፣ኢትዮጵያዊ ማንነትን ፣የአገርና የቤተሰብ ፍቅር፣ነፃነትና አልበገርም ባነይነት፣ በኢትዮጵያዊነት መመካትና መኩራት ልዩ ዕሴቶቻቸው አድርገው የተቀበሉና ለነርሱም ዳብሮ መቀጠል የየእምነቶቹ ተከታዮች አይከፍሉ መስዋዕትነት በጋራ እየከፈሉ የኖሩ መሆኑ ግልጥ ነው፡፡<br />
ከድል ኋላ “ሃይማኖት የግል ነው፣ አገር የጋራ ነው “ በሚለው የንጉሠ ነገሥቱ የሃይማኖት ፖሊሲ ምክንያት በርካታ አዳዲስ ሃይማኖቶች ወደ አገራችን እንዲገቡ ሠፊ በር ከፈቱ፡፡ ቀደም ሲል ገብተው የነበሩትም ተልዕኮአቸውን ያላንዳች ሥጋት እንዲወጡ  ሁኔታዎች  የበለጠ ተመቻቸላቸው፡፡ “ገንፎ ሲያምርበት ተንከባሎ ከቅቤ ማሰሮ ይገባል” እንደሚባለው ሆኖ፣ ቀደም ሲል በሃይማኖት፣በአገር አሳሽነት፣በመሬት ግዥና በቀጥታ ወረራ ኢትዮጵያን ቅኝ ግዛት ለማድረግ ያልቻሉ ኃይሎች ፣ ሕዝቡ ወዶና ፈቅዶ የኅሊና ቅኝ ተገዥ የሚሆንበት መንገድ በስፋት ተከፈተላቸው፡፡ ንጉሠ-ነገሥቱ  ኢትዮጵዊነትን መጠበቅ የሚያስችል ስልት ሳይነድፉ፣ በሃይመኖት ነፃነት ስም ትውልዱ   ለኅሊና ቅኝ ተገዥነት የሚመቻችበትን መንገድ በስፋት  ከፈቱ፡፡ በመሆኑም በርካታ የሃይማኖት ድርጅቶች ወደ አገራችን ገቡ፡፡<br />
አዲስ ገቦቹ ሃይማኖቶች ቀደም ሲል ቅኝ ግዛትን ለማስፋፋት በአፍሪካና በእስያ የተሠማሩ ስለነበሩ የተጠናከ መዋቅር፣በከፍተኛ የመረጃና የሰው ኃይል የተደራጁ ከመሆናቸውም በላይ፣ የቅኝ ገዥ ኃይሎች መዋዕለ ንዋይ በገፍ የሚጎርፍላቸው በመሆኑ ነባሮቹ ኢትዮጵያዊ ሃይማኖቶች ከሚሰጡት መንፈሳዊና ሥጋዊ አገልግሎቶች በላይ ለሕዝቡ  በስፋት መስጠት ጀመሩ፡፡ መንፈሳዊ አገልግሎታቸው በሙዚቃ ፣በጭብጨባና በዳንስ የታጀበ በመሆኑ የአድማጮችን ኅሊና በቀላሉ ሳበ፡፡ ከመንፈሳዊ ትምህርቱ፣ዝማሬውና ሽብሸባው በተጓዳኝ፣ የአውሮፓን ታሪክና ስልጣኔ፣ ሕዝቡ የደረሰበትን የዕደገት ደረጃ የሚያሳዩ ፊልሞችን በብዛት አሰራጩ፡፡ ኢትጵያውያንን የኅሊና ቅኝ ተገዥዎች የሚያደርጉበትን ሁነኛ መሣሪያ የሆነውን የዘመናዊ ትምህርትን ከሃይማኖት ጋር አቀላቅለው የሚያስተምሩበትን የትምህርት ሥርዓት ዘረጉ፡፡ ይህም ብቻ አይደለም፡፡ አብዛኛውን ጊዜ በነፃና አልፎ አልፎም በተመጣጣኝ ክፍያ የሕክምና አገልግሎት መሥጠት ጀመሩ፡፡ ዘወትር እሑድ የዕለት ምግብ አጥተው ለሚራቡ ሰዎች የምግብ ፕሮግራም ዘርግተው መመገብ የዘወትር ተግባራቸው አድርገው ያዙት፡፡  የዓመት ልብስ ለሌላቸው የአውሮፓና የአሜሪካ ልባሾችን እየሰበሰቡ በነፃ በማደል እርቃናቸውን እንዲከልሉ አደረጉ፡፡ “ይህም የሆድ ነገር ሆድ ይቆርጣል” እንዲሉ ሆኖ፣የበርካታ ሰዎችን ኅሊና እንዲገዙ አስቻላቸው፡፡<br />
ነባሮቹ ሃይማኖቶች አማኙ የሚከተላቸው በመወለድ እንጂ፣በመማር ካለመሆኑም ሌላ፣ሃማኖቶቹ እንዲስፋፉ የሚያስችል የአደረጃጃት፣የሰው፣ የገንዘብና በዕወቀት ላይ የተመሠረተ የመረጃ ፍሰትና ልውውጥ አቅም የሌላቸው በመሆኑ ፣ከአዲስ ገቢዎቹ ሃማኖቶች ጋር ከታሪክ ርዝመት አንፃር ሲመዘን አቻ ለመሆነ ቀርቶ ለመከተል እንኳ እንዳልቻሉ ሁኔታዎች ያሳሉ፡፡<br />
የአዲስ ገብ ሃይማኖቶቹ መሠረታዊ ተልዕኮ  ሕዝቡ የኢትዮጵያዊነት ማንነቱ መገለጫ የሆኑ ዕሴቶቹን ቀስ በቀስ በፈቃዱ አውልቆ ጥሎ የአውሮፓዊ  ማንነትን ጥብቆ እንዲያጠልቅ በመሆኑ፣ባቋቋሙዋቸው ትምህርት ቤቶች የተማሩትንና ብሩኅ አዕምሮ ያላቸውን በስኮላር ሽፕ መልክ ወደ አውሮፓና አሜሪካ  በመላክ አውሮፓዊና አሜሪካዊ አስተሳሰብና አመለካከል አዳብረውና ይዘው እንዲመለሱና መልስው ወገናቸውን በነርሱ ሥር እንዲሰለፍ እንዲያደርጉ አደራጁዋቸው፡፡ ”እስ በሱ ሥጋን በኩበት ጠበሱ” እንዲሉ፣መልሰው የገዛ ወገኖቻቸውን የራሳቸውን ማንነት ትተው ሌላ ማንነትን እንዲላበሱ እንዲሰብኩና እንዲያስተምሩ አደረጉ፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ በከፈቱዋቸው የጤና ጣቢያዎች የቀጠሩዋቸውን ሰዎች ወደ ውጭ በመላክ ህክምናን ከሃይማኖት ዕውቀት ጋር አጣምረው የሚሠሩ ሰባኪና ሐኪሞችን በብዛት አሰለጠኑ፡፡  በዚህ የተጠናከረ ሂደት የደቡብ፣የምዕራብ፣የደቡብ ምዕራብና የመሀል ኢትዮጵያ ነዋሪ ነባር ሃይማኖቱን እየተዎ የአዲስ ገብ ሃይማኖቶች ተከታይ ሆነ፡፡  ይህም ያለጥርጥር ኢትጵያዊው ኅሊናውን ለቅኝ ተገዥነት ወዶ እንዲያመቻች እንዳደረገው መገንዘብ ይቻላል፡፡ የተግንጣይ ብሔርተኞች ድርጅቶች መሪዎች ተኮትኩተው ያደጉት በነዚህ የአዲስ ገብ ሃይማኖቶች ባቋቋሟቸው ትምህርት ቤቶች መሆኑን ልብ ስንል፣እነዚህ ሃይማኖቶች የቱን ያህል ሕዝቡን ለኅሊና ቅኝ ተገዥነት እንዳመቻቹት እንረዳለን፡፡<br />
4.	የኢትዮጵያ አብዮት ያስከተለው የኅሊና ስብራት፣<br />
ሚሽነሪዎቹ በቂ ተከታይ ማግኘታቸውን ካረጋገጡ በኋላ፣ሕዝቡ በኅሊና ቅኝ ተገዥነት ሥር ወዶና ፈቅዶ ለዘመናት መኖር የሚችለው የትኞቹን ተቋሞች ብናፈርስ ነው/ እንዚህን መዋቅሮችስ እንዴት እናፈርሳለን/ በሚል ጥናት ላይ ተሰማሩ፡፡ በዚህ ጥናታቸውም የኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት መሠረትና ምሰሶ የሆኑ ተቋሞችን ምንነት ለይተው በማወቅ ተቋሞቹ ሊፈርሱባቸው የሚችሉባቸውን መንገዶች የሚያሳዩ መጽሐፍትን በጥናትና ምርምር ስም ለዓለም አሰራጩ፡፡ የሃይማኖት ተከታዮቻቸውም እንዚህን በኢትዮጵያ መሠረታዊ ጠላቶች ማር ቀብተው  ያዘጋጁዋቸውን በርዞች  እንደ ደረቅ ሐቅ በመውሰድ ያላንዳች ማመዛዘንና አድሮ እየው ጥያቄ ዋጡዋቸው፡፡<br />
ሚሽነሪዎቹ ባደረጉት ጥናት የኢትዮጵያዊነት መሠረት የሆኑት ተቋሞች  “የሥልጣን ምንጭና የአንድነት ምልክት የሆነ ዘውዳዊ ሥርዓት፣የዘውዳዊ ሥርዓቱ ርዕዮተ-ዓለማዊ ክንድ የሆነ ኦርቶዶክስ ሃይማኖት እና ራሱን በቋንቋ ትስስር ያላደራጀ፣ በመሠረታዊ አደረጀደጀት ደረጃ በአጥቢያ ቤተ እምነቶች ዙሪያ  የሚደራጅ፤ከፍ ሲል በአስተዳደራዊ ክልሎቸ ማንነቱን የሚገልጥ፣በሠፊዋ ኢትዮጵያ በበቂ መጠን ተሰራጭቶ የሚኖርና በኢትዮጵያዊነት በጽኑ የሚያምን፣በተፈጥሮው ተዋጊና የአገር ዘብ የሆነ ዐማራ የተሰኘ ነገድ እንደሆኑ ተረዱ፡፡ ኢትዮጵያዊነት ብሔርተኝነትም ሲባል የዐማረው እንጂ፣የሌሎችን ነገዶች የሚጨምር አይለም፣ኢትዮጵያዊነት በሌሎች ላይ ዐማራው የጫነባቸው ዕዳ ነው ሲሉም ጨመሩበት፡፡” እነዚህ ተቋሞች ካልጠፉ ወይም በሕዝቡ ላይ የሚያሳድሩት ሁለንተናዊ ተፅዕኖ ካልተወገደ ኢትዮጵያን በውጭ ኃይሎች ሥር ለማዋል እንደማቻል  እርግጠኛ ሆኑ፡፡<br />
ተከታዩ ሥራቸው እንዚህን ተቋሞች እንዴት ማጥፋት ይቻላል? በሚለው ዙሪያ ወጥሮ መሥራት ነበር፡፡ ባደረጉት ጥረትም የነርሱን ዓላማ የሚጋሩ ብቻ ሳይሆን፣ብዙ ማይል ርቀው የኢትዮጵያን የብዙ ሺህ ዓመታት ታሪክ በመቶ ዓመት የገደቡ ብሔርተኛ ግለሰቦችንና በሚሽነሪ ትምህርት ቤቶች በፀረ ኢትዮጵያነት ተኮተረኩተው ያደጉ በርካታ ሰዎችን አገኙ፡፡ እንዚህን ግለሰቦች በተለያዩ መሰባሰቢያ መድረኮች ስም እንዲደራጁና የሰው ኃይል እንዲያሰባስቡ፤ፍላጎታቸውን በየጸሎት ቤቱና ባመቻቸው አጋጣሚ ሁሉ እንዲያሰራጩ አበረታቱ፡፡የኦነግ መሠረት የሆነው የሜጫና ቱሉማ ማኅበር የተመሠረተው በዚህ መልክ ሲሆን፣ የኦነግ መሪዎችም ወለጋ ጊንቢ አውራጃ ውስጥ በተከፈተ የካቶሊክ ሃይማኖት ተከታዮችና ተማሪዎች በነበሩ ግለሰቦች መሆኑን ስንገነዘብ የአዲስ ገብ ሃማኖቶች ተልዕኮ ምን እንደነበር በቅጡ ልንገነዘብ እንችልለን፡፡  የሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ድርጅት የተመሠረተውም በትግራይ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ማኅበር ስም እንደሆነ ይታወቃል፡፡የወያኔ መሥራቾችም በዐድዋ አውራጃ ተወላጆች መያዝ ፣ ዐድዋ ከተማ ውስጥ ከነበረ የሚሽነሪ ትምህርት ቤት ጋር በጥብቅ የተቆራኘ እንደነበር እንረዳለን፡፡  ከሁሉም በላይ መያዝ ያለበት መሠረታዊ ጉዳይ የብሔረሰብ ጥያቄ አንስተው የተደራጁ ብሔርተኛ ሰዎች የባንዳ ልጆች መሆናቸው ነው፡፡ሚሽነሪዎቹ በዚህ መልክ አደራጅተው ኢትዮጵያን ለመናድ በሚጥሩበት ወቅት ፣ የኢትዮጵያ ተማሪዎች  ከ1960ዎቹ መባቻ ጀምሮ ማርክሳዊ-ሌኒናዊ ርዕዮተዓለምን በተቀበሉ ቡድኖች አቀንቃኝነት የሚያራምዱት  የፍትሕና የዲሞክራሲ ጥያቄ ከፍተኛ ደረጃ ላይ የደረሰበት ጊዜ ነበር፡፡ በሁለቱ ወገኖች እንቅስቃሴ የሚፈልጉትን ሳያሟሉ ወይም ሳያገኙ ፣ የየካቲት 1966ዓ.ም  ሕዝባዊ አብዮት በድንገት በሕዝብ ብሶት ፈነዳ፡፡<br />
የሕዝቡን ቁጣና ብሶት መሠረታዊ ምክንያቶች በቅጡ ለይቶና አውቆ፣ ሕዝባዊው አብዮቱ በኢትዮጵያዊነት ማንነት ላይ መሠረቱን ጥሎ ወደ ፊት መጓዝ የሚችልበነትን መንገድ የሚያመቻችና የሚመራ ሕዝባዊ ኃይል በወሳኝነት መልኩ ሳይወጣ የፈነዳው አብዮት፣ቅኝ ገዥ ኃይሎቹ ባላሰቡትና ባልጠበቁት ፍጥነት የኢትዮጵያዊነት መገለጫ ፣ የአንድነትና የሥልጣን ምንጭ የነበረው ዘውዳዊ ሥርዓት በራሱ ዐወቅን ባይ ልጆች እንዲወድም ተደረገ፡፡ የቅኝ አገዛዝ ተልዕኮን አንግበው በሃይማኖት ስም ወደ አገራችን የገቡ ሰዎች የመጀመሪያ ዓላማ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተሳካለቸው፡፡ ተያይዞም የኢትዮጵያዊነት መሠረታዊ ተቋምና የዘውዳዊ ሥርዓቱ ርዕዮተ ዓለማዊ ክንድና የበርካታው  ሕዝብ መንፈሳዊ መሪ የነበረው የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት በመንግሥትና በሕዝብ ውስጥ የነበረውን ከፍተኛ ኃላፊነት አሳጣ፡፡ ቀሪው ተግባር እምብዛም አድካሚ የማይሆንባቸው የቁልቁለት መንገድ የሆነው፣ሌሎችን ብሔረሰቦች በዐማራው ላይ በጠላትነት ማስነሳትና እርስ በርሳቸው በማበጣበጥ የወል ዕሴቶቻቸውን በራሳቸው በማሳጣት፣ የቅኝ ገዥዎችን ማንነት እንዲላበሱ የማድረጉ ነው፡፡<br />
ለዚህ ተግባርም ትውልዱ ምቹ ሆኖ ቀረበላቸው፡፡ ከሁሉም በላይ ዐማራው ራሱን ለእርድ አመቻችቶ ቀረበ፡፡ ሌሎቹ በአዲስ ገብ ሃይማኖቶች ተኮትኩተው ያደጉ የሌሎች ነገድ አባል ልጆች ዐማራውን በጠላትነትና በቅኝ ገዥነት ፈርጀው እንደሚመለከቱትና ሊያጠፉት በዝግጅት ላይ ያሉ መሆናቸውን የዐማራው ቀለም ቀመስ ትውልድ አልተረዳም፡፡  ቀደም ሲል ኤርትራን ለመገንጠል የተደራጀው የጀብሃ እና የሻዕቢያ ቡድኖች ፀረ-ዐማራ መሆናቸውን ፈጽሞ የተገነዘበ አልነበረም፤ ይህ ብዥታ ዛሬም የጠራ አይደልም፡፡ በተመሳሳይ መልኩ ኦሮሞን እገነጥላለሁ የሚል ቡድን በመካከሉ ያቆጠቆጠ መሆኑን የዐማራው ነገድ ምሁራን ልብ አላሉም፡፡ ይህ ባለበት ሁኔታ ሕዝባዊ አብዮቱን ለመምራት በተነሳ የሥልጣን ጥያቄ ኢትዮጵያውያን አግባቢ መልስ ላይ ለመድረስ አልቻሉም፡፡ ሁሉ ባፈተተው ተጓዘ፡፡  በጉዞው በርካታ ፀረ-ዐማራና ፀረ- ኢትዮጵያ የሆኑ ድርጅቶች በቅኝ ገዥዎች ፍላጎት ላይ ተመሥርተው ተደራጁ፡፡ ነባሮቹ ጀብሓና ሻዕቢያ፣ሕወሓት፣ ኦነግ፣እስላሚያ ኦሮሞያ፣የኦጋዴን ነፃ አውጭ፣የአፋር፣የጉራጌ የከምባታ፣የወላይታ፣ የሲዳማ፣ ወዘተ እንደ አሸን ፈሉ፡፡ በሌላ በኩል ኅብረ-ብሔራው ድርጅቶች እንደ መኢሶን፣ኢሕአፓ፣ኢዲኅ፣ወዝሊግ፣አብዮታዊ ሰደድ፣ማሌሪድ፣ኢጭአት፣ የመሳሰሉት ተፈጠሩ፡፡ጉዞው  ግን ቀላል አልሆነም፡፡ ብዙ ሕይዎትን የጠየቀ፣ማንነትን በእጅጉ የሚፈታተን፣ መወለድን የሚያስጠላ ሆነ፡፡ በዚህ ጉዞው ውስጥም የውጭ ድጋፍ በማግኘት የበላይነትን እናገኛልን በሚል ስሌት ኢትዮጵያውያን ራሳችን ለኅሊና ቅኝ ተገዥነት አመቻቸን፡፡ የጉዞው ክፋት ያስከተለው ተስፋ መቁረጥ የናቅነውንና አባቶቻችን ድል ነስተው የመለሱትን ቅኝ ገዥ ኃይል ለምነንና ደጅ ጠንተን ቅኝ ተገዥ ለመሆን ስደትን እንድነመርጥ አደረገን፡፡ ይህ አጠቃላይ ሁኔታም ኢትዮጵያውያን ለኅሊና ቅኝ ተገዥነት እንድንዳረግ አድርጎናል፡፡<br />
በሌላ በኩል፣በአገሪቱ የተለያየ ዓላማና ግብ ይዘው፣በብሔርና በኅብረ-ብሔር ስም የተደራጁ የፖለቲካ ድርጅቶች የጠላትነት ደረጃውንና ስሙን ይለዋውጡት እንጂ፣ሁሉም የዐማራውን ነገድ “በገዥ መደብና በጨቋኝ  ብሔርነት” በመፈረጅ የጥፋት ክንዳቸውን አነሱበት፡፡ በነገዱ ላይ በእርዳ ተራዳ ከደረሰበት የኢኮኖሚና የፖለቲካ ጥቅምና መብት ነጠቃ በተጨማሪ፣በኢትዮጵያ ምድር ሠርቶ የመኖር መብቱን እንዲነጠቅ ሆነ፡፡ ስልታዊ በሆነ መንገድ በተከፈተበት የዘር ማጽዳት ዘመቻም ባለፉት የወያኔ አገዛዝ 2.4 ሚሊዮን ሕዝብ የደረሰበት አለመታወቁን የራሱ የወያኔ ሕዝብና ቤቶች ቆጠራ ባለሥልጣን ለሕዝብ ይፋ ማድረጉ ይታወቃል፡፡ ይህም ቅኝ ገዥዎች ኢትዮጵያን በፈለጉት መንገድ በቁጥጥራቸው ሥር ለማዋል እንቅፋት ሆነውብናል ያሏቸውን ተቋሞች “እሾህን በሾህ “ እንዲሉ ራሳችን፣እራሳችንን እንድናጠፋና የኅሊና ቅኝ ተገዥዎች እንድንሆን እንዳደረጉን እያየን ነው፡፡ በዚህ ራስን በራስ የማጥቃት ሂደት ውስጥ ከዐማራ ነገድ ውጭ ያሉ ምሁራን በዘር ተደራጅተው የዘራችን አውራ ጠላት ነው ብለው በፈረጁት የዐማራ ነገድ ላይ የጥፋት ክንዳቸውን ሲያነሱ፣የዐማራው ነገድ ምሁራን ራሱን አደራጅቶ ዘሩን ከጥፋት ለመከላከል ካለማሰቡም ሌላ፣የተለያዩ የፖለቲካ ድርጅቶች አባል በመሆን በራሱ ነገድ ላይ የጥፋቱ ተባባሪ ሆኖ ይታያል፡፡ ለአብነት ያህል በኅብረ ብሔራዊ ድርጅቶች ውስጥ ተደራጅተው የነበሩት የዐማራው ምሁራን የገዥ መደብ ነው ብለው በፈረጁት ዐማራ ላይ ያለፍርድ ሂደት አያሌ ዐማሮች ንብረታቸውንና ሕያዎታቸውን እንዲያጡ አድርገዋል፤ ተባብረዋል፡፡ ይህ ነው እንግዲህ “እስ በሱ ሥጋን በኩበት ጠበሱ” የሚያሰኘው፡፡<br />
5.	የኅሊና ቅኝ ተገዥነት የሚገልጽባቸው መልኮች፣<br />
 የቅኝ ገዥነት መሠረታዊ ግብ የቅኝ ተገዢውን ቋንቋ፣ባህል፣ሃይማኖት፣ማኅበራዊና ፖለቲካዊ ግንኙነት፣ተቋሞች፣አጠቃላይ ሁለንተናዊ ማንነትን ማስለወጥና የቅኝ ገዥውን ቋንቋ፣ባህል፣ሃይማኖት፣ማኅበራዊና ፖለቲካዊ ግንኙነት፣ተቋሞችና ማንነት መተካት ነው፡፡ይህም  በሁለት መልኩ ተግባራዊ እንደሚሆን የቅኝ አገዛዝ ታሪክ ያስተምረናል፡፡ እነዚህም አካል  እና  ኅሊናዊ ቅኝ ተገዥነት ናቸው፡፡ አካላዊ ቅኝ ተገዥነት ከአቅም በላይ በሆኑ አስገዳጅ ምክንያቶች፣ ቅኝ ተገዥ ወገኖች፣ በቅኝ ገዥው ኃይል ሁለንተናዊ ፍላጎት ቁጥጥር ሥር የሚውሉበት ሁኔታ ነው፡፡ አካላዊ ቅኝ ተገዥነት በእንስሳና በሰዎች መካከል ባለግንኙነት መመሰል ይቻላል፡፡ ቅኝ ተገዥው ለአገልጋይነት፣ቅኝ ገዥው ለተገልጋይነት የተፈጠሩ ዓይነት ሆነው የሚታዩበት ነው፡፡ ይህ ግንኙነት በውዴታ፣ወይም በተፈጥሮ ሕግ የተገዛ ባለመሆኑ፣ በቅኝ ተገዥው ኅሊና ውስጥ ምንጊዜም የማይጠፋ፣ጊዜና አጋጣሚን የሚጠብቅ የታመቀ አመጽ የቋጠረ ነው፡፡ አመጹ በራሱ ወይም በተከታዩ ትውልድ ለመቀስቀስ የሚያስችልና ለተቀሰቀሰው አመጽም የሞራል፣ የተፈጥሮና የሰው ሠራሽ ሕግ  ጊዜ የማይሽረው ድጋፍ ያለው ነው፡፡ ስለሆነም አካላዊ ቅኝ ተገዥነት የሁለንተናዊ አቅም ማጣት ወይም ማነስ የሚያስከትለው በመሆኑ ቅኝ ተገዥው ማንነቱን ከውስጡ አያጠፋም፡፡ የእርሱነቱ መገለጫዎችን በልዩ ልዩ ዘዴዎች ለትውልዱ ያስተላልፋል፤በሚስጢር ይጠብቃል፡፡ የቅኝ ገዥዎች የሆኑ ማናቸውንም ነገሮች በውስጡ ይጠላቸዋል፤ይጠየፋቸዋል፤ይንቃቸዋል፡፡<br />
ለምሳሌ ሕንዶች ከመቶ አምሳ ዓመታት ያላነሰ በእንግሊዞች ተገዝተዋል፡፡ ባህላቸውን፣ቋንቋቸውን፣እምነታቸውን እንዲለውጡ አያሌ ማስገደጃዎች ጭነውባቸው እንደነበርም ይታወቃል፡፡ ሆኖም፣ ሕንዶች የተጣለባቸውን ጫና ተቋቁመው፣ባሕላቸውን፣ቋንቋቸውንና ሃይማኖታቸውን አስጠብቀው ለነፃነት በቅተዋል፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ እስራኤላውያን ከሁለት ሺህ ዓመታት በላይ በኃይል አገራቸውን ተገደው በዓለም አገሮች እንደጨው ተዘርው ሲኖሩ፣ ቋንቋቸውንና ሃይማኖታቸውን በሰው አገር አሰጠብቀው አገር ለመመሥረት ችለዋል፡፡ በሌሎች በቅኝ ግዛት ቀንበር ሥር የነበሩ አገሮችም የምናየው ተመሳሳይ ነው፡፡ከዚህ ላይ ማስተዋል ያለብን መሠረታዊ ጉዳይ የትኛውም ዓይነት ቅኝ አገዛዝ ግቡ አድርጎ የሚንቀሳቀሰው፣ የቅኝ ተገዥዎችን ባህል፣ሃይማኖት፣ቋንቋ፣ታሪክና አጠቃላይ ማንነትን አስጥሎ፣ የቅኝ ገዥውን ሁለንተናዊ ማንነት እንዲላበስ ማድረግ መሆኑን ነው፡፡<br />
በአንፃሩ ኅላናዊ ቅኝ ተገዥነት በተለያዩ ምክንያቶች ሰዎች በቡድን ወይም በተናጠል የራሳቸውን ማንነት በገዛ ፈቃዳቸው በመተው የሌሎችን ማንነት መላበስ ነው፡፡ የኅሊና ቅኝ ተገዥነት ራስን በራስ ሰቅሎ በመግደል ይመሰላል፡፡ ራሱን ሰቅሎ የሞተሰው በክርስቲያን ሃይማኖት ፍታት አይፈታም፤ ነፍሱም እንደማትማር የሃይማኖቱ ሕግ ያስተምራል፡፡ ይህም ማለት ራስን በራስ መስቀል የሞራል፣ የተፈጥሮና የሰው ሠራሽ ሕጎች ድጋፍ የለውም ማለት ነው፡፡ በተመሣሣይ መልኩ፣ራሱን ወዶ ለቅኝ ተገዥነት ያቀረበና የተገዛ ሰው በውስጡ በራሱ ቁጭት የለውም፤  ወዶ ውርደትን የተቀበለ በመሆኑ፣ውርደቱ አይሰማውም፣ባለመሰማቱም ነፃ ለመውጣት አያስብም፤ ቢያስብም  የሞራል፣የሰው ሠራሽና የተፈጥሮ ሕጎች ድጋፍ አይኖረውም፡፡ የሚገፋፋው ውስጣዊ ምክንያት የሌለው በመሆኑም፤ለተከታዩ ትውልድ የሚያቀብለው ነገር ስለሌለው ትውልዱ የወላጆቹን ይዞ እንዲቀጥል ይገደዳል፡፡ ስለሆነም የኅሊና ቅኝ ተገዥነት ከአካላዊ ቅኝ ተገዥነት እጅግ የከፋ ነው፡፡ የከፋ የሚሆነው ወዶ የተቀበለው በመሆኑ፣መውጫ ቀዳዳ የሌለው መሆኑና ቅኝ የተገዛላቸው ፣ቅኝ በመገዛቱ የሚንቁት እንጂ፣የሚያከብሩት አለመሆኑን አለመገንዘቡ ነው፡፡ በጽንሰ ሀሳብ ደረጃ የአካላዊና የኅሊናዊ ቅኝ ተገዥነት ምንነት በመጠኑም ካየን፣ኅሊናዊ ቅኝ ተገዥነት የሚገለጥባቸው መልኮች ምን እንደሆኑ ማየቱ፣የኅሊናን ቅኝ ተገዥነት በተጨባጭ በእኛ ሁኔታ ለማየት ያስችለናል፡፡<br />
ኅሊናዊ ቅኝ ተገዥነት በሚከተሉት መልኮች ራሱን ይገልጻል፡፡<br />
(1)	በባህል፣ (2) በስም፣ (3) በቋንቋ፣ (4) አገርን በመጥላት፣ (5) በስደት፣<br />
1.	ባህል፡- ባህል የሰው ልጅ  በማምረት፣በማከፋፈልና በመጠቀም ሂደት ውስጥ፣ ሰዎች ከሰዎች እና ሰዎች ከተፈጥሮ ጋር በሚፈጥሩት መስተጋብር ተገቢና ትክክል ነው ብለው በተደጋጋሚ በግልና በቡድን የሚፈጽሙት ተግባር ነው፡፡ አመራረት፣አመጋገብ፣በዐላት አከባበር፣ሰላምታ አሰጣጥ፣አለባበስ፣ደስታና መከራ የሚገለጽባቸው መንገዶች( ዘዴዎች) ፣የጋብቻ ሥርዓት፣ ምግብ አዘገጃጀት፣የአመጋገብ ሥርዓት፣ወዘት ባህል የሚገለጽባቸው ናቸው፡፡  </p>
<p>ከነዚህ የባህል መከሰቻ መልኮች ውስጥ ኢትዮጵያውያን ብዙም ያለወጥነውና አጥብቀን የያዝነው የምግብ አዘገጃጀታችን፣ አመጋገባችንና ሃይማኖታዊ የበዐል አከባበር ሥርዐታችን ነው፡፡ አለባበሳችን በአብዛኛው የምዕራባዊው አለባበስ  ባህል የተጫነው ነው ፡፡ ካባ፣በርኖስ፣ተነፋነፍ፣ባት ተሁለትና ወንጨሬ ሱሪዎች፣ጋቢ፣አግድሞሽ፣ኩታና ነጠላ ፣ዙሪያ ገብ እና ኋላ ግማሽ እዳይት ቀሚስና ጎዳ፣ጀበርባሬ ኩታ፣ባለጃኖ ጋቢ ወዘት ለወግ በተወሰኑ ሰዎች ካልሆነ ሕዝቡ የኔ ብሎ የያዛቸው አለባበሶች ከሆኑ ዘመን አስቆጥረዋል፡፡ በገና እና በትንሣዔ በአሎች ይደረጉ የነበሩ የአማትና የአማች መገናኛ ዝግጅቶችና በውስጡ ይከናወኑ የነበሩ ሥርዐቶች ፈጽሞ ተረስተዋል፡፡<br />
በገና የክስቶስን መወለድ የደስታ ስሜት መግለጫ በወጣቶች መካከል ይደረግ የነበረ የገና ጨዋታ፣ ዛሬ  እንኳን ስለጨዋታው ፣ስለመኖሩም የሚያውቁ  መኖራቸውም አጠራጣሪ ነው፡፡ እንደ ዳቢሎስ ተመስሎ በገና ሰሞን በአዋቂዎችና በጎልማሶች ይጨወት የነበረ “ኃይሚሎ” የተሰኘ የጉግስ ጨዋታ ከተረሳ ዘመን የለውም፡፡ በዚሁ ሰሞን ይዘወተር የነበረው የፈረስ ጉግስ ጨዋታ ከጠፋ ዘመናት ተቆጥረዋል፡፡<br />
በፍልሰታ ታዳጊ ወጣቶች ተሰባስበው ሆያ ሆየ እያሉ እየዘፈኑ በሚሰበስቡት ገንዘብና እህል የመስቀል ዕለት ደግሰው የአካባቢውን ሰው የሚመግቡበት፣ ከኅብረተሰቡ ይቸራቸው የነበረ የእደጉ ተመንደጉ ምርቃት፣ ደመራው ከተቃጠለ በኋላ፣በፍሙ በስሎ የሚበላው እርምጦ ዛሬ የለም፡፡ ሴት ወጣቶች በቋግሜ ሳምንት አሸንድየ ታጥቀው፣ አሻንድዬ አበባዬ እያሉ ወቅትን መሠረት አድርጎ ይጨወት የነበር የጨዋታ ባህል ዛሬ በድሮው መልኩ በስፋት አይታይም፡፡ እነዚህና የመሳሰሉት አንዳንዶቹ በምዕራባውያኑ ሲተኩ ሌሎቹ በልዩ ልዩ ምክንያቶች ከሕዝቡ አእምሮ ውስጥ ተሰርዘዋል፡፡ ገና ጨዋታ በእግር ኳስ የተተካ ይመስላል፡፡ ኃይሚሎ፣ጦር ውርወራ ለኢትዮጵያውያን አዲስም እንግዳም ባይሆንም፣ በዳርትና በጦር ውርወራ የተተካ ይመስላል፡፡ የአማትና የአማች ግንኙነት ሌላ መልክ ይዟል፡፡ አማት ፣ምራት፣አይት፣አማች፣አገቡኝ፣ ዋርሳ የሚሉት ቃላት ራሳቸው በአማትና በአማች ግንኙነት መላላት የተነሳ ትርጉማቸው ከማይታወቅበት ደረጃ ተደርሷል፡፡ የምዕራባውያኑ ግንኙነት የበላይነቱን በመያዙ የእኛ ማንነት መገለጫ ተረሳ፤ ወይም ተጣለ፡፡ የጋብቻ ሥርዓታችን በእጅጉ ተለውጧል፡፡ በለቅሶ ጊዜ እንደ ሟቹ ማንነት ይደረጉ የነበሩ ፉከራዎችና ቀረርቶዎች ዛሬ አይደመጡም፡፡ ይህም ኅሊና  የራሱን እየተወ የሌሎችን እየያዘ መምጣቱን አመልካች ነው ፡፡ የኅሊና ቅኝ ተገዥነት የሚባለው ይኸነው፡፡<br />
2.	ስም፡- ስም መጠሪያ ፣መታወቂያ ነው፡፡ እያንዳንዱ ነገር ከሌላው የሚለይበት የወል፣የጥቅልና የተጸውዖ ስሞች አሉት፡፡ ስሞችም የሚወጡት በዘፈቀደ ሳይሆን፣ ስም አውጨዎቹ በኖሩበት ማኅበረሰብ ባህል፣ቋንቋና እምነት ጋር ተያይዞ የሚሰጥ ነው፡፡( ከዚህ ላይ ስም ስንል ልዩ ትኩረት የምንሰጠው የሰው መሆኑን እናስተውል፡፡) ስለሆነም የአንድ ሰው ስም በወላጆቹ ፈቃድና ውሳኔ የሚሰጥ ነው፡፡ ውሳኔው መሠረት የሚያደርገውም ከፍ ሲል እንደተጠቀሰው ባህልን፣እምነትንና ስም የሚወጣለት ሰው በተወለደበት ወቅት በአካባቢው በተፈጠሩ ሁኔታዎች ላይ ተመርኮዞ ነው፡፡ በዚህ መሠረት ከዐማራ ነገድ የተወለደ ወይም የተወለደች ሰው፣አበበ፣አበበች፣ላቀው፣ላቀች፣በላቸው፣በላይነሽ፣አስፋው-ወሰን፣ወሰን-የለሽ፣ ወርቁ፣ወርቂቱ (ወርቅነሽ)፣በላቸው ፣በላይነሽ፣አግርደው፣አግርጅው፣አስካበ፣አስካበች፣ፀጋው፣ፀጋነሽ፣ ብሬ፣ ብሪቱ፣ ወዘተ እያሉ ስም ይሰጧቸዋል፡፡ በአንዳንድ አካባቢዎች የሚወጡ ስሞች የአባትየውን ፍላጎት በሚገልጥ መልኩ፣የልጅና የአባት ስም ባንድነት ሲጠሩ የተለየ ትርጉም በሚሰጥ መልኩ ይሰይሟቸዋል፡፡ ለምሳሌ፣ ሰውበሰው ደረጀ፣ መጥምቁ ዮሐንስ፣ ቅዱስ ዮሐንስ፣ቁምነገር ገበየሁ፣በዓለምላይ ገበየሁ፣ኃይለሥላሴ ቀለጠ፣ ወገን በለጠ፣ አማላጅ በለጠ፣ወዘተ፣ እነዚህ ስሞች የኢትዮጵያዊነት<br />
በተለይም የዐማራ ነገድ ማንነት መገለጫዎች እንደሆኑ በቀጥታ ከስማቸው መረዳት ይቻላል፡፡</p>
<p>ይሁን እንጂ ቀለም ቀመሱ ትውልድ በተለያዩ ምክንያቶች ማለትም፣ አዲስ ሃይማኖት በመቀበል፣የስም አጠራሩን ለውጭ አገር ሰዎች  በቀላሉ አይገባም በሚሉና በመሳሰሉ ምክንያቶች በቤተሰብ የተሰጣቸውን ስም ሆነ እነርሱ ለወለዷቸው ልጆች ኢትዮጵያዊ ያልሆኑ ስሞች ሲሰጡ መታየቱ እግዳ ነገር አይደለም፡፡ ሊያ፣ሚኩ፣ሚሚ፣ሣራ፣ማይክ፣አቤነዘር፣ሌላም ሌላም ሕዝቡ የሚያውቃቸው ከኢትዮጵያዊነት ጋር ምንም ዓይነት ግንኑነት የሌላቸው ስሞች እንሰማልን፤እናውቃለን፡፡ ይህ የራስን ዕንቁ ወርውሮ የሌሎችን ነሃስ መሰብሰብ ከመሆኑም በላይ፣ ራስን ለኅሊናዊ ቅኝ ተገዥነትን ወዶ ማሰለፍ ነው፡፡ ሌሎቹን ሁሉ ለትዝብት ትተን ሣራ የሚለውን ስም እንደኛ(እንደ ኢትዮጵያዊ) ሆነን እንሰብ፡፡ </p>
<p>ማንም መጽሐፍ ቅዱስን የሚከታተል ሰው ሣራ የሚለው ስም እንግዳ ነገር አይሆንበትም፡፡ “የአባታችን” የአብርሃም ባለቤት መሆኑዋን ይረዳል፡፡ ይህ ስም በእበራይስጥ ቋንቋ ትርጉሙ “እናት” እንደማለት ይመስለኛል፡፡ የእብራይስጥን ቋንቋና ባህል ለሚያውቅ ሰውና በዚያ ባህል ለኖረ ስሙ ወርቅ ነው፡፡ የኢትዮጵያዊ ባህልና ቋንቋ ባለቤት ለሆነ ሰው ደግሞ ይህ ስም እንኳን የልጅ መጠሪያ ሊያደርጉት ሊናገሩት የሚከብድ ትርጉም ያለው ነው፡፡ እግዚአብሔር ያሳያችሁ! “ሣራ ነጋ” ብሎ ስም የሚያወጣ ሰው ለልጁ መጠሪያ ሳይሆን መሰደቢያ ነው የሰጣት፡፡  የቋንቋው ሥርዓትና የሕዝቡ ባሕል ከሚፈቅዱት ውጭ የተሰጡ ስሞች የኅሊና ቅኝ ተገዥነት ስሜት የፈጠራቸው ስሞች መሆናቸውን መጠራጠር አይቻልም፡፡ በዚህ ረገድ ኢትዮጵያዊው በተለይም ዐማራው ማንነቱን ፈቅዶና ወዶ እያወለቀ እየጣለ የሌሎችን ማንነት እያጠለቀ መሆኑ ጉልሁ ማመላከቻ ለልጆቹ የሚያወጣላቸው ስሞች ናቸው፡፡</p>
<p>በአማርኛ ቋንቋ ሥርዓት ውስጥ በተጸውዖ ስም ላይ እየተደረቡ የሚገቡ ለሁለቱም ፆታዎች የሚያገለግሉ ድርብ ስሞች እንዳሉ ይታወቃል፡፡ እነዚህ ድርብ ስሞች የማዕረግ፣የአክብሮትና የተዘምዶ ስሞች ይባላሉ፡፡ የማዕረግ ስሞች በቤተ እምነቶች ወይም በቤተ መንግሥት የሚሰጡ ናቸው፡፡ ምሳሌ፡- ቤተእምነት፣ እጨጌ፣ጳጳስ፣ቆጶስ፣መላዕ-ከፀሐይ፣ግራ ጌታ፣ ሸህ፤ወዘተ፣፣ ቤተ መንግሥት፣አጼ፣እቴጌ፣ንጉሥ፣ራስ፣ቢትወደድ፣ደጃዝማች፣ፊታውራሪ፣ቀኛዝማች፣ግራዝማች፣ብላታ፤ እነዚህ ስሞች ግለሰቦች ለአገራቸው ባበረከቱት ተግባር፣ባሳዩት አርዓያነት ያለው ሥራ ጉዳዩ በሚመለከታቸው አካለት ተመርምሮ የሚሰጡ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ስሞቹ የክብር መጠሪያዎች በመሆናቸው ሌሎች የዚያ ስም ባለቤት ለመሆን የተሻለ ተግባር እንዲፈጽሙ አነቃቂ እንደነበሩ ግልጽ ነው፡፡ በመንግሥት ደረጃ የሚሰጡት የማዕረግ ስሞች በአብዛኛው አገርን ከጠላት በመከላከል ሂደት ውስጥ በተጫወቱት ሚናና በሰላም ጊዜም በአስተዳደር፣ በልማትና መሰል ተግባሮች አርኣያነት ያለው ተግባር ለተወጡ ግለሰቦች ነው፡፡ የቤተ እምነቶቹ ስሞች የሚሰጡት በሃይማኖቱ መንፈሳዊ ዕውቀት ላይ ተመሥርቶ በዚያ ተግባር ላይ ያበረከቱት አስተዋጽዖ ተመዝኖ እንደሆነ ይታወቃል፡፡</p>
<p>ዛሬ በምንገኝበት ነባራዊ ሁኔታ የቤተ እምነቶቹ ስሞች በአገልግሎት ላይ ሲገኙ፣ ከመንግሥት በኩል የሚሰጡት ስሞች እንደ አድኃሪና ኋላ ቀር ነገር ተቆጥረው ተወግዘው የተወረወሩ ሆነዋል፡፡ ማዕረግተኞቹም በማረጋቸው ያፈሩ ይመስላል፣ ሊጠሩበት አይሹም፡፡ ለምሳሌ ልዑል ራስ መንገሻ ሥዩም  ከዚህ ስማቸው ይልቅ  “ታጋይ” የሚለው እንደሚመቻቸው ሲናገሩ የተደመጠበት ጊዜ አለ፡፡ “ታጋይ” መንገሻን ለዚህ ያበቃቸው የማዕረግ ስሙን ያገኙት በግል ባስመዘገቡት የመልካም አርኣያነት ተግባር ሳይሆን፣ከንጉሡ ጋር በመጋባታቸውና ከአጼ ዮሐንስም እወለዳለሁ ስለሚሉ፣በነዚህ ሁለት ምክንያቶች ያገኙት በመሆኑ ለስሙ ክብደት ከመስጠት ይልቅ አሳፍሯቸዋል ማለት ነው፡፡ በሌላ በኩል ግራዘመም አመለካከት አቀንቃኝ የሆነው ትውልድ ማዕረጎቹን የተረዳበት አቅጣጫ ከኢትዮጵያዊነት መንፈስ ባፈነገጠ መልኩ መሆኑ መዕረጎቹ የገዥና የተገዥ፣የአዛዥና የታዣዥ፣ የሀብታምና የድሀ ግንኙነት መገላጫዎች አድርጎ በመመልከቱ ትውልዱ ስሞቹን በጭፍን አወገዛቸው፡፡ ማዕረግተኞቹም አብዛኛዎቹ በአብዮቱ በግራ ቀኙ ኃይሎች ተመቱ፡፡ የቀሩትም እንደ ራስ መንገሻ ያሉት ዘመኑን ለመምሰል ሌላ ዘመነኛ ስም መረጡ፡፡ ትውልዱ ኅሊናው በቅኝ ተገዥነት ስሜት ሳያወቀው ባይገዛ ኖሮ፣ስሞቹ  በልዩ ልዩ መስኮች አርኣያነት ያለው ተግባር ላከናወኑ ሰዎች መጠሪያ እንዲሆን  ይፈቅድ ነበር፡፡ይህም ኢትዮጵያዊነትን ማድመቅ እንጂ ማፍዘዝ አይሆንም ነበር፡፡ እንግሊዞች ንጉሣዊ አመራርን  አሻሻሉት፣ሕዝቡ በሚፈልገው ደረጃ አሳደጉት እንጂ፣ፈጽሞ አላወደሙትም፡፡ በዚህም የተነሳ “ሰር” የሚለውን የማዕረግ ስም ዛሬም በልዩ ልዩ መስኮች ለሰው ልጅ ጠቃሚ ሥራዎችን ለሠሩ ሰዎች መጠሪያና መከበሪያ እንዲሆን እያደረጉት ይገኛል፡፡ ኢትዮጵያውያን ግን የራስን ማጥፋት፣የራስ ያልሆነን መካብና ማድመቅ በመሆኑ ሥራችን፣ እነዚህን አገራችን ከረጅም ጊዜ ጀምሮ ስትገለገልባቸው የነበሩ የማዕረግ ስሞች እንዲጠፉ ፈርደንባቸዋል፡፡ ይህም ውጭ አምላኪነት ነው፡፡ ውጭ አምላኪነት ደግሞ ፈቅዶና ወዶ ቅኝ ተገዥነትን መለማመድ ነው፡፡</p>
<p> የተዘምዶ ስሞች የምንላቸው ልጆች ለወላጆቻቸው፣ታናናሾች ለታላላቅ ወንድሞቻቸውና እህቶቻቸው የሚሰጡዋቸው እንዲሁም በዕድሜ ታናሽ የሆኑ ሰዎች ታላላቆቻቸውን የሚጠሩባቸው ስሞች ናቸው፡፡ ይህም በመሆኑ ልጆች ወላጆቻቸውን አባባ፣አባበይ፣ እማማ፣ እማመይ፣ታላላቆቻቸውን አይወይ፣ክንዴ፣ጋሻዬ፣መከታዬ፣ወንድም-ዓለም፣እዋዋ፣ወንድም-ጥላ፣ወንድም-ጋሼ፣ እታበባ፣እታለም፣እትሸት፣እንጎቻዬ፣እባባ እገሌ፣ጋሼ እገሌ ፣አይዋ እገሌ፣እማማ እገሊት፣እታታ እገሊት ወዘተ እያሉ መጥራት የቋንቋው ሥርዓትም ሆነ የሕዝቡ መልካም ባህል ነበር፡፡ በሌላም በኩል ወንዶች ለአቅመ አዳም፣ሴቶች ለአቅመ ሔዋን ከደረሱ በኋላ የሚጠሩበት የማዕረግ ስም አላቸው፡፡ ወንዶች “አቶ” ሲባሉ ሴቶች “ወይዘሮ” ላገባች፣ “ወይዘሪት” ላላገባች እያሉ መጠራት እንዳለባቸው ባህሉና ሥርዓቱ ያዛል፡፡ </p>
<p>እነዚህ  ስሞች ከማዕረግ መገለጫቸው በተጨማሪ በጠሪውና በተጠሪው በካከል እጅግ የቀረበ የሥጋ ዝምድና  ያላቸው መሆኑን ከማመልከቱም በላይ፣ ባለማዕረግ ስሙ ታላቅ፣ በማዕረግ ስም ጠሪው ታናሽ መሆናቸውን ላድማጭ ግልጽ በሆነ መንገድ ያስረዳሉ፡፡ ከዝምድና መገለጫ ውጭ ያሉት የአክብሮት ስሞች  በአክብሮት ስም ጠሪው በዕድሜ ታናሽ፣ ተጠሪው ታላቅ መሆኑን ያስረዳሉ፡፡ ይህ እንዴት ያለ የኢትዮጵያዊነት ልዩና ውብ መታወቂያ ነበር፡፡ ዳሩ ምንያደርጋል/ እነዚህ እንኳን ውጪ ተወልደው ባደጉ፣ በአገር ቤት በተወለዱትና ባደጉት ከ1950ዎቹ መጨረሻ ጀምሮ በተወለደው ትውልድ ያላዳች አስገዳች ውጫዊ ኃይል በራስ ፍጹም ፈቃድ ስሞቹን ከአገልግሎት ውጭ እንዲሆኑ ተድርጓል፡፡ አባትና እናትን እንደ ጓደኛ በስማቸው መጥራት እንደስልጣኔ ተቆጥሯል፡፡ አለያም እንደምዕራባዊኑ “ዳድ” ፣”ማም” ማለት የተዘወተረ ሆኗል፡፡ የኅሊና ቅኝ ተገዥነት ማለት ሌላ ምንም ሳይሆን፣የራስን ጥሩ ነገር ትቶ የሌሎችን ባህል፤እምነትና ማንነትን መላበስ ነው፡፡ ወላጆቹን በባህላችን የአክብሮት ስሞች የማይጠራ፣ታላላቅ ወንድሞቹንና እህቶቹን በኢትዮጵያዊ የአክብሮት ስም የማይጠራ ከማንነቱ የተፋታ ነው፡፡ ተጠሪዎችም በባህላችን የሚመጥናቸውን የማዕረግ ስም ነጥለው የሚጠሩዋቸውን ልጆቻቸውንም ሆነ ወንድም እህቶቻቸውን አዎንታዊ መልስ ከሰጡ የመጀመሪያዎቹ ባህል ጣሾችና ሥርዓት አፍራሾች መሆናቸውን ሊረዱት ይገባል፡፡ ለሁሉም ቀለም ቀመሱ ትውልድ ከኢትዮጵያዊነት ጨዋነት፣ባህልና ማንነት ራሱን እያፋታ የመጣ መሆኑ ባህላችን የሚገኝበት ሁኔታ ቁልጭ አድርጎ ያሳያል፡፡ ይህ ደግሞ የኅሊናዊ ቅኝ ተገዝነት መገለጫ ነው፡፡</p>
<p>3. ቋንቋ፡- ቋንቋ መግባቢያ፣ሀሳብ መግለጫና መለዋወጫ የሆነ የድምፅ ሥርዓት ነው፡፡ ይህም በመሆኑ የተለያዩ ሕዝቦች የተለያዩ የድምፅ ሥርዓት የሚከተሉ ቋንቋዎች አሏቸው፡፡ ቋንቋ አዳጊም ጠፊም ነው፡፡ ቋንቋ የሚጠፋው በሥራ ላይ የሚያውለው ማኅበረሰብ በልዩ ልዩ ምክንያቶች አልገለገልበት ሲል ነው፡፡ ቋንቋ ዳባሪ የሚሆነውም የቋንቋው ባለቤት የሆነው ሕዝብ የኢኮኖሚ ደረጃ ማደግና ከሌሎች ሕዝቦች ጋር የሚፈመሠርተው ግንኙነት ሲሠፋ ነው፡፡ በዚህ ዓይነት በዓለማችን ላይ የጠፉ ቋንቋዎች የመኖራቸውን ያህል፣የዳበሩም እንዳሉም እንረዳለን፡፡ ዳበሩ ከምንላቸው ቋንቋዎች ውስጥ እንግሊዝኛ የመጀመሪያውን ደረጃ የያዘ ነው፡፡  ጠፉ ከሚባሉት ውስጥ ላቲን አንዱ ነው፡፡በአገራችን ከጠፉ ቋንቋዎች ውስጥ ጋፋትኛ የመጀመሪያው ነው ፡፡ አንፃራዊ በሆነ መልኩ አድጓል ወይም ዳብሯል ከሚባሉት ውስጥ አማርኛ አንዱ ነው፡፡ </p>
<p>አማርኛ ቋንቋ አድጓል ስንል በሚጠበቅበት ደረጃ እያደገነው ወይም አድጓል ማለት እንዳልሆነ መታወቅ አለበት፡፡ ቋንቋው በጽሑፍ ሥራ ላይ ከዋለ ከ320 ዓ.ም ጀምሮ ካስቆጠረው ዘመን አንፃር ሲመዘን ወደ ኋላ እንጂ፣ወደ ፊት ሄደ የሚባል አይደለም፡፡ ይኸም ሆኖ፣ትውልዱ በተጠናወተው ኅሊናዊ ቅኝ ተገዥነት ስሜት ሳቢያ፣ አባቶቻችን ባቆዩልን መልኩ እንኳ ለልጆቻችን ለማስረከብ ከማንችልበት ደረጃ ላይ ነን፡፡ ቋንቋ ባህል በመሆኑ የሚከተላቸው የራሱ የሆኑ መንገዶችና  ሥርዓቶች አሉት፡፡ ለምሳሌ በአማርኛ ቋንቋ ሰዎች ሰላምታ ሲለዋወጡ የሚከተሉት ሥርዓት አለ፡፡ ሰላምት ሰጪው  ጤና ይስጥልኝ እንዴት አደራችሁ?  ዋላች?  አመሻችሁ ፣ሲል፣ ሰላምታ ተቀባዩ  ወይም መላሹ እግዚአብሔር ይመስገን ደህና ነኝ ፣ደህና ነን ሲል መመለስ እንዳለበት ይታወቃል፡፡ ይህ በዛሬው ትውልድ እንደነውር የሚቆጠር ሆኖ፣የሰላምታው ዘይቤ የምዕራባውያኑን መንገድ ተከትሏል፡፡ እዴት አደርክ?  አደራችሁ ሲባል መልሱ ደህና ወይም መልሶ እንዴት አደርክ የሚል ነው ፡፡ ይህ የራስን ውብ ነገር መጣል ነው፡፡ በንግግር ወቅት በአማርኛ ጀምሮ በአማርኛ መጨረስ የሚታሰብ አልሆነም፡፡ በመሀሉ እንግሊዝኛ፣ፈረንሣይኛ፣ዐረብኛ፣ ወዘተ ጣልቃ ማግባት የዐዋቂነት ምልክት እንደሆነ መቆጠር ከጀመረ ሰነባብቷል፡፡ በሌላም በኩል የአማርኛ  እናት ግዕዝ መሆኑ እየታወቀ ግዕዝን እንድንማር ባለመደረጉ፣እኛም ራሳችን ለማስተማርና ለመማር ባለመትጋታችን ዘመኑ ለሚፈጥራቸው አዳዲስ የቴክኖሎጂ ውጤቶች መጠሪያ የሚሆኑ ቃሎች ከአማርኛ ስናጣ፣አማርኛን መውቀስና የውጭ ቋንቋዎችን ማግነን የራስን ካለማወቅ የተፈጠረን ችግር፣የቋንቋው ችግር አድርጎ ማቅረብ የራስን ከመናቅ የመነጨ ውጭ አደርነት ስሜት የፈጠረው መሆኑን መጠራጠር አይቻልም፡፡ </p>
<p>ትውልዱ ግራ ዘመም ርዕዮት በመከተሉ ሳቢያ፣የተለያዩ ግንኙነቶች መገለጫ የሆኑ ስያሜዎቸን “ ገዥ መደቦች ወይም ብሔረሰቦች” እንዳዎጡዋቸው በመቁጠር ከንግግር ዘይቤ ውጭ እንዲሆኑ ሆኗል፡፡ ምሳሌ “አዝማሪ”፤ ይህ ቃል ትርጉሙ አዘመረ አመሰገነ የሚል ሲሆን፣ትርጉሙን በሚገባ ካለማወቅ የሙያ ማንቋሸሻ እንደሆነ ተቆጥሮ “ አርቲስት” በሚል የውጭ ቃል እንዲተካ ተደርጓ፡፡በምዕራቡ አገር ጢሰኛ፣ገባር የሚሉት ቃሎች ለልዩ ልዩ አገልግሎቶች የሚውሉ ቤቶችን ፣መሬቶችን የሚከራዩ ሰዎች የሚጠሩበት የተከራይና አከራይ ግንኙነት መገለጫዎች በመሆን በሥራ ላይ ውለው እናያለን፡፡ እነዚህ ቃሎች በኢትዮጵያችን የጭቆና መገለጫዎች እንደሆኑ ተቆጥረው ከአገልግሎት ውጭ እንዲሆኑ ተደርጓል፡፡ በዚህ መሰል ሌሎችም እንዳሉ ግልጽ ነው፡፡ በሌላ በኩል ቋንቋው እንዳያድግ ፍላጎት ባላቸው ክፍሎች  ስልታዊ በሆነ መንገድ የአማርኛ ቋንቋ እንዲጠፋ የሚሠራው የቤት ሥራ ቀላል አይደለም፡፡ ዛሬ ወያኔ በዘረጋው የትምህርት ፖሊሲ በተዘጋጁ የማስተማሪያ መጽሐፍቶች ፊደሎች ካለቦታቸው ከመግባታቸው በላይ ፣ቃሎቹን በሚገባ የሚገልጹ የግዕዝና የአመርኛ ቃሎች እያሉ ሆን ተብሎ እንግሊዝኛ  ወይም ትግርኛ ቃሎች ከአማርኛ ጋር እንዲዳቀሉ ተደርጓል፡፡ </p>
<p>አባቶቻችን ስድስት ሀ፣ሃ፣ ሐ፣ሓ ፣ኀ ፣ኃ፣ሁለት  ሰ ፣  ሠ   ፣ሁለት ጸ፣  ፀ ፣አራት አ፣ኣ፣ ዐ፣ዓ ፣ ፊደሎች ድምፅ የቀረጹት የተለያየ ድምፅና ትርጉም ያላቸው መሆኑን በመገንዘብ ነው፡፡ ለምሳሌ  ሀብት፣ሃብት፣ ሐብት፣ሓብት፣ኀብት፣ኃብት ተብለው በተገቢው ድምፅ የተገለጠውን ምረጥ ብንባል ትክክለኛው መልስ በሀሌታው “ሀ” የተጻፈው ነው፡፡ የቀሩት በድምፅና በትርጉም የተለያዩ ናቸው፡፡ ሐመር፣ሐረግ ሕዝብ፣ የሚሉት ቃሎች በሌሎች የሀ ድምፅ እንዳላቸው በሚታወቁት ፊደሎች ቢጻፉ ፍጹም ስሕተት ነው፡፡ ሠራ፣ሥራ፣ንጉሥ፣ ንግሥት ወዘተ የሚሉ ቃሎች በሌላ ሰ ድምፅ ባላቸው በሚመስሉ ፊደሎች ብንጽፋቸው ስሕትት ነው፡፡ ኃይል፣ኃይሉ፣ኅብረት፣ማኅበር፣  ቤሎች የሀ ድምጽ ያላቸው ፊደሎች ቢጻፉ ስሕተት ነው፡፡ በአጠቃላይ ለፊደሎቻችን የሚወክላቸውን ድምፅ በሚገባ አለማወቅ በማይወክሉበት ቦታ ፊደሎችን እያስገባን የቋንቋውን ሥርዓትና አጠቃቀም ከማዛባት አልፎ እያጠፋነው መሆኑን ትውልዱ የተገነዘበ አይመስልም፡፡  በተመሳሳይ ሁኔታ ሀ፣ ሃ ፣ሐ፣ ሓ፣ ኀ፣ ኃ፣ ኻ ፣ህ፣ ሕ፣ ኅ፣ ኽ ፣ ወ ፣ዎ፣ ዉ ፣ ው፣ ዪ ፣ይ ቸ፣ ቼ፣አ፣ ኣ ፣ ዐ፣ዓ፣  ሸ፣ ሼ ፣ ዠ ፣ዤ፣ጀ ፣ ጄ፣ጨ ፣ጬ ወዘተ የሚሉትን ድምፆች ልዩነት በሚገባ ባለማወቅ በማይወከወሉበት ቦታ እያስገባናቸው የቋንቋው ሥርዓት እንዲፋለስ እየተደረገ መሆኑ ግልጽ ነው፡፡  ይህም ሂዶ ሂዶ መዳረሻው ራስን ለቅኝ ተገዥነት ማመቻቸት መሆኑ የተገለጠልን አይመስልም፡፡ የአማርኛን ቋንቋ ድምፆች በሚገባ ለማወቅ ባለመቻላችን፣ ልናውቅም ጥረት ባለማድረጋችን ፊደሎች እንደበዙና አንዳንዶቹም የተደጋገሙ ናቸው በማለት ምትክ የሌላቸውን ቅርሶቻችን እንዲጠፉ እያደረግን ነው፡፡ ቃሎች በሚመጥኑአቸው ድምፆች ፊደሎች አለመጻፍ የድምፅ ልዩነት ብቻ ሳይሆን፣የትርጉምም ለውጥ አላቸው፡፡ በሌላም በኩል ተገቢዎቹን ፊደሎች እንዲጠፉ ፈረድንባቸው ማለት ነው፡፡ ይህም የራስን መጣል፣የሌሎችን ማንጠልጠል ነው፡፡</p>
<p>በቋንቋ ረገድ የራሳችን እየጣልን የኛ ያልሆነን የማንጠልጠላችን ሁኔታ ጎልቶ የሚታየው በሕፃንነታቸው ከአገር የወጡና ውጭ የተወለዱ ልጆች የወላጆቻቸውን የአፍ መፍቻ ቋንቋ እንዲያውቁ አለመደረጉ ነው፡፡ ዛሬ በምዕራቡ ዓለም ብቻ በሚሊዮን የሚቆጠር ኢትዮጵያዊ እንደሚኖር ይታወቃል፡፡ ከተሰዳጁ ኢትዮጵያዊም ውስጥ በርካታውን ቁጥር የያዘው የዐማራው ነገድ እንደሆነ የተለያዩ ጥናቶች ያመላክታሉ፡፡ ይህን ያህል ቁጥር ያለው ሕዝብ ልጆቹን የማንነታቸው ቋሚ መገለጫ የሆነውን ቋንቋቸውን እዲያውቁ ሲያደርግ አይስተዋልም፡፡ ልጆች የወላጆቻቸውን ቋንቋ ባለማወቃቸው፣ወላጆችም ልጆቻቸው የሚያውቁትን የነርሱ ያልሆነ ቋንቋ ስለማያውቁ  በቤት ውስጥ የመግባባት ችግር እንዳለ ጎልቶ መነገር ጀምሯል፡፡ ወላጆች ላሉበት አካባቢና ቋንቋ ባይተዋሮች በመሆናቸው የልጆቻቸውን ቤት ሥራ ተከታትሎ ለማሠራት ባለመቻላቸው ወላጅና ተወላጅ “ፈረንጅና አበሻ” ለመባባል በቅተዋል፡፡ ከዚህ የባሰ ውርደትና ሞት የት አለ?</p>
<p>ልጆቻችን የአገራቸውን ቋንቋ እንዲያውቁ  አለመደረጉም ወጥተው እንዲቀሩ፣ከማንነታቸው እንዲፋቱ፣ከኅሊና ቅኝ ተገዥነት በባሰ የማንነት ቀውስ ውስጥ እንዲገቡ እየተደረገው መሆኑ በውል የተጤነ አይመስልም፡፡ በዓለም ላይ እንደጨው ተዘርተው ከሁለት ሺህ ዘመን በላይ የኖሩት እስራኤላውያን ቋንቋቸውንና ሃይማኖታቸውን ፈጽሞ አላጠፉም፡፡ እንዳውም በስደት ዓለም አዳበሩት፡፡ ዐማራው ምን እንደነካው አይታወቅም  ከእሱነቱ አልፎ፣ የኢትዮጵያዊነት መገለጫ፣የጥቁር ሕዝብ መመኪያ የሆነውን የአፍሪካ ብቸኛ የጽሁፍ ቋንቋ ባለቤት የሆነውን የዐማርኛ ቋንቋ እንደዘበት ተመልክቶ እዲጠፋ የፈረደበት ይመስላል፡፡ “ባለቤት ያቀለለውን አሞሌ፣ ባለዕዳ አይቀበለውም” ነውና እኛ ለልጆቻችን ለማውረስ የተጠየፍነውን ቋንቋ ማን ሊወርስልን፣ሊያሳድግልንና ሊያዳብርልን እንሻለን? ለአማርኛ ከዐማራው ነገድ ሌላ ማን ባለቤት እንዲሆን ይጠበቃል? ቋንቋችን ለመጠበቅና ለማዳበር አለመትጋታችን የኅሊና ቅኝ ተገዥነታችን ያሳደረብን ተፅዕኖ መሆኑን መጠራጠር አይቻልም፡፡</p>
<p>4.	አገር የመጥላት ስሜት እየጎለበተ መምጣት፡- ማንም ሰው አገሩን ይወዳል፡፡ ይህ አጠቃላይ አገላለጽ ነው፡፡ አገራቸውን በልዩ ልዩ ምክንያቶች የሚጠሉ መኖራቸው ግልጽ ነው፡፡ አገራችን ኢትዮጵያ ካለባት የመልካም አስተዳደር ዕጦት በላይ፣ ታዳጊ አገር በመሆኗ  ለዜጎቿ የዕለት ተዕለት ኑሮ አስፈላጊ የሆኑ ነገሮችን በብዛትና በጥራት የምታቀርብ አይደለችም፡፡ የየብስ፣የባሕርና የአየር መጓጓዣ እንደፈለጉት አይገኝም፡፡ ቴሌቪዥን፣ማቀዝቀዣ( ፍሪጂ)፣አውቶሞቢል፣ የቤት ውስጥ መጸዳጃ፣ ሶፋ፣ ወንበር ጠረጴዛ፣ የአካል ንጽሕና መጠበቂያ ሙቅና ቀዝቃዛ ውኃ በቤት ውስጥ መኖር ለሰው ልጆች እንደመሠረታዊ አስፈላጊ ነገሮች የሚታዩ ሳይሆን፣ የሀብት መገለጫ፣ያላቸው ሰዎች ብቻ ሆነው የሚታዩ በመሆኑ ለአብዛኛው ሰው እንደቅንጦት የሚታዩ ናቸው፡፡ ይህም በመሆኑ “ተድራ ብትመለስ የውኃው መንገድ ጠፋት” ዓይነት የሆነባቸው ሰዎች አውሮፓና አሜሪካ ደርሰው ወይም ኑረው ሲመለሱ በውጭ ያዩትን የመገናኛና የአገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች በፈለጉት መጠን አለማግኘት አገራቸውን ጠልተው እንዲመለሱ ይሆናሉ፡፡ ከሁሉም  በላይ ወደ ገጠር ጎራ ካሉ አቧራው፣ቁንጫው፣ትኋኑና የመንገዱ ውጣውረድ በሚፈጥርባቸው የተለየ ስሜት የተነሳ ዳግም ወደ አገራቸው ላለመመለስ ምለው የሚመጡ አያሌዎች እንደሆኑ በየአጋጣሚው የምንሰማው ሐቅ ነው፡፡ ይህ ማለት ሁለመናቸው ለውጭው ኑሮ የተገዛ መሆኑን ያሳይል፡፡  ሁኔታውን ለመለወጥ ከእኔ ምን ይጠበቃል ብሎ የተሻለ ነገር ለመሥራት፣ቴከኖሎጂ ለማሸጋገር  በመትጋት፣ የራስን ድርሻ ተወጥቶ አገርን ሌሎች ከደረሱበት ደረጃ ለማድረስ የሚቻለውን ሁሉ በግልና በተናጠል ከመሥራት ይልቅ፣ የራስን ጠልቶ አያሳየኝ ብሎ ምሎ መመለስ ምን ይባላል/ይህን አቋምና አመለካከት የኅሊና ቅኝ ተገዥነት ካልሆነ ሌላ ምን ልንለው እንችላለን፡፡</p>
<p>5.	ስደት ናፋቂነት፡- “ሞት በእንቅልፍ ይለመዳል”  እነዲሉ ሆኖብን፣ኢትዮጵያውያን በመሣሪያ ኃይል የፖለቲካ ሥልጣን በጨበጡ ቡድኖች በተከታታይ በተፈጸመብንና በሚፈጸምብን የአፈናና ረገጣ አገዛዞች  ስደትን የሞት ያህል እየተለማመድነው መጥተና ፡፡ በግልጽ እነደሚታወቀው፣ አንድ ሰው ከተወለደበትና ካደገበት አካባቢ የሚሰደደው ለሕይዎቱ ቀጣይነት አስጊ ሁኔታዎች ሲፈጠሩ ነው፡፡ እነዚህ የሕይዎት አስጊ ሁኔታዎች ከፖለቲካ አቋም፣ከሃይማኖት፣ከነገድና ከኢኮኖሚ ጋር በተያያዘ መንገድ ልዩነቶች ሲፈጠሩና አለመግባባት ላይ ሲደረስ እንደሆነ ይታመናል፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ በድርቅ፣በአንበጣ ወረራ፣ በመሬት መንሸራተትና በጦርነት ምክንያቶች በሚፈጠሩ ችግሮች ሳቢያ፣ የሰሜኑ ወደ ደቡብ፣የደቡቡ ወደ ሰሜን፣የምሥራቁ ወደ ምዕራብ፣የምዕራቡ ወደ ምሥራቅ  በመፍለስ እንደኖረና ይህም ለአንድነቱ መሠረት ከሆኑት ጉዳዮች አንዱ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ይህ የአገር ውስጥ ፍልሰት የባህል፣የቋንቋና የሃይማኖት መወራረስን በመፍጠር ሕዝቡ የአካባቢያዊ ልዩነቶችን ግድግዳ በመሰባበር፣ኢትዮጵያዊ የሆነ የወል ማንነትን እንዲገነባ እንዳደረገው ግልጽ ነው፡፡ በግልጽ ለመገንዘብ እንደሚቻለው፣የአገር ቤቱ ፍልሰት፣የጠነከረ ኢኮኖሚያዊ አስተሳሰብ፣ ሃይማኖት፣ባህልና ቋንቋ ያላቸው በሄዱበት አካባቢ ነዋሪ ላይ ተፅዕኖ ማሳደራቸው አይዘነጋም፡፡ ተፅዕኖው ሰጥቶ መቀበልን መሠረት ያደረገ ስለነበር የነገዶች ልዩ መታወቂያ የሆነው ቋንቋቸው ተጠብቆ እንዲዘልቅ ሆኗል፡፡</p>
<p>        እስከቅርብ ዘመን ድረስ አገርን ጥሎ ወደ ባዕድ አገር መሰደድ ለኢትዮጵያዊያን የሚታሰብ አልነበረም፡፡ ትውልዱ የስደትን ሕይዎት እየተለማመደው  የመጣው ከአምስቱ ዓመት የአርበኝነት ትግል ዘመን ጀምሮ ነው፡፡ የስደትንም ሕይዎት ለትውልዱ ያስተማሩት ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ከነቤተሰባቸው መሣፍንቱንና መኳንንት የሚባሉትን ይዘው አውሮፓ መግባትና መኖር ጋር ተያያዞ ነው፡፡ “እንደንጉሡ አጎንብሱ”  ወይም “ግዝ እንደንጉሡ አውድማ እንደ አግማሱ” ይሉ ሆኖ፣ ከዚንያ ዘመን ጀምሮ ትውልዱ ስደትን የሕይዎት ማቆያ አማራጭ መንገድ አድርጎ ወሰደው፡፡ በማከታተልም የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እ.ኤ.አ 1948 የሰብአዊ መብት ድንጋጌዎችን ባጸደቀበት ወቅት አንድ ሰው ወይም ቡድን በዘሩ፣በሃይማኖቱ እና በሚያራምደው የፖለቲካ አቋም የተነሳ፣መሳደድ፣መታሰርና መገደል የሚደርስበት መሆኑ ከታወቀና ይህም ከተረጋገጠ ወደ ሁለተኛ አገር ሂዶ የመኖር መብት እንዳለው ያወጣው ሕግ የስደተኝነትን መንፈስ በሕዝቦች ላይ እንዳሳደረ እንገነዘባለን፡፡  በዚህ ድንጋጌ መሠረት ከንጉሠ ነገሥቱ የመጨረሻዎቹ ሁለት ዐሥረተ ዓመታት ጀምሮ ኢትዮጵያውያን “የመደብና የብሔር ጭቆና” ተፈጽሞብናል፣ለዲሞክራሲ ቆመናል የሚሉ ወገኖች በአገዛዙ ሊፈጸምብን ይችላል የሚሉትን እስራትና እንግልት በመፍራት መሰደዳቸው ይታወቃል፡፡<br />
በዘመነ አብዮት  ትውልዱ  በየፊናው ተደራጅቶ ባካሄደው የፖለቲካ ሥልጣን ሽሚያ በርካታ ዜጎች ለሞትና ለእስራት መዳረጋቸው ይታወቃል፡፡ አገዛዙ በሥልጣን ተቃዋሚዎቹና በተገንጣይ ቡድኖች ላይ በወሰደው መራር ርምጃ አያሌ ሰዎች ስደትን እንዲመርጡ እንዳደረጋቸው ግልጽ ነው፡፡ ስደቱ በተከታዩም ብሔርተኛው አገዛዝ በከፋ መልኩ ቀጠለ፡፡ በዘመን ደርግና በዘመነ ወያኔ የሕዝቡ ስደት መሠረት ያደረገው በሚከተለው ፖለቲካዊ አቋም፣ሃይማኖት፣ዘር ወዘተ ከሚመነጭ ግድያና አስራት ፍራቻ ብቻ አይደለም፡፡ የተሻለ ሕይዎት ለመኖር  ከመነጨ ፍላጎትም ስደትን የመረጠው ወገን ቁጥር በቀላሉ የሚገመት አይደለም፡፡ የዚህ ፍላጎት ምንጩም የአገሪቱ ሰላም አስተማማኝ አለመሆን፣ የሥራ ዋስትን አለማግኘት፣የግል ሀብት ተገቢ የሆነ ሕጋዊ ጥበቃ አለማግኘት፣ሥራ በችሎታ ሳይሆን፣ በፖለቲካ ሽርክናና በዘር ላይ መመሥረት ወዘተ ናቸው፡፡ ይህም በመሆኑ፣ ፖለቲካዊ ሁኔታውን መነሻ በማድረግ በልዩ ልዩ መንገዶች  ሕዝቡ መሰደድን ሥራዬ ብሎ ተያያዘው፡፡ ለዚህም ዋናው ተጠቃሽ ምክንያት  ቀድመው የተሰደዱ ሰዎች የግልና የቤተሰብ ሕይዎት በአገር ቤት ከሚኖሩ ጥሩ ነዋሪ ከሚባሉ ሰዎች የተሻለ ሆኖ መገኘት ነው፡፡ በሁለተኛና በሦስተኛ አገር ጥገኝነት ለመጠየቅም ባገር ቤት ያለው የዘር ፖለቲካና በሕዝቡ ላይ የሚፈጸሙ ኢ-ሰባዊ ድርጊቶች ተባብሰው መቀጠል ከፖለቲካ ጋር ምንም ዓነት ግንኙነት የሌላቸው ሰዎች ለሚያቀርቡት “የመብታችን ተገፈፍን ጥያቄ” ተቀባይነት እንዲኖረው አስገደደ፡፡ ስለሆነም በዓለም አቀፍ ሕጉ መሠረት ወደ ፈለገው አገር መግባት ያቃተው  ተሰዳጅ ወገን፣ከኢትዮጵያ ኬንያ፣ ከኬንያ ታንዛኒያ፣ከታንዛኒያ ሞዛምቢክ፣ ከሞዛምቢክ ደቡብ አፍሪካ፣ከደቡብ አፍሪካ ብራዚል፣ ከብረዚል ሜክሲኮ፣ከሜክሲኮ ዩ፣ኤስ.ኤ እያለ አያሌ ፈተናዎችንና ውጣውረዶችን አልፈው የሚገቡት ስደተኞች ቁጥር ቀላል አለመሆኑ በጉልህ እየታየ ነው፡፡ በዚህ ውጣ ውረድ በሞላበት አስቸጋሪ የስደት ጉዞ በአራዊቶች ተበልተው፣በወባ ተነድፈው፣በልዩ ልዩ በሽታዎች ተይዘው ምኞታቸው ሳይሳካ ለሕልፈተ ሕይዎት የሚዳረጉት ቁጥር የት እየለሌ እንደሆነ በጉዞ ቀንቷቸው ከተመኙት አገር የደረሱ ሰዎች የሚናገሩት ነው፡፡<br />
ይህም ብቻ አይደለም፡፡ ከግብፅና ከሶማሊያ ተነስተው ወደ እስራኤልና የመን፣ ከሊቢያ ወደ ጣሊያንና ግሪክ ለመግባት የሚጥሩ፣  ኢትዮጵያኖች በባሕር ላይ  በሚያደርጉት ጉዞ ፣ ጉዞው ሕጋዊ ካለመሆኑ የተነሳ ከሚደርስባቸው የመጓጓዣ ጫና፣ እንግልትና መሳቀቅ በላይ የሚጓጓዡበት ጀልባ  እየሰጠመና እየተገለበጠ የዓሣ ቀለብ የሚሆኑት አያሌዎች እንደሆኑ፣ የዓለም ብዡኃን መገናኛ መሣሪያዎች ዘወትር ለሕዝብ ጆሮ የሚያደርሱት ዜና ነው፡፡  በሌላ በኩል መንግሥት ነኝ ባዩ ሕፃናትና ወጣት ሴቶችን ለባርነት የሚሸጥ ድርጅት አቋቁሞ ሕዝቡን ለባርነት፣ለኅሊናዊ ቅኝ ተገዥነት አመቻችቶታል፡፡ ወደ ዐረቡ ዓለም በአገራቸው ሠርተው የመኖር ዕድሉን አጥተው በግልና በመንግሥት የሚሄዱት ሴቶች እህቶቻችን ቁጥር እጅግ ብዙ ነው፡፡ እነዚህ እህቶቻችን በዐረቡ ዓለም የሚገቡት ስማቸውን ለውጠው፣ሃይማኖታቸውን በልባቸው ይዘው፣በአፋቸው ግን ቀይረው እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ከዚህስ በላይ የኅሊና ቅኝ ተገዥነት በምን ይገለጣል?<br />
እኛ ኢትዮጵያውያን ለኅሊናዊ ቅኝ ተገዥነት እጃችን የሰጠን መሆኑ ማሳያው፣በሚደርሰብን ፖለቲካዊ፣ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ተፅዕኖች ባስከተለብን ሁለንተናዊ ጫና ብቻ የተሰደድን አለመሆኑን ስንገነዘብ ነው፡፡ እነዚህ ጫናዎች የደረሱባቸው ኅሊናዊ ቅኝ ተገዥነትን ወደው ወይም ፈቅደው ሳይሆን፣ ተገደው፣ ከቁጥጥራቸው ውጭ በሆነ ሁኔታ የተፈጠረ መሆኑን ስለሚገነዘቡ፣ቅኝ ተገዥነቱ በኅሊናቸው ውስጥ ቦታ አይኖረውም፡፡ በመሆኑም የማንነታቸው መገለጫ የሆኑ ዕሴቶቻቸውን የኔ ብለው ይጠብቋቸዋል፤ይንከባከቧቸውል፤ያስተዋውቋቸዋልም፡፡ በሌሎች ምክንያቶች ማለትም በኢኮኖሚ ጥቅሞችና ለተሻለ ሕይዎት ሲሉ የተሰደዱ ግን ፣ቀድመው ውጪ ያዩ በመሆኑ የነርሱነት መገለጫ የሆኑ ዕሴቶቻቸውን ፈጥነው ከኅሊናቸው መፋቅ ብቻ ሳይሆን፣ በጥላቻና በንቀት ስለሚመለከቷቸው ያፍሩባቸዋል፤ አይገለገሉባቸውም፤እንዲታወቁም አይፈልጉም፡፡ ከሁሉም በላይ ወላጆች በፈለጉ ጊዜ ከፈለጉት አገር ለመውጣትና ለመግባት እንዲያም ሲል ለመኖር የሚፈልጉ ሰዎች፣ በአገራቸው ምንም ዓይነት የመኖር ችግር ሳይገጥማቸው ሚስቶቻቸው ሊወልዱ ጥቂት ሳምንታት ሲቀራቸው፣ አሜሪካ፣ካናዳ፣ጀርመን ወይም ሌላ አገር ሂደው እንዲወልዱና ሕፃናቱ የዚያ አገር ዜግነት እንዲኖራቸው የማድረጉ ተግባር በስፋት የሚታይ ነው፡፡ የእነዚህ ሰዎች ኅሊናዊ ቅኝ ተገዥነት መጠኑን ያለፈ ብቻ ሳይሆን ለኢትዮጵያዊነት ያላቸው ስሜትና እምነት ባንዳዊ  ነው፡፡  ዛሬ በኢትዮጵያ የተሻለ ገቢ ካላቸው ሰዎች መካከል አብዛኛዎቹ ልጆቻቸው የኢትዮጵያዊነት ዜግነት ያላቸው አይደሉም፡፡  ይህም ሕዝቡ ትናንት በዘመነ ቅኝ አገዛዝ ወቅት በአካል ቅኝ ያልተገዛው ኢትዮጵያዊ  በሚከተሉት ሁለት ተያያዥና ተደጋጋፊ ምክንያቶች ለኅሊና ቅኝ ተገዥነት እንደተዳረገ እናያለን፡፡<br />
አንድ ሕዝብ ትውልድ አገሩን ትቶ ወደማያውቀው አገር የሚሰደደው ሁለት ተያያዥና ተደጋጋፊ የሆኑ ሁኔታዎች ተሟልተው ሲገኙ ነው፡፡ የመጀመሪያው በአገሩ በሰላም ሠርቶ የመኖር ፖለቲካዊ፣ኢኮኖሚያዊ፣ማኅበራዊና ባህላዊ መብተና ነፃነቶቹን ሲገፈፍና ሲነጠቅ፣ በሕይዎት ለመኖር የሚያስችል ሁኔታ ሲጣበብበት ነው፡፡ ሁለተኛው ከአገሩ ወጥቶ ለመኖር የሚያስችል ሁኔታ መኖሩ አስተማማኝ ሲሆን ናቸው፡፡ እነዚህም ከውስጥ አስወጪ ገፊ ኃይል እና ከውጪ ተቀባይ ሳቢ ኃይል መኖር ናቸው፡፡ በዚህ ረገድ ላለፉት 50 እና 60 ዓመታት የኢትዮጵያ ፖለቲካዊ፣ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ ሕዝቡን በነበረ መልኩ እንዲኖር የፈቀደ አልሆነም፡፡ ትውልዱ በፖለቲካዊ ፍልስፍና፣በነገድ፣ በሃይማኖት፣በሥልጣን አያያዝ ተከፋፍሎ አገሪቱን የብጥብጥ ምድር አደረጋት፡፡ ሥልጣን የያዙ ቡድኖች ተቀናቃኛችን ነው ያሉትን ግለሰብና ቡድን ያላንዳች ርኅራኄ ገደሉ፣አሰሩ፣አሰቃዩ፤ የፖለቲካ ትርምሱ ማኅበራዊ ሰላምን በእጅጉ በማመሱ፣በሰላም ወጥቶ ለመግባት፣ሠርቶ ለማምረት፣ወልዶ ለመሳም፣አሳድጎ ለመዳር አላስቻለም፡፡ እነዚህ ሁኔታዎች በስፋትና በተከታታይ መታየት ሕዝቡን አማራጭ የመኖሪያ አካባቢን እንዲያማትር ግድ አለው፡፡  ባደረገው የአማራጪ መኖሪያ ፍለጋም ለማስተማር ቀይ ሳንቲም ሳያወጡ በተማረ የሰው ጉልበት ያልተማረ ሰው ሊሠራቸው የሚችሉ ሥራዎችን በጥራት፣በቅልጥፍናና ሥጋት በሚፈጥረው ጥንቃቄ ኃላፊነቱን የሚወጣ ፣ያወቀ፣ግን በርካሽ የጉልበት ዋጋ ጥራት ያለው ሥራ የሚሠራ የሰው ኃይል የሚፈልጉ አገሮች ቁጥር መበራከት፤(አሜሪካ፣ካናዳ፣አውትራሊያ፣ጀርመን፣ኖርዌ፣ስውዲን) የኢትዮጵያዊነት ብሔርተኝነትን ለማጥፋት የረጅም ጊዜ ዕቅድ የነበራቸው አገሮች የተፈጠረውን አጋጣሚ በመጠቀም ትውልዱን ከኢትዮጵያዊነት ስሜትና እምነት ለማፋታት ባለቸው የቆየ ዓላማ መሠረት፣ ስደት ፈላጊዎችን በገፍ የመቀበል ፍላጎት አሳዩ፡፡  ይህም  የሕይዎት ማቆያ ፣የተሻለ ኑሮ መምራት አማራጪ ይፈልግ ለነበረው  ሰው እንደመልካም አጋጣሚ ቆጥሮ የተቸገረውም ያልተቸገረውም ለስደት ተሰለፈ፡፡ ፣ስደትንም አማራጭ የሌለው ተመራጭ አድርጎ እንዲይዘው አደረገው፡፡ በነዚህ የውስጥና የውጪ ሁኔታዎች ተሟልተው መገኘት ኢትዮጵያዊው የተሻለ ኑሮና ሰላም የነበራቸው ሁሉ ቋሚ ንብረቶቻቸውን በአልባሌ ዋጋ እየሸጡ ተሰደዱ፡፡ ምዕራባውያኑ በተለይም ዩ.ኤስ.ኤ በራሱ ፍላጎት የሚሰደደው ሕዝብ የሚፈልገውን ያህል የተማረ የሰው ኃይል ሊያስገኝላት ባለመቻሉ፣ዲ.ቪ የሚል ፕሮግራም በመዘርጋት አያሌ የሦስተኛው ዓለም ሕዝቦችን የተማረ የሰው ኃይል መሳቡ ይታወቃል፡፡ በዚህ ፕሮግራም የተሰደዱ ኢትዮጵያውያን ቁጥር በቀላሉ የሚገመት አይደለም፡፡ ይህም ወዶና ፈቅዶ ራስን ለኅሊና ቅኝ ተገዥነት ማዋል አለመሆኑን በምን መልክ ማሳመን ይቻላል?<br />
በዚያም  አልን በዚህ እኛ ኢትዮጵያውያን በአካል ቅኝ ሳንገዛ፣የኅሊና ቅኝ ተገዥዎች መሆናችንን ልናስተባብልበት የምንችልበት ማስረጃ የለም፡፡ የሚያዋጣው የኅሊና ቅኝ ተገዥዎች አልሆንም ብሎ በመሸምጠጥ ሳይሆን፣ለዚህ የዳረጉንን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ምክንያቶች ምን እንደሆኑ ዐውቀን ከነዚያ ሁኔታዎች ልንወጣ የምንችልባቸውን መንገዶች ማመቻቸት ነው፡፡ እንደ ነገድ ሳይሆን፣እንደ አገር በአንድነት ማሰብና በአንድነት መቆም ስንችል ነው፡፡ የተጫነንን ከማንነት የመፋታት አባዜ ከላያችን ላይ አራግፈን ጥለን አኩሪው ማንነታችን ስንላበስ ነው፡፡ ታሪካችን ፣ባህላችን፣ቋንቋችን፣ በአጠቃላይ እኛነታችን ዐውቀን ለማንነታችን ዳብሮ መቀጥል ስንቆም፣ለዚህም ተገቢ የሆነውን መስዋእትነት ለመክፈል ዝግጁ ስንሆን ብቻ ነው፡፡ </p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1214"     class="crp_title">የኢትዮጵያ ሙዚቃ ከየት ተነስቶ ምን&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1575"     class="crp_title">“አይቴ ብሔሩ ለአማራ . . . የአማራ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1590"     class="crp_title">ባሁኑ ሰዓት በአማራው ወገናችን ላይ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1761"     class="crp_title">የአማርኛ ተናጋሪ ኢትዮጵያውያን&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/549"     class="crp_title">መርዝ ከውጭ ይረጫል ወይም ከውስጥ&hellip;</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=83026</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>የአዲስ ጉዳይ መጽሔት ርዕሠ አንቀጽ፡ የሙስናን ዛፍ ለማድረቅ ቅርንጫፉን ብቻ መቁረጥ በቂ አይሆንም</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3329</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3329#comments</comments>
		<pubDate>Sun, 19 May 2013 00:09:27 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3329</guid>
		<description><![CDATA[ፈረንጆች ታይታኒክ የተባለችውን ግዙፍ መርከብ የገለበጠውን ዓይነት ከባሕር በታች የተደበቀ ግግር በረዶ ‘ለአንዳንድ የማይታዩ ነገር ግን ግዙፍ የሆኑ’ ችግሮች ተምሳሌት አድርገው ይጠቀሙበታል።ከባሕሩ ውስጥ ብቅ ብሎ የሚታየው የበረዶ ጫፍ ሲያዩት ትንሽ ስለሚመስል ብዙዎችን ያሳስታል-ከሥሩ ያለውን ተራራ የሚያህል ግዙፍ የበረዶ ግግር ለመገመት አያስችልምና።ለዚህም ነው አንዳንድ ተገልጦ ያልታየ ነገር ግን በትንሹ ብቅ ያለ ችግርን “this is only the [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3198">የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በተጠርጣሪዎቹ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3201">በሙስና ተጠርጥረው የታሰሩት&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1080">ኢህአዴግ ተቃዋሚዎችን በኪራይ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/705">የጁኔይዲ ሳዶን ወደ ኬኒያ መሰደድ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1110">“መንግሥት የለም ወይ?!”- የማንና&#8230;</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/addis-guday.jpg"><img src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/addis-guday-220x300.jpg" alt="addis guday" width="220" height="300" class="alignleft size-medium wp-image-3330" /></a>ፈረንጆች ታይታኒክ የተባለችውን ግዙፍ መርከብ የገለበጠውን ዓይነት ከባሕር በታች የተደበቀ ግግር በረዶ ‘ለአንዳንድ የማይታዩ ነገር ግን ግዙፍ የሆኑ’ ችግሮች ተምሳሌት አድርገው ይጠቀሙበታል።ከባሕሩ ውስጥ ብቅ ብሎ የሚታየው የበረዶ ጫፍ ሲያዩት ትንሽ ስለሚመስል ብዙዎችን ያሳስታል-ከሥሩ ያለውን ተራራ የሚያህል ግዙፍ የበረዶ ግግር ለመገመት አያስችልምና።ለዚህም ነው አንዳንድ ተገልጦ ያልታየ ነገር ግን በትንሹ ብቅ ያለ ችግርን “this is only the tip of the iceberg” (ይህ የግግር በረዶው ጫፍ ብቻ ነው) በማለት የሚገልጹት-ከሥሩ ቢታይ ሥር የሰደደና ሰፊ ነው ለማለት።<br />
ሰሞኑን ከተራ ደላሎችና ትራንዚተሮች አንሥቶ እስከ ቱጃር ባለሀብቶችና ከፍተኛ ባለሥልጣኖች ድረስ የተዳረሰው የሙስና ቅሌት የብዙው ዜጋ የመወያያ ርእስ ሆኖ ሰንብቷል።ይህ የሰሞኑ ክስተት ብቻውን ግን የመጨረሻ ውጤት አይደለም።ይልቅስ ከባሕር በታች ገዝፎ እንደተደበቀው የግግሩ በረዶ ጫፍ ጥቂቱ ማሳያ ነው እንጂ።<br />
መንግሥት ለረጅም ዘመን ሙስናን የመዋጋት ቁርጠኝነትም ቢያሳይም በዚያው ልክ ግን ችግሩ በአገራችን አሳሳቢ ደረጃ ላይ አልደረሰም ሲል ኖሯል። አንዳንድ መረጃዎች ብቅ ሲሉም ችግሩ እንደሚወራው አይደለም፣ የተጋነነ ነው ሲል ተደምጧል። ይህን ሲል ቢቆይም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን የሙስናን አፈጻጸም ረቂቅነትን እያባከነ ያለውን የሕዝብና የሀገር ንብረት ሲያስተውል ግን አሳሳቢነቱን አምኖ ለመቀበል ተገድዷል፡:<br />
በአገራችን እየተስፋፋ የመጣውን ሙስና በተመለከተ ከመንግሥት አስቀድሞ የነቃው ሕዝቡ ነው ማለት ይቻላል፡፡ ሙሰኞችን በተመለከተ ሕዝቡ “በማስረጃ ካልሆነ” እየተባለ ሐሳቡን የሚገልጽበት መድረክ ባያገኝም እርስ በርሱ መወያየቱ ግን አልቀረም፡፡ በተለይም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በፍጥነት ወደላይ እየተተኮሰ የመጣውን የአንዳንድ የመንግሥት ባለሥልጣናት አኗኗር በመመልከትም ሆነ ያካበቱትን ንብረት በመታዘብ ከጥርጣሬ ያለፈ ግንዛቤ ይዞ ነበር፡፡ ቢያንስ እነዚህ ሰዎች ምንጩ ያልታወቀ ገንዘብና ሀብት ማካበታቸውን መጠርጠር ችሏልና።<br />
የፌዴራል ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን እስከ አሁን ድረስ በሙስና ባሕር ውስጥ ሲዋኙ የቆዩትን ትንንሾቹን ዓሣዎች እንጂ ዓሣ ነባሪዎቹን ለመያዝ ድፍረቱም፣ ፍላጎቱም አቅሙም የለውም እየተባለ ሲታማ ቆይቷል፡፡ በተለያዩ መድረኮችም ተጠይቋል። ለምሳሌም ኮሚሽኑ ባለፈው ማክሰኞ የሰሞኑን ሙስና በተመለከተ ጋዜጣዊ መግለጫ ሲሰጥ ይኸው ጥያቄ ለኮሚሽነር ዓሊ ሱሌይማን ተነሥቶላቸው ነበር። “እኛ ከግለሰቦች ጋር ሳይሆን ከወንጀሉ ጋር ነው ጉዳያችን። ሙስና ከፈጸመ ማንንም አንተውም። ሁሉንም ጥፋተኞች ለሕግ እናቀርባለን” ብለዋል።<br />
ያም ሆኖ ‘የመንግሥትን ሌቦች’ በተፈለገው ሁኔታ ወደፍርድ አደባባይ ቶሎ ቶሎ ብቅ ሲሉ አይተናቸው አናውቅም። አንዳንድ ጊዜ ስለመንግሥት ሌቦች በመንግሥት መዋቅሮች ውስጥ መሰግሰግና አለአግባብ መበልፀግ አልፎ አልፎ በራሱ በመንግሥት ከሚነገረው ውጪ እነዚህ ‘ሌባ&#8217; የተባሉት ሰዎች የት እንዳሉና የተነከሩበት የሙስና ባሕር ስፋትና ጥልቀትስ ምን ያህል እንደሆነ ማወቅ ሳይቻል ቆይቷል፡፡ የፌዴራል ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በአብዛኛው በዝቅተኛ ደረጃ ላይ ባሉ በመንግሥት መሥሪያ ቤት ሹሞች የሚፈፀሙትን የሙስና ድርጊቶች ተከታትሎ በማጋለጥና አጥፊዎች በማስቀጣት ረገድ የማይናቅ ሥራ ቢሠራም ትልልቆቹን ዓሣዎች ግን በተደጋጋሚ ጊዜ ሳይደፍራቸው ቆይቶ ነበር፡፡<br />
አሁን ፀረ ሙስና ኮሚሽን የጀመረው ሙሰኞችን ወደሕግ የማቅረብ አካሄድ ይበልጥ ይግፋበት የሚያሰኝ ተግባር ነው፡፡ ለዚህ የኮሚሽኑ እርምጃም ከመቀመጫችን ተነሥተን ተገቢውን ክብርና አድናቆት እንሰጣለን፡፡ ሙስናን መዋጋት የመንግሥት ብቻ ሳይሆን የሁሉም ዜጎች ሓላፊነት መሆኑን በመረዳት ለኮሚሽኑ ሥራ መቃናት የየበኩላቸውን አስተዋጽኦ ላበረከቱ በስም ያልተገለጹ ዜጎችም በአድናቆት እናጨበጭባለን። ይህን በምንናገርበት አንደበታችንም እግረ መንገዳችንን እርማት የሚያሻውን የኮሚሽኑን አካሔድ ለመጠቆም እንሞክራለን፡፡<br />
አንደኛ ነገር ኮሚሽኑ በአንድ መንግሥት መሥሪያ ቤትና በተወሰኑ ግለሰቦች ላይ ብቻ ሳይሆን በተመረጡ ተቋሞች ላይ ጊዜ ወስዶ ተመሳሳይ መረጃ የመሰብሰብ ሥራውን ካጠናቀቀ በኋላ ውጤቱን በአንድ ላይ ይፋ ቢያደርግ የተሻለ ይሆን ነበር እንላለን፡፡ አሁን እንዳደረገው በአንድ ቦታ ላይ ማተኮሩ ለሌሎች የማንቂያ ደወል ሊሆናቸው ይችላል፡፡ በዚህም መረጃዎችን ለመደበቅ፣ ምስክሮች ሊሆኑ የሚችሉትን የዶክመንትና የሰው ማስረጃዎችን ደብዛ ለማጥፋት እንዲሁም በሙስና የሰበሰቡትን ሀብትና ንብረት በተለያዩ ዘዴዎች ለማሸሽ ጊዜ ያገኛሉ ማለት ነው፡፡<br />
አሁን በቁጥጥር ሥር የዋሉት ተጠርጣሪዎች ጉዳይ በፍርድ ቤት እልባት እስኪያገኝ ድረስ የሕዝቡም የኮሚሽኑም ትኩረት በእነሱ ላይ ይውልና ያልተጋለጡ ባለሥልጣናት ከሚታዩበት የግግር በረዶው ጫፍ ተነሥተው ወደ ጥልቁ ባሕር ለመግባትና ለመሰወር አመቺ ሁኔታ ሊፈጠርላቸው ይችላል፡፡ ሁለት ዓመት ፈጀ የተባለው ክትትል እነዚህን 24 ሰዎች ብቻ ለመያዝ ከሆነ በርግጠኝነት ዘግይቷል። ክስ ከተመሰረተበት የሙስና ጉዳይ ተነካኪነት አንጻር ሲታይ ሌሎችም ባሕሩ የደበቃቸው ብዙዎች መኖራቸው አይቀርም።<br />
ያም ሆኖ አሁን የተጀመረው እርምጃ ተጠናክሮ የግግሩ በረዶ ጫፍ በባሕሩ ተሸፍኖ ሳይጠፋ በፊት ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል፡፡ በሌላ አባባል የአንድ ሰሞን የሚዲያ ግርግር ከመሆን አልፎ ተከታታይ መሆን ይጠበቅበታል ማለት ነው፡፡<br />
ሁለተኛው ጉዳይ ኮሚሽኑ የመንግሥት ባለሥልጣናት ሀብት ምዝገባ ውጤት ለሕዝብ ይፋ ይሆናል ብሎ ቃል ከገባ ረዘም ያለ ጊዜ ቢሆንም ይህ እስከ አሁን ባለመፈፀሙ የትኛው የመንግሥት ባለሥልጣን ምን ያህል ሀብት እንዳለው በሕዝቡ ዘንድ ሳይታወቅ ቆይቷል፡፡ ይህ የ30ሺህ ሰዎችን ሀብት መዝግቤያለሁ የሚለው የኮሚሽኑ ድክመት ነው። የባለሥልጣናት ሀብት በጊዜ ቢታወቅ ኖሮ ከሚታወቀው አቅማቸው በላይ ሲያካብቱ ሕዝብ አይቶ ዝም አይልም ነበር።<br />
ሌላው ኮሚሽኑ የግሉን ዘርፍ ‘አያገባኝም’ ብሎ መተዉ አግባብ አይደለም እንላለን። እስከ አሁን ድረስ በሙስና ከመንግሥት ባለሥልጣናት ጋር የተከሰሱት የግል ባለሀብቶች ናቸው። ከየት እንዳመጡት ሳይታወቅ ድንገት ጣሪያ ላይ የሚወጡት የግል ባለሀብቶች ጀርባ ካልተጠና ወደፊትም ባለሥልጣናትን ማባለጋቸው፣ ሙስናውም ተጠናክሮ መቀጠሉ አይቀርም።<br />
የሆነው ሆኖ የፌዴራል ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን እስካሁን የሠራው ሥራ የሚያስመሰግነው ነው። የራሱን አቃቤ ሕግ በሙስና ከመክሰስ አንሥቶ ‘የመንግሥት ሌቦችን’ ጥሩ እያየ ነው። አሁንም የመንግሥት ባለሥልጣናትን ሀብት በፍጥነት ለሕዝቡ ያሳውቅ፡፡ ካሁን በኋላም ጥረቱን በማጠናከር ከሕዝቡም ከሚዲያው ጋር ይበልጥ በመተባበር በሙስና ላይ የተጀመረውንና ጠብ…ጠብ የሚለውን ካፊያ ዘመቻ ወደ ጎርፍ ይለውጥ! ከግግር በረዶው ጫፍ ላይ የሚታዩትንም ሆነ ከባሕሩ ሥር የተደበቁትን ተጠርጣሪዎች ለማጋለጥና ለፍርድ ለማቅረብ ይበልጥ በተቀናጀ ሁኔታ ይነሳ! የሙስናውን ዛፍ ከቅርንጫፉ ብቻ ሳይሆን ከሥሩ ይቁረጥ!!</p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3198"     class="crp_title">የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በተጠርጣሪዎቹ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3201"     class="crp_title">በሙስና ተጠርጥረው የታሰሩት&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1080"     class="crp_title">ኢህአዴግ ተቃዋሚዎችን በኪራይ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/705"     class="crp_title">የጁኔይዲ ሳዶን ወደ ኬኒያ መሰደድ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1110"     class="crp_title">“መንግሥት የለም ወይ?!”- የማንና&hellip;</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=83027</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>የ’ልማታዊው አርቲስት’ ሠራዊት ፍቅሬ የኢቲቪ ፕሮግራም ታገደ</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3320</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3320#comments</comments>
		<pubDate>Sat, 18 May 2013 22:28:32 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3320</guid>
		<description><![CDATA[(ዘ-ሐበሻ) በሕዝብ ዘንድ &#8220;ልማታዊ አርቲስት&#8221; በሚል የመሽሟጠጫ ስያሜ ከሚጠሩት አርቲስቶች መካከል የቀድሞው የደርግ ወታደርና የአሁኑ የወያኔ ስርዓት ዋነኛ አቀንቃኝ አርቲስት ሰራዊት ፍቅሬ፤ ለመንግስት በሚያደርጋቸው የአጎብዳጅነት ተግባራት በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ላይ የቶክ ሾው ፕሮግራም እንዲያዘጋጅ የዓየር ሰዓት ተፈቅዶላት ሲሰራ መቆየቱ ይታወሳል። ከአዲስ አበባ የዘ-ሐበሻ ምንጮች እንደጠቆሙት አርቲስቱ በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ላይ ያቀርበው የነበረው ቶክ ሾው ውለታው ተዘንግቶ እንዲታገድ [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1060">አርቲስት ሠራዊት ፍቅሬ በአስገድዶ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/163">የአርቲስት ታምራት ሞላ የቀብር ሥነ-&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1660">ከየት ነው ያመጣት?!? (ግጥም&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1690">አርቲስት ብርሃኑ ተዘራ በኢትዮጵያ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1807">ድምጻዊ ብዙአየሁ ደምሴ በካናዳ&#8230;</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/03/serawit-fikre.jpg"><img src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/03/serawit-fikre-300x146.jpg" alt="serawit fikre" width="300" height="146" class="alignleft size-medium wp-image-1061" /></a>(ዘ-ሐበሻ) በሕዝብ ዘንድ &#8220;ልማታዊ አርቲስት&#8221; በሚል የመሽሟጠጫ ስያሜ ከሚጠሩት አርቲስቶች መካከል የቀድሞው የደርግ ወታደርና የአሁኑ የወያኔ ስርዓት ዋነኛ አቀንቃኝ አርቲስት ሰራዊት ፍቅሬ፤ ለመንግስት በሚያደርጋቸው የአጎብዳጅነት ተግባራት በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ላይ የቶክ ሾው ፕሮግራም እንዲያዘጋጅ የዓየር ሰዓት ተፈቅዶላት ሲሰራ መቆየቱ ይታወሳል። ከአዲስ አበባ የዘ-ሐበሻ ምንጮች እንደጠቆሙት አርቲስቱ በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ላይ ያቀርበው የነበረው ቶክ ሾው ውለታው ተዘንግቶ እንዲታገድ ተደርጓል።<br />
&#8220;ግራና ቀኝ&#8221; የሚል ቶክ ሾው ከሌላኛው &#8216;ልማታዊ&#8217;አርቲስት ሽመልስ በቀለ ጋር ላለፉት 6 ወራት ሲያቀርብ የቆየው የደርጉ ወታደር ሰራዊት ፍቅሬ ይህን የዓየር ሰዓት ያገኘው ለመንግስት ባለው ታማኝነት እንደሆነ የሚታወቅ ቢሆንም ድንገት ያቀርበው የነበረው ፕሮግራም በወያኔ ካድሬዎች በሚመራው ኢቲቪ እንዲታገድ መዳረጉ አስተተያየት ሰጪዎችን &#8220;ፍቅር አለቀ ወይ?&#8221; የሚሉ ግምቶችን እንዲሰጡ በር ከፍቶላቸዋል።<br />
የአቶ መለስ ዜናዊ ሕልፈት ከተሰማ በኋላ አርቲስቶች ጥቁር በጥቁር ለብሰው &#8220;ባለ ራዕዩን መሪ&#8221; እንዲቀብሩ በማስተባበር እንዲሁም ጥቁር በጥቁር አንለብስም ያሉና ለቅሶ አንደርስም ያሉ አርቲስቶችን &#8220;ሲያስጠቁር&#8221; (ለመንግስት በማቃጠር) ነበር እየተባለ የሚተቸው አርቲስቱ 6 ወር በቴሌቭዥን ያቀረበው &#8220;ግራና ቀኝ&#8221; ቶክ ሾው እንዲታገድ የተደረገው &#8220;አዝናኝ ፕሮግራም&#8221; አይደለም በሚል ምክንያት ነው ተብሏል። ይህ እገዳ እስከመቼ ሊቀጥል እንደሚችል እንደማያውቁ የሚገልጹት የዘ-ሐበሻ ምንጮች ከባለፈው እሁድ ጀምሮ መታየት አቁሟል ብለዋል።<br />
ኢቲቪ ወትሮም አዝናኝ ፕሮግራም አቅርቦ የት ያውቅና ሲሉ የሚተቹ አስተያየት ሰጪዎች አዝናኝ ፕሮግራም አይደለም በሚል ቶክ ሾው እንዲታገድ መደረጉ በቂ ምክንያት አይደለም በሚል ከእገዳው በስተጀርባ አንድ ነገር እንዳለ ይገምታሉ። በተለይም እንደሪፖርተርን ያሉ አፍቃሬ ሕወሓት/ኢሕአዴግ ያሉ ጋዜጦች &#8220;በአቶ መለስ ስም መነገድ ይቁም&#8221; በሚል በረዥሙ ሲተቹ የከረሙት እንደሠራዊት ያሉትን ሆዳም አርቲስቶች ነው የሚሉት አስተያየት ሰጪዎች የኢቲቪ ካድሬ መሬዎች የሰራዊትን ማንነት በግልጽ ተረድተው ይሆናል ያገዱት ሲሉ አስተያየታቸውን ይሰጣሉ።<br />
 በዚህ ዜና ዙሪያ ዘ-ሐበሻ አርቲስት ሠራዊት ፍቅሬን ለማነጋገር ያደረገችው ጥረት አልተሳካም።<br />
አርቲስት ሠራዊት ፍቅሬ በቅርቡም በአስገድዶ መድፈር አቤቱታ እንደቀረበበት መዘገቡ ይታወሳል።<br />
<a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1060">የአስገድዶ መድፈር አቤቱታውን ዜና ለማንበብ እዚህ ይጫኑ<br />
</a><br />
ለግንዛቤ ደግሞ  የታገደውን የሰራዊት ፍቅሬ ሾው አቅርበናል።<br />
<iframe width="500" height="380" src="http://www.youtube.com/embed/eqpbiq2Y2LY" frameborder="0" allowfullscreen></iframe></p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1060"     class="crp_title">አርቲስት ሠራዊት ፍቅሬ በአስገድዶ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/163"     class="crp_title">የአርቲስት ታምራት ሞላ የቀብር ሥነ-&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1660"     class="crp_title">ከየት ነው ያመጣት?!? (ግጥም&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1690"     class="crp_title">አርቲስት ብርሃኑ ተዘራ በኢትዮጵያ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1807"     class="crp_title">ድምጻዊ ብዙአየሁ ደምሴ በካናዳ&hellip;</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=82961</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>Sport: የቤካም እና የካራገር “ጫማ ሰቀላ” የእንግሊዛውያኑ ብቻ ሳይሆን የኛም ወሬ ሆኗል</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3315</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3315#comments</comments>
		<pubDate>Sat, 18 May 2013 22:12:02 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3315</guid>
		<description><![CDATA[ከአሰግድ ተስፋዬ የተወዳጁ እግር ኳስ ስፖርት « ፈጣሪ » እንደሆነች የሚነገርላት ነገር ግን በዓለም አቀፍ ውድድሮች ብዙም ውጤታማ መሆን ያልቻለው እንግሊዝ በተለያዩ ወቅቶች ምርጥ እግር ኳሰኞችን አፍርታለች። ከነዚህ ምርጥ እግር ኳስ ተጫዋች ኮከቦች መካከል ላለፉት ሃያ ዓመታት በስፖርቱ በስኬታማነት ያሳለፈው ዴቪድ ቤካምና ከልጅነት እስከ እውቀቱ የመርሲሳይዱን ክለብ መለያ ብቻ የለበሰው ጂሚ ካራገርን ፣ ዋይኔ ሩኒን [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/776">የአውሮፓ ፉትቦል ፌዴሬሽን ድሮግባ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2614">አሥሩ ዋንጫዎች:- አሥሮቹ ጀግኖችና&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3204">ሰር አሌክስ ፈርጉሰን በቁጥሮች</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1866">ትውልደ ኢትዮጵያዊው በአርሰናል&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/233">ጆናታን ፒትሮይፓ የአፍሪካ ዋንጫ&#8230;</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/david-bechekam.jpg"><img src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/david-bechekam-300x200.jpg" alt="david bechekam" width="300" height="200" class="alignleft size-medium wp-image-3316" /></a></p>
<p><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/david-bechekam-2-caragher.jpg"><img src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/david-bechekam-2-caragher-300x199.jpg" alt="david bechekam 2 caragher" width="300" height="199" class="alignleft size-medium wp-image-3317" /></a>ከአሰግድ ተስፋዬ<br />
የተወዳጁ እግር ኳስ ስፖርት  « ፈጣሪ » እንደሆነች የሚነገርላት ነገር ግን በዓለም አቀፍ ውድድሮች ብዙም ውጤታማ መሆን ያልቻለው እንግሊዝ በተለያዩ ወቅቶች ምርጥ እግር ኳሰኞችን አፍርታለች።<br />
ከነዚህ ምርጥ እግር ኳስ ተጫዋች ኮከቦች መካከል ላለፉት ሃያ ዓመታት በስፖርቱ በስኬታማነት ያሳለፈው ዴቪድ ቤካምና ከልጅነት እስከ እውቀቱ የመርሲሳይዱን ክለብ መለያ ብቻ የለበሰው ጂሚ ካራገርን ፣ ዋይኔ ሩኒን ፣ ማይክል ኦዌንና  ሌሎች  ተጫዋቾችን መጥቀስ ይቻላል።<br />
ከእነዚህ ተጫዋቾች መካከል በስፖርቱ ባስመዘገበው ስኬት ግንባር ቀደም የሆነው ዴቪድ ቤካምና የሊቨርፑሉ ጂሚ ካራገር « ጫማ መስቀላቸውን» ገልጸዋል። የማንችስተር ዩናይትዱ የተከላካይ መስመር ተሰላፊው ሪዮ ፈርዲናንድ ደግሞ ራሱን ከብሔራዊ ቡድኑ ማግለሉን ይፋ አድርጓል።<br />
እነዚህ ጉዳዮች የመገናኛ ብዙኃን ሰሞነኛ መሪ ዜና ቢሆኑም ልዩ ትኩረት ያገኘው የዴቪድ ቤካም ጫማ መስቀል ጉዳይ ነው።<br />
አንጋፋውና ውጤታማው የማንችስተር ዩናይትድ እግር ኳስ ክለብ አሰልጣኝ የነበሩት ሰር አሌክስ ፈርጉሰን ካሳደጓቸውና « ፈርጊ ቤቢስ » እየተባሉ ይታወቁ ከነበሩት መካከል አንዱ የሆነው ዴቪድ ቤካም ለእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን በ115 ጨዋታዎች ላይ ተሰልፎ ተጫውቷል። ለአሳዳጊው ማንችስተር ዩናይትድ እግር ኳስ ክለብ ደግሞ 394 ጨዋታዎችን አድርጓል።<br />
የ38 ዓመቱ ቤካም « ቀያይ ሰይጣኖች » በመባል ከሚታወቀው ማንችስተር ዩናይትድ ክለብ ጋር ስድስት የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫዎችንና የሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫዎችን አንስቷል። በምስራቃዊ ለንደን የተወለደው የመሐል ሜዳ ተጫዋቹ ቤካም ከአሳዳጊው ክለብ ከተለያየ በኋላ ለስፔኑ ኃያል ሪያል ማድሪድ ፣ በአሜሪካ ሜጀር ሶከር ሊግ ተሳታፊ ለሆነው ሎስ አንጀለስ ጋላክሲ፣ለጣሊያኑ ኤሲ ሚላን ፣ በመጨረሻ ደግሞ ለፈረንሳዩ ሻምፒዮና ፓሪስ ሴንት ጄርሜን እግር ኳስ ክለቦች ተጫውቷል። ተጫዋቹ በጨዋታ ዘመኑ ከዩናይትድ ጋር ያነሳቸውን ዋንጫዎች ጨምሮ በጠቅላላው 19 ዋንጫዎችን አንስቷል።<br />
ዴቪድ ቤካም በአራት የተለያዩ ሊጎች ከተለያዩ ክለቦች ጋር ዋንጫ በማንሳት ብቸኛው እንግሊዛዊ ተጫዋችም ነው።<br />
ዴቪድ ቤካም ቀያይ ሰይጣኖቹን በተለ ማማጅነት የተቀላቀለው በአውሮፓውያኑ 1991  ሲሆን በቀጣዩ ዓመት ለዋናው ቡድን ተሰልፎ የመጫወት እድል አግኝቷል። ከአንድ ዓመት በኋላ የመጀመሪያውን የፕሮፌሽናል ተጫዋችነት ኮንትራት ፈርሟል። በኦልድ ትራፎርድ በነበረው ቆይታ ያሳየው ምርጥ ብቃቱ ዓለም አቀፍ እውቅና አስገኝቶለታል። ይህንን እውቅናውን ተከትሎም ታላላቅ ተጫዋቾችን በመሰብሰብ የሚታወቀውን የስፔኑን ሪያል ማድሪድን ተቀላቅሎ በአውሮፓውያኑ 2003 የላ ሊጋውን ዋንጫ አንስቷል።<br />
ከስፔኑ ኃያል ወደ አሜሪካው ሎስ አንጀለስ ጋላክሲ ተዛውሮ ተጫውቷል። በዚህ ክለብ በነበረው ቆይታ በውሰት ለጣሊያኑ ኤሲ ሚላን ተሰልፎ የመጫወት እድል አግኝቷል። ወደክለቡ ኤልኤ ጋላክሲ ተመልሶ ዋንጫ ካነሳ በኋላ ለፈረንሳዩ ፓሪስ ሴንት ጄርሜን ፈርሞ ተጫውቷል።  እንዲሁም ዋንጫ ካነሳ በኋላ ጫማ መስቀሉን ይፋ አድርጓል።<br />
ቤካም በሦስት ተከታታይ የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎች ላይ ግብ በማስቆጠር ብቸኛው እንግሊዛዊ ተጫዋች ከመሆኑም በላይ በአውሮፓ ዋንጫ ለግብ የሚሆኑ በርካታ ኳሶችን በማቀበል በታሪክ ሁለተኛው ተጫዋች ነው።<br />
  «ለልጅነት ክለቤ ማንችስተር ዩናይትድ ተጫውቼ ዋንጫዎችን አንስቻለሁ። ለአገሬም ከአንድ መቶ በላይ ጨዋታዎችን ከማድረጌም በላይ በአምበልነት መርቻለሁ ። ለታላላቅ ክለቦች ተጫውቻለሁ። ይህ ለእኔ ከስኬትም በላይ ነው» ብሏል ስንብቱን ይፋ ባደረገበት መግለጫው።<br />
«በእግር ኳስ ተጫዋችነት ሕይወቴ ካከና ወንኳቸው ተግባራት ከምኮራባቸው ነገሮች አንዱ አገሬን በአምበልነት መምራት መቻሌ ነው። የሦስቱን አናብስት መለያ በመልበሴ ከታላላቆቹ ተጫዋቾች ተርታ ከመመደቤም በተጨማሪ አገራቸውን ለሚወዱ ደጋፊዎችም የኩራት ምንጭ ሆኛለሁ። በዚህም እድለኛ ነኝ  » ብሏል።<br />
ሰዎች ሜዳ ሲገባ ያለውን ሁሉ እንደሚሰጥ ጠንካራ እግር ኳሰኛ እንዲያየኝ እፈልጋለሁ ያለው ቤካም በተጫዋችንት ሕይወቱ የረዱትን ሁሉ አመስግኗል።<br />
የእንግሊዝ ዋና ከተማ የ2012 ኦሊምፒክ የአዘጋጅነት እድል እንድታገኝና እድሉን ካገኘች በኋላም በዝግጅቱ ወቅት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደረገውን የቤካምን ከእግር ኳስ ዓለም መገለል አስመልክቶ የአገሪቱን ጠቅላይ ሚኒስትር ዴቪድ ካሜሩንን ጨምሮ በርካታ ሰዎች አድናቆታቸውን ለተጫዋቹ በመግለጽ ላይ ይገኛሉ።<br />
ሰሞኑን ራሳቸውን ከእግር ኳስ ተጫዋችነት ማግለላቸውን ካስታወቁት መካከል  የሊቨርፑሉ የተከላካይ መስመር ተጫዋች ጂሚ ካራገር ይገኝበታል። የ35 ዓመቱ ካራገር ክለቡ ሊቨርፑል እሁድ ከኩዊንስ ፓርክ ሬንጀርስ ጋር ከሚያደርገው ጨዋታ ላይ ከተሳተፈ በኋላ ነው ሙሉ ለሙሉ ከጨዋታ ዓለም የሚገለለው።<br />
ካራገር በእግር ኳስ ተጫዋችነት በሊቨርፑል ባሳለፋቸው 16 ዓመታት ሁለት የኤፍኤ ፣ ሦስት የሊግ ፣ሁለት የኮሙኒቲ ሽልድና አንድ የሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫዎችን ቢያነሳም አንድም ጊዜ የፕሪሚየር ሊጉን ዋንጫ ሳያነሳ ከኳስ ተጫዋችነት መገለሉ  እንደሚቆጨው ተናግሯል።<br />
 « የፕሪሚየር ሊጉን ዋንጫ<br />
አላገኘሁም።ይህ ከፍተኛ ቁጭት ውስጥ እንድገባ አድርጎኛል » ብሏል።<br />
ሊቨርፑል 732 ጨዋታዎችን ያደረገው ካራገር ለክለቡ በርካታ ጨዋታዎችን በማድረግ ሁለተኛው ተጫዋች መሆን ችሏል።ለሊቨርፑል በርካታ ጨዋታዎችን በማድረግ ቀዳሚ የሆነው ያን ካላጋን ሲሆን ተጫዋቹ 857 ጊዜ የመርሲሳይዱን ክለብ መለያ አድርጎ ተጫውቷል።<br />
በቴሌቪዥን የእግር ኳስ ተንታኝ ሆኖ ለመስራት ዝግጅት በማድረግ ላይ የሚገኘው ካራገር « ጫማውን የመስቀል » ውሳኔ ላይ የደረሰው ከ12 ወራት በፊት እንደነበረም ገልጿል።<br />
እንግሊዛዊው የማንችስተር ዩናይትድ እግር ኳስ ክለብ የተከላካይ መስመር ተሰላፊ ሪዮ ፈርዲናንድ ራሱን ከብሔራዊ ቡድን ማግለሉን ይፋ አድርጓል።<br />
ለእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን 81 ጊዜ ተሰልፎ የተጫወተው የ38 ዓመቱ ፈርዲናንድ ከብሔራዊ ቡድኑ ራሱን ለማግለሉ በምክንያትነት የጠቀሰው ትኩረቱን ለክለቡ ለማድረግ በመፈለጉ መሆኑን ተናግሯል። እነዚህ ተጫዋቾች ጉዳይ የሰሞኑ የዓለም የመገናኛ ብዙኃን የፊት ገጽ ዜናና መነጋገሪያ ሆነውሰንብተዋል።</p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/776"     class="crp_title">የአውሮፓ ፉትቦል ፌዴሬሽን ድሮግባ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2614"     class="crp_title">አሥሩ ዋንጫዎች:- አሥሮቹ ጀግኖችና&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3204"     class="crp_title">ሰር አሌክስ ፈርጉሰን በቁጥሮች</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1866"     class="crp_title">ትውልደ ኢትዮጵያዊው በአርሰናል&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/233"     class="crp_title">ጆናታን ፒትሮይፓ የአፍሪካ ዋንጫ&hellip;</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=82962</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>የመለስ መታሰቢያ ተቋም (Foundation) – ክፍል 3 ከ 3</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3306</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3306#comments</comments>
		<pubDate>Sat, 18 May 2013 21:41:22 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3306</guid>
		<description><![CDATA[ግርማ ሞገስ (girmamoges1@gmail.com) የአቶ መለስን መሞት መንግስት ነሐሴ 15 ቀን 2004 ዓ.ም. ይፋ አደረገ። መንግስት ጥር 17 ቀን 2005 ዓ.ም. የመለስ ራዕይ እንዲቀጥል የኢትዮጵያ ህዝብ በሃዘን መግለጹን የሚያብራራ እና መታሰቢያ ተቋም የሚመሰረት ህግ አወጀ። የመለስ ዜናዊ መታሰቢያ ተቋም የገቢ ምንጭ የግል ለጋሾች፣ ገቢ ማስገኛ ፕሮግራሞች፣ የኢትዮጵያ መንግስት እና ሌሎች ምንጮች እንደሚሆኑ አዋጁ ጨምሮ አብራራ። መጋቢት [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2827">የአቶ መለስ መታሰቢያ ተቋም (Foundation)! </a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/22">ጂሃዳዊ እርምጃን በኢትዮጵያ ላይ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2811">ግርማዊነታቸው የአቡነ ጴጥሮስን&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1265">የኢህአዴግ መተካካት ፖለቲካ &#8211;&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/subscribe">Subscribe</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/azeb.jpg"><img src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/azeb.jpg" alt="azeb" width="271" height="294" class="alignleft size-full wp-image-3308" /></a> ግርማ ሞገስ (girmamoges1@gmail.com)<br />
የአቶ መለስን መሞት መንግስት ነሐሴ 15 ቀን 2004 ዓ.ም. ይፋ አደረገ። መንግስት ጥር 17 ቀን 2005 ዓ.ም. የመለስ ራዕይ እንዲቀጥል የኢትዮጵያ ህዝብ በሃዘን መግለጹን የሚያብራራ እና መታሰቢያ ተቋም የሚመሰረት ህግ አወጀ። የመለስ ዜናዊ መታሰቢያ ተቋም የገቢ ምንጭ የግል ለጋሾች፣ ገቢ ማስገኛ ፕሮግራሞች፣ የኢትዮጵያ መንግስት እና ሌሎች ምንጮች እንደሚሆኑ አዋጁ ጨምሮ አብራራ። መጋቢት 29 ቀን 2005 ዓ.ም. ደግሞ ህውሃት ‘የመታሰቢያ ተቋም መስራች ጉባኤ’ ተብሎ የሚጠራ ሌላ ድራማ በማዘጋጀት የኢትዮጵያ ህዝብ በአቶ መለስ ራዕይ ፍቅር መጠመዱን እና ይኽን ፍቅሩን በሃዘን መግለጹን የተለያዩ ተናጋሪዎች በጉባኤው እንዲያብራሩ አደረገ። የመታሰቢያ ተቋሙ ግቦች እና ተዛማጅ ጉዳዮችም ተነገሩ። በድርጅታዊ የሚስጢር አሰራር ቀደም ብሎ የተመረጡ የቦርድ አባላት በጉባኤው ላይ አንደ አዲስ ተመረጡ። ወ/ሮ አዜብም ፕሬዘዳንት ተደርጋ ተመረጠች። ‘መለስ እንደተሰዋ ሁሉ እኛም እስከምንሰዋ ድረስ ለመስራት ቃል እንገባለን‘ የሚል የደርግ አይነት መፈክር በማሰማት ምርጫውን መቀበሏን ገለጸች። ይኽ ድራማ የታየው በአፍሪካ ኅብረት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ውስጥ ነበር። ይሁንና አዜብ መስፍን በጉባኤው ላይ ‘እንደ መለስ እስከምንሰዋ ድረስ እንሰራለን’ ስትል ‘እስክንሞት ድረስ አምባገነናዊ አገዛዛችን ይቀጥላል’ ማለቷ ይመስላል። አምስት ነጥቦች አነሳለሁ።</p>
<iframe src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/plugins/google-document-embedder/view.php?url=http%3A%2F%2Fwww.zehabesha.com%2Famharic%2Fwp-content%2Fuploads%2F2013%2F05%2FFinal_Pic_YemelesMetasebiyaTequam-Part-3.pdf&hl=&gpid=1&embedded=true" class="gde-frame" style="width:100%; height:300px; border: none;" scrolling="no"></iframe>
<p class="gde-text"><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/Final_Pic_YemelesMetasebiyaTequam-Part-3.pdf" class="gde-link">Download (PDF, 107KB)</a></p>
<p><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2566">ክፍል 1ን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ</a></p>
<p><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2827">ክፍል 2ን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ</a></p>
<p><script type="text/javascript">// <![CDATA[
google_ad_client = "ca-pub-8555893555560582";
/* Post  336 x 280 */
google_ad_slot = "9157038725";
google_ad_width = 336;
google_ad_height = 280;
// ]]&gt;</script><br />
<script type="text/javascript" src="http://pagead2.googlesyndication.com/pagead/show_ads.js">// <![CDATA[</p>
<p>// ]]&gt;</script></p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2827"     class="crp_title">የአቶ መለስ መታሰቢያ ተቋም (Foundation)! </a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/22"     class="crp_title">ጂሃዳዊ እርምጃን በኢትዮጵያ ላይ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2811"     class="crp_title">ግርማዊነታቸው የአቡነ ጴጥሮስን&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1265"     class="crp_title">የኢህአዴግ መተካካት ፖለቲካ &#8211;&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/subscribe"     class="crp_title">Subscribe</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=82959</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>ታላቅ የተቃውሞ ሰልፍ በጀርመን በርሊን ከተማ ተካሄደ</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3303</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3303#comments</comments>
		<pubDate>Sat, 18 May 2013 21:31:34 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3303</guid>
		<description><![CDATA[ዘጋቢ በየነ መስፍን ከጀርመን እ.ኤ.አ በሜይ 14 ቀን 2013 ዓ.ም. በጀርመን በርሊን ከተማ የኢትዮጵያውያን የፖለቲካና ሲቪክ ማህበር አባላት አንድነት ድርጅት (ኢ.ፕ.ኮ.) በጠራው ታላቅ የተቃውሞ ሰልፍ ላይ ከተለያዩ የጀርመን ከተሞች የተሰባሰቡ ቁጥራቸው ከ350 በላይ የሆኑ ኢትዮጵያውያን፣ትውልደ-ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች የተገኙ ሲሆን የኢትዮጵያ ህዝብ አንድነት ፓርቲ /ኢሕአፓ/፣የሞረሽ ወገኔ የአማራ ድርጅት /ሞረሽ/ እና የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር አመራር እና [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/767">በጀርመን የወያኔን አምባገነን&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2165">የኢሕአግ ሰራዊት በዋልድባ ወታደራዊ</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1535">አንድነት በህሊና እስረኞች ላይ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1073">የፊታችን አርብ ኢትዮጵያውያን&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1733">በአማሮች ላይ የሚደረገውን&#8230;</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p>ዘጋቢ በየነ መስፍን ከጀርመን</p>
<p>እ.ኤ.አ በሜይ 14 ቀን 2013 ዓ.ም. በጀርመን በርሊን ከተማ የኢትዮጵያውያን የፖለቲካና ሲቪክ ማህበር አባላት አንድነት ድርጅት (ኢ.ፕ.ኮ.) በጠራው ታላቅ የተቃውሞ ሰልፍ ላይ ከተለያዩ የጀርመን ከተሞች የተሰባሰቡ ቁጥራቸው ከ350 በላይ የሆኑ ኢትዮጵያውያን፣ትውልደ-ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች የተገኙ ሲሆን የኢትዮጵያ ህዝብ አንድነት ፓርቲ /ኢሕአፓ/፣የሞረሽ ወገኔ የአማራ ድርጅት /ሞረሽ/ እና የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር አመራር እና አባላትም በሰልፉ ላይ ተገኝተዋል።<br />
<a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/germeney-demonstation-ethiopians.jpg"><img src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/germeney-demonstation-ethiopians.jpg" alt="germeney demonstation ethiopians" width="500" height="407" class="alignnone size-full wp-image-3304" /></a><br />
መነሻውን &#8221;ቬንደርሸር ማርክት አንድ&#8221; /Werderscher Markt 1/ ከሚባለው የከተማው ክፍል በማድረግ በተለያዩ መፈክሮችና የኢትዮጵያ ባንድራ በማሸብረቅ ጉዞውን ወደ ቻንስለር አንጌላ ሜርክል ጽ/ቤት አድርጓል።<br />
&#8221;በአማራ ህዝብ ላይ የሚደረገው የዘር ማጥራት ዘመቻ ይቁም!&#8221;<br />
&#8221;የህሊና እስረኞች ይፈቱ!&#8221;<br />
&#8221;የሃይማኖት ነፃነት ይከበር!&#8221;<br />
&#8221;ከአባይ በፊት ዘረኝነት ይገደብ!&#8221;<br />
&#8221;የጀርመን መንግስትና የአውሮፓ ህብረት ለአፋኙ የወያኔ አገዛዝ የሚያደርጉትን የገንዘብ ድጋፍ ያቁሙ!&#8221;<br />
&#8221;ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ይከበር!&#8221; የሚሉ መፈክሮች በሰፊው የተደመጡ ሲሆን ከአንድ ሰዓት ተኩል የእግር ጉዞ በኋላ ተሰላፊው በመጀመሪያ በጀርመን ፓርላማ /Bundestag/ ፊት ለፊት በኋላም በጀርመን ቻንስለር ጽ/ቤት ፊት ለፊት በመሰባሰብ የተለያዩ መፈክሮችን ያሰማ ሲሆን ከአንድ ወር በፊት በኢ.ፕ.ኮ. አማካኝነት በአማራ ተወላጆች ላይ የደረሰውን የዘር ማጥራት ወንጀል የሚቃወሙ ቁጥራቸው ከሶስት ሺህ በላይ የሚሆኑ ጀርመናውያንን ፊርማ የያዘውን ሰነድ ለቻንስለሯ ጽ/ቤት ገቢ የተደረገ ሲሆን የኢ.ፕ.ኮ. ሊቀ መንበር፣እንዲሁም የኢሕአፓ ተወካይ፣የሞረሽ እና የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ተወካዮች አጠር ያለ ንግግር ያደረጉ ሲሆን ይህ ከሶስት ሰዓት በላይ የፈጀ የተቃውሞ ሰልፍ በሠላምና በታላቅ ድምቀት ተጠናቋል።</p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/767"     class="crp_title">በጀርመን የወያኔን አምባገነን&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2165"     class="crp_title">የኢሕአግ ሰራዊት በዋልድባ ወታደራዊ</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1535"     class="crp_title">አንድነት በህሊና እስረኞች ላይ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1073"     class="crp_title">የፊታችን አርብ ኢትዮጵያውያን&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1733"     class="crp_title">በአማሮች ላይ የሚደረገውን&hellip;</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=82960</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>የመምህራን ማኅበር በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆችና ተቋማት መዳከም ዙሪያ ስጋቱን የሚገልጽ መግለጫ አወጣ</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3298</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3298#comments</comments>
		<pubDate>Sat, 18 May 2013 12:46:02 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3298</guid>
		<description><![CDATA[(ዘ-ሐበሻ) በስደት የሚገኘው የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር አባላት አስተባባሪ ኮሚቴ &#8220;የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጆችና ተቋማት&#8221; የውድቀት አደጋ አንዣቦባቸዋል ሲል ስጋቱን ገለጸ። ማህበሩ ለዘ-ሐበሻ በላከው መግለጫው &#8220;በመምህራን ላይ የሚታየው የ እውቀትና የክህሎት ክፍተት ለመሙላት አጫጭር ስልጠናዎችንና የክረምት ኮርሶች ቢሰጡም የትምህርቱ ጥራት ዋነኛ መመዘኛ መስፈርት የፖለቲካ ታማኝነት የሚለው ስንኩል የወያኔ አስተሳሰብ ገኖ በመውጣቱ በርካታ ልምድ ያላቸው መምህራን [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/20">በሰደት የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/767">በጀርመን የወያኔን አምባገነን&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/358">ባለራዕይ ወጣቶች ማህበር በመንግስት</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/183">ኦነግ የሙስሊሙን ጥያቄ በሸፍጥ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1840">የትግራይ መምህራን እሮሯቸውን&#8230;</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/ethiopian-teachers.jpg"><img src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/ethiopian-teachers-1024x221.jpg" alt="ethiopian teachers" width="500" height="121" class="alignleft size-large wp-image-3300" /></a><br />
(ዘ-ሐበሻ) በስደት የሚገኘው የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር አባላት አስተባባሪ ኮሚቴ &#8220;የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጆችና ተቋማት&#8221; የውድቀት አደጋ አንዣቦባቸዋል ሲል ስጋቱን ገለጸ። ማህበሩ ለዘ-ሐበሻ በላከው መግለጫው &#8220;በመምህራን ላይ የሚታየው የ እውቀትና የክህሎት ክፍተት ለመሙላት አጫጭር ስልጠናዎችንና የክረምት ኮርሶች ቢሰጡም የትምህርቱ ጥራት ዋነኛ መመዘኛ መስፈርት የፖለቲካ ታማኝነት የሚለው ስንኩል የወያኔ አስተሳሰብ ገኖ በመውጣቱ በርካታ ልምድ ያላቸው መምህራን ሥራቸውን እያለቀቁ መሄዳቸው የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆችና ተቋማት በአሁኑ ጊዜ ይበልጥ ተዳክመዋል&#8221; ብሏል።</p>
<iframe src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/plugins/google-document-embedder/view.php?url=http%3A%2F%2Fwww.zehabesha.com%2Famharic%2Fwp-content%2Fuploads%2F2013%2F05%2FETA-Press-Release-2005-1.pdf&hl=&gpid=1&embedded=true" class="gde-frame" style="width:100%; height:300px; border: none;" scrolling="no"></iframe>
<p class="gde-text"><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/ETA-Press-Release-2005-1.pdf" class="gde-link">Download (PDF, 621KB)</a></p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/20"     class="crp_title">በሰደት የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/767"     class="crp_title">በጀርመን የወያኔን አምባገነን&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/358"     class="crp_title">ባለራዕይ ወጣቶች ማህበር በመንግስት</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/183"     class="crp_title">ኦነግ የሙስሊሙን ጥያቄ በሸፍጥ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1840"     class="crp_title">የትግራይ መምህራን እሮሯቸውን&hellip;</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=82794</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>ጠ/ቤተ ክህነት የመምህር ግርማ ወንድሙን እገዳ አጸና</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3294</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3294#comments</comments>
		<pubDate>Fri, 17 May 2013 22:14:49 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3294</guid>
		<description><![CDATA[ዘ-ሐበሻ ከጥቂት ሳምንታት በፊት መምህር ግርማ ወንድሙ በደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤ/ክ እንዳያጠምቁ መታገዳቸውን መዘገቧ ይታወሳል። ዛሬ ከአዲስ አበባ የደረሰን ዜና እንደሚያመለክተው ደግሞ አዲስ አበባ የሚገኘው ጠቅላይ ቤተ ክህነት የአጥማቂውን እግድ እንዳጸና ገልጿል። በአነጋጋሪነታቸው የቀጠሉት መምህር ግርማ እንዳያጠምቁ መታገዳቸው ከተሰማ በኋላ ም ዕመናን የተለያዩ አስተያየቶችን ሲሰነዝሩ ቆይተዋል። ጠ/ቤተክህነቱ ግንቦት 2 ቀን 2005 ለ:- - ለቅዱስ [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3059">በቅዱስ እስጢፋኖስ ቤ/ክ ሲያጠምቁ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/683">የ5ቱ እጩ ፓትርያርክ ማንነት በጥቂቱ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/241">ኮሚቴው የፓትርያሪክ ምርጫ ሕገ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/669">በገለልተኝነት የቆየችው የኖርዝ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/493">ስለ መንበረ ፕትርክናው ዕጩዎች&#8230;</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/girma1.jpg"><img src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/girma1.jpg" alt="girma1" width="314" height="448" class="alignleft size-full wp-image-3295" /></a> ዘ-ሐበሻ ከጥቂት ሳምንታት በፊት መምህር ግርማ ወንድሙ በደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤ/ክ እንዳያጠምቁ መታገዳቸውን መዘገቧ ይታወሳል። ዛሬ ከአዲስ አበባ የደረሰን ዜና እንደሚያመለክተው ደግሞ አዲስ አበባ የሚገኘው ጠቅላይ ቤተ ክህነት የአጥማቂውን እግድ እንዳጸና ገልጿል። በአነጋጋሪነታቸው የቀጠሉት መምህር ግርማ እንዳያጠምቁ መታገዳቸው ከተሰማ በኋላ ም ዕመናን የተለያዩ አስተያየቶችን ሲሰነዝሩ ቆይተዋል።<br />
ጠ/ቤተክህነቱ  ግንቦት 2 ቀን 2005 ለ:-<br />
<a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/015.jpg"><img src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/015-150x150.jpg" alt="በቅዱስ እስጢፋኖስ ቤ/ክ ሲያጠምቁ የከረሙት አነጋጋሪው መ/ር ግርማ ወንድሙ እንዳያጠምቁ ታገዱ" width="150" height="150" class="alignleft size-thumbnail wp-image-3064" /></a>- ለቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት<br />
- ለብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪክ ልዩ ጽ/ቤት<br />
- ለአስተዳደር መምሪያ<br />
- ለሕዝብ ግንኙነት መምሪያ<br />
- ለምሥራቅ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት<br />
- ለፌዴራል ጉዳዮች ጽ/ቤት<br />
- ለፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን<br />
- ለብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት<br />
- ለአ/አ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሽን<br />
- ለቂርቆስ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ<br />
- ለአ/አ አስተዳደር ፍትሕ ቢሮ<br />
- ለቂርቆስ ክ/ከ ፍትሕ ጽ/ቤት<br />
ግልባጭ አድርጎ በጻፈው የእግዳ ማጽኛ ደብዳቤ ላይ መምህሩን &#8220;አጥማቂ ነኝ ባይ&#8221; ሲል ገልጿቸዋል።  ደብዳቤውን እንደወረደ ያንብቡት።</p>
<p>ጉዳዩ፡- በአስቸኳይ አጥማቂ መምህር ግርማ ወንድሙ በደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን ሰ/ጉ/ጽ/ቤት በቁጥር 339/ቀ/አ/ቤ/ክ በ28/8/2005 ዓ.ም የተሰጠው እገዳ መ/ፓ/ጠ/ጽ/ቤት ያጸናው ስለመኾኑ ይመለከታል፤</p>
<p>መ/ር ግርማ ወንድሙ ሰባኬ ወንጌልና አጥማቂ ነኝ፤ የማዳን ፈውስ አለኝ በማለት በሕገ ወጥ መንገድ እስከ አሁን ድረስ በደብሩ እያጠመቁ ይገኛሉ፡፡</p>
<p>ይኹንና በቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ከ1993 ዓ.ም እስከ 2002 ዓ.ም ድረስ በየወቅቱ በሕገ ወጥ መንገድ የማዳን ፈውስ አለኝ በማለት ሕዝበ ክርስቲያኑን በየደብሩ ቅጽር ግቢ በማሰባሰብ የሚያጠምቁትን በተመለከተ ውሳኔ አስተላልፏል፡፡</p>
<p>ከቤተ ክርስቲያኗ ቀኖና ሥርዐት ውጭ በሚፈጸም ስብከትና ጥምቀት፤<br />
የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ሳይፈቅዱ የሚሰጥ የወንጌልና ጥምቀት አገልግሎት መስጠትን በተመለከተ ቅዱስ ሲኖዶስ የወሰነ ቢኾንም በሥርዐተ አልበኝነት በተለያዩ ቦታዎች የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ሲጣስ ይታያል፡፡<br />
በመኾኑም መምህር ግርማ ወንድሙ በደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን ቅጥር ግቢ ውስጥ በሕገ ወጥ መንገድ የሚፈጽሙት ሕገ ወጥ የማጥመቅ ሥርዐትና የወንጌል አገልግሎት መኾኑን እየገለጽን የእምነታችን ተከታይ ሕዝበ ክርስቲያኑ ከዚህ እግድ ጋራ በተያያዘ የጸጥታ ችግር እንዳይገጥመው የሰበካ ጉባኤ ጽ/ቤት ጥብቅ ክትትል በማድረግ ውሳኔውን ተግባራዊ እንዲያደርግ እያሳሰብን የሚመለከታቸው የመንግሥት የጸጥታ አካላትም የቤተ ክርስቲያኒቱን ውሳኔ ተግባራዊ በማድረግ ረገድ አስፈላጊው ትብብር እንዲያደርጉልን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡</p>
<p>ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን:: </p>
<p><iframe width="500" height="380" src="http://www.youtube.com/embed/UwYQqime9nc" frameborder="0" allowfullscreen></iframe></p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3059"     class="crp_title">በቅዱስ እስጢፋኖስ ቤ/ክ ሲያጠምቁ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/683"     class="crp_title">የ5ቱ እጩ ፓትርያርክ ማንነት በጥቂቱ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/241"     class="crp_title">ኮሚቴው የፓትርያሪክ ምርጫ ሕገ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/669"     class="crp_title">በገለልተኝነት የቆየችው የኖርዝ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/493"     class="crp_title">ስለ መንበረ ፕትርክናው ዕጩዎች&hellip;</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=82732</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>ሰውየው (ክፍልሁለት) ከይገርማል ታሪኩ</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3281</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3281#comments</comments>
		<pubDate>Thu, 16 May 2013 19:21:25 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3281</guid>
		<description><![CDATA[ከይገርማል ታሪኩ ሻለቃ ሀይለየሱስ እጅጉ መዐሕድን  ሲቀላቀሉ ድርጅቱ በአማራው ክልል እግሩን አልሰደደም ነበር:: ችግሩ ፋታ የሚሰጥ አይደለም:: አማሮች ካለአለሁ ባይ: ካለአይዟችሁ ባይ እየተጨፈጨፉ ነው:: በቀልን ሰንቆ ከበረሀ የተነሳውና ስልጣኑን ሙሉ በሙሉ በእጁ ያደረገው ወያኔ ሀላፊነት በጎደለው የጭካኔ ተግባር በአማራው ህዝብ ላይ ሽብር ነዛ- ሞት አወጀ:: መዐሕድን በሁለት እግሩ እንዲቆም ለማድረግ በሰውሀይል ማጠናከር ያስፈልጋል:: ህዝብን የማደራጀትና [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3162">ሰውየው &#8211; ክፍል 1</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1163">ሰላማዊ ትግል እና ኢትዮጵያውያን&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3164">የኢትዮጵያ ወጣቶች ብሄራዊ ንቅናቄ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3018">በእውነት ኢትዮጵያን እንመራለን&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1138">አገር ቤት ያሉ ተቃዋሚዎች&#8230;</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p style="text-align: left;" align="center"><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/03/Pen-4.jpg"><br />
</a><strong>ከይገርማል ታሪኩ</strong></p>
<p style="text-align: left;" align="center"><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/03/Pen-4.jpg"><img class="alignleft" alt="Pen-4" src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/03/Pen-4-150x150.jpg" width="150" height="150" /></a>ሻለቃ ሀይለየሱስ እጅጉ መዐሕድን  ሲቀላቀሉ ድርጅቱ በአማራው ክልል እግሩን አልሰደደም ነበር:: ችግሩ ፋታ የሚሰጥ አይደለም:: አማሮች ካለአለሁ ባይ: ካለአይዟችሁ ባይ እየተጨፈጨፉ ነው:: በቀልን ሰንቆ ከበረሀ የተነሳውና ስልጣኑን ሙሉ በሙሉ በእጁ ያደረገው ወያኔ ሀላፊነት በጎደለው የጭካኔ ተግባር በአማራው ህዝብ ላይ ሽብር ነዛ- ሞት አወጀ:: መዐሕድን በሁለት እግሩ እንዲቆም ለማድረግ በሰውሀይል ማጠናከር ያስፈልጋል:: ህዝብን የማደራጀትና የማንቃት ስራ ገንዘብ ያስፈልገዋል:: የወገን ጩኸት ያባነናቸው አማሮች በከተሞች አካባቢ በቁጭት ድርጅቱን ለማጠናከር ደፋ ቀና ማለት ጀመሩ::</p>
<p>ብዙሀኑ ገበሬ ምን እየተደረገ እንደሆነ እንኳ አያውቅም:: መንግስት ይመጣል መንግስት ይሄዳል:: &#8220;ሽህ ቢታለብ ያው በገሌ&#8221; እንዳለችው ድመት ማንም መጣ ማን ያው አርሶ አደር ነውና ሁሉም የእለት ጉርሱን የአመት ልብሱን ያሟላ ዘንድ ደፋ ቀና ይላል:: ሌሊት ወጥቶ ሌሊት ይገባል:: ጠብ ለማይል ኑሮ ነጋ ጠባ ደፋ ቀና እንዳለ ይኖራል:: ወሬ የሚያዳምጥበት ጊዜ የለውም:: ብቻ ይሰራል- ሰርቶ ከሚያገኘው ይገብራል:: ገበሬው የሚፈቀደው የግብር ጊዜ ወይም የተለየ መዋጮ እንዲያደርግ ሲፈለግ: አሊያም ለውትድርና:: ከዚያ ውጭ የት ወደቀ የሚለው የለም:: እርሱም የቤቱን ገበና ለመሸፈን ላይ ታች ከማለት ውጪ ስለፖለቲካ የሚያውቀው ነገር የለውም:: መንግስት- አስተዳዳሪ: የህዝብን ሰላም የሀገርን ዳር ድንበር አስጠባቂ: መሰረት ልማት (መንገድ: አስኳላ ትምህርት: የጤና ተቋም&#8230;) አስፋፊ መሆኑን ያውቃል::  የመንግስት ዘር መኖሩን ግን አያውቅም:: አንዱን ህዝብ ጎድቶ ሌላውን ለመጥቀም እንደሚያልምም አያውቅም:: በርግጥ በዘር ወይም በቀረቤታ የሚሰሩ ባለስልጣኖች እንደነበሩ: አሁንም እንደማይጠፉ ያውቃል:: የማያውቀው ነገር ቢኖር መንግስት ለአንዱ ወላጅ አባት ለሌላው ደግሞ የእንጀራ አባት መሆን ስለመቻሉ ነው::</p>
<p>&nbsp;</p>
<p>ከተሜው የገበሬውን ያህል ለፖለቲካ ሩቅ አይደለም:: ለሚዲያወች የተሻለ ቀረቤታ ስላለው ምን እየተካሄደ እንዳለ መጠነኛም ቢሆን ግንዛቤው አለው:: ስለዚህ ይህንን የህብረተሰብ ክፍል ማደራጀት ብዙም አይከብድም:: ግን እንዴት? ሰላምና መረጋጋት ብሎ መንግስት ያደራጃቸውና የኮር አባል ተብለው የሚታወቁት ምልምል ካድሬወች ህዝቡን ሰላሙን ነሱት:: በኮር አባላት ስብሰባ ላይ የመጀመሪያው ክፍል ኢንፎርሜሽን ማቀበል ነው:: ስለዚህ የኮር አባላቱ አይደለም የሚወራውን የሚበላውንና የሚጠጣውን ሳይቀር እያነሱ እገሌ እንዲህ አለ: እገሊት ከገሊት ቤት ቡና ጠጣች በማለት በየተሰጣቸው ቀጠና ያዩትንና የሰሙትን እያጋነኑ ያቀርቡ ጀመር:: ኢንፎርሜሽን ያላመጣ የኮር አባል ስለሚገመገም ግምገማውን ለማለፍ አይደለም የታየውና የተሰማው ያልታየና ያልተደረገው ሁሉ በንጹሀን ላይ መወራት ጀመረ:: የኮር አባላቱ በግላጭ አይታወቁ ስለነበር አንዱ አንዱን ማመን እየከበደው መጣ:: ፍርሀትና ጥርጣሬ ነገሰ:: የመንግስትን ፖሊሲ ይነቅፋሉ የተባሉ ሰዎች የተነፈሱት ሳይቀር እየተነገራቸው ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ ምክርና ማስፈራሪ ይሰጣቸው ጀመር:: ምክርና ማስጠንቀቂያውን የጣሱ ሰዎች ሰርቀው ሊያመልጡ ሲሉ ተገደሉ: ወይም መጠጥ ቤት በተነሳ ግጭት ክፉኛ ተደብድበው ሞቱ: ወይም ባላንጣ ጊዜ ጠብቆ ገደላቸው እየተባሉ ተወገዱ:: የደርግ የቀይ ሽብር በድብቅ መተግበር ጀመረ:: ይህን ዘመን ለማለፍ ከተሜው ኮረንቲና ፖለቲካን በሩቁ አለ::</p>
<p>&nbsp;</p>
<p>ድርጅት ለመመስረት የሚደረገው ትግል ግን በምንም መልኩ ሊደናቀፍ አይችልም:: መከፈል የሚያስፈልገው መስዋእትነት ተከፍሎ መዐሕድ እውን መሆን አለበት:: ድርጅቱ ስር እስኪሰድ ድረስ ለየት ያለ አካሄድ መከተል እንደሚገባ በመታመኑ በአንዳንድ አካባቢ ዱሮ በኢሕአፓ ጊዜ በነበረው የአደረጃጀት ስርአት መሰረት እምነት የሚጣልባቸውን በተለይ ደግሞ በዚህ መንግስት ደስተኛ ያልሆኑትን ሰዎች ሁለትና ሶስት በአንድ ላይ በማደራጀት ግንዛቤ ማስጨበጥና የአባልነት ፎርም ማስሞላት ተጀመረ:: በዚህ መልክ ውስጥ ውስጡን መዐሕድ ስር መስደድ ጀመረ:: በርግጥ የመጣውን ሁሉ በጸጋ ለመቀበል የግንባር ስጋ ሆነው ፈጥጠው የወጡ በርካታ ሰዎች ነበሩ:: መዐሕድ የሰላም ታጋይ ድርጅት ነው:: ሰላማዊ ትግል ማለት ቅሬታን ሰላማዊ በሆነ መንገድ መግለጽ ማለት ነው:: ቅሬታ መፍትሄ ካላስገኘ ትግሉ በመንፈስና በአካል እስከመሸፈት ያደርሳል:: ይህም ማለት ከሀይል ርምጃ በመለስ ያሉትን ሁሉ መጠቀም: እምቢ አልታዘዝም አላደርግም በማለት ተቃውሞን መግለጽን ያጠቃልላል:: አዎ! ሰላማዊ ትግል ማለት ከመንግስት በኩል የሚሰነዘረውን ማንኛውም ጥቃት በሰላም መቀበል ማለት ነው:: ሳያቆስሉና ሳይገድሉ እየቆሰሉና እየሞቱ ማሸነፍ ማለት ነው:: ይህ የትግል ባህሪ በለየላቸው የወያኔ አይነት አምባገነን መንግስታት ዘንድ በእጅጉ ጎጅ ነው:: የህዝብ እምቢ ማለት አያስደነግጣቸውም:: ራሳቸውን መለስ ብለው ለመመርመር አያስችላቸውም:: ይልቁኑ በተደፈርኩ መንፈስ ያወራጫቸዋል:: ለበቀል ጦራቸውን ይሰብቁና ያገኙትን ሁሉ ማጥቃት ይጀምራሉ:: በዚህ መልኩ ሰላማዊ ትግል መስዋእትነቱን ያከፋዋል:: ኋላቀር በሆኑ አምባገነኖች በሚመሯቸው አገሮች ዘንድ ሰላማዊ ትግል የሽምቅ ውጊያ ያህል ያስቀጣል:: ሰላማዊ ታጋይ ማለት ለመንግስት አመራር አልመችም የሚል አጉራ ዘለል ነውና የሸማቂውን ያህል ይቀጣል:: አምባገነኖች አይደለም የተቃወማቸውን ኮከባቸው ያልፈቀደውን ሰው ሁሉ ቢገሉ ይችላሉ:: ወያኔወች ደግሞ ሰላማዊ ታጋይ ያውም የአማራ ማየት ቀርቶ መስማትም አይፈልጉም:: ሆኖም በአግባቡ ከተጠቀሙበት ሰላማዊ ትግል በአጭር ጊዜ ውጤታማ ያደርጋል:: ውጤታማነት ከጠንካራ አደረጃጀትና ከበሳል አመራር ውጭ አይገኝም:: መዐሕድ አመሰራረቱ ለፖለቲካ የስልጣን ፉክክር አይደለም:: አላማው በአማራው ላይ እየደረሰ ያለውን ዘርፈ ብዙ ጭቆናና ግድያ ለአለም መንግስታትና ለሰብአዊ ድርጅቶች ለማሰማት ነው:: ግን ሁሉም ትግል ያስፈልገዋል:: በዚህ ሂደት ወያኔ መራሹ መንግስት መውደቅ ከቻለ እሰየው ነው- በደምና በአጥንት የሚያምኑት እኩዮች ከጠፉ አማራውን ለይቶ የሚያሳድድ አይኖርም ማለት ነው:: ከዚያ በኋላ ለኢትዮጵያ የሚበጅ የህዝብ አስተዳደር ለመመስረት ተፎካካሪ ሆኖ መቅረብ ይቻላል:: ለሁሉም የህዝብን መንፈስ መማረክ የሚያስችል ሁለንተናዊ ብቃት መጎናጸፍ ያስፈልጋል::</p>
<p>&nbsp;</p>
<p>የልጆች ማስፈራሪያ &#8220;አባ ዳውሎ&#8221; ተብሎ ይጠራል:: አባ ዳውሎን አይቶ የሚያውቅ ልጅ የለም:: ግን አባ ዳውሎን ይፈራል:: ሲያለቅስ የነበረን ልጅ &#8220;አባ ዳውሎ መጣብህ&#8221; ካሉት ልቅሶውን ይውጣል:: ሻእቢያና ወያኔ ደግሞ ብሄር ብሄረሰቦችንና ህዝቦችን የሚያስፈራሩት &#8220;አማራ መጣልህ&#8221; ብለው ነው:: በሻእቢያና በወያኔ የተሰበከ የዋህ ይህንን ተቀብሎ አስተጋብቷል:: በኤርትራ እናቶች ልጆቻቸው ሲያስቸግሯቸው &#8220;አማራ መጣልህ&#8221; ይሏቸው ነበር:: አማራ አፉ እንደአዞ አፍ 180 ዲግሪ የሚዘረጋ ጆሮው እንደዝሆን የሰፋ: አስፈሪ የሆነ ፍጡር እንደሆነ ተደርጎ እየተነገራቸው ያደጉት ልጆች ታዲያ አማራ መጣብህ ሲባሉ ቱር ብለው የትም ይጠፋሉ- እናቶችም ከህጻናቱ ብጥበጣ ተንፈስ ይላሉ:: ይህ በኤርትራ የልጆች ማስፈራሪያ የነበረው አማራ አሁን ከልጆች አልፎ የብሄር ብሄረሰቦች ማስፈራሪያ ሆኗል:: &#8220;ነፍጠኛ&#8221; የአማራ ተለዋጭ ስም ነው:: እና ነፍጠኞች ከተባለ አማሮች ማለት ነው:: &#8220;ነፍጠኞች የብሄር ብሄረሰቦች ጠላቶች ናቸው- ኢትዮጵያ ደግሞ እስር ቤታቸው:: ነፍጠኞች አንገታቸውን ቀና ሊያደርጉ አይገባም:: አንገታቸውን ቀና ካደረጉ መሬትህን ይወስዳሉ: ነጻነትህን ይነጥቃሉ&#8221; ነቅተህ ጠብቅ ተብለው ይቀሰቀሳሉ:: የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦች አማሮችን ጠንቅቀው ያውቋቸዋል:: አማሮች በያሉበት ላባቸውን አንጠፍጥፈው ሰርተው የሚኖሩ እንደሆኑ አሳምረው ያውቃሉ:: አሁን አማራ ክልል ተብሎ በሚታወቀው ክልል የሚኖሩ አማሮችም ቢሆኑ የእግር ጫማ እንኳ የሌላቸው ለፍቶ አዳሪወች መሆናቸውን ይረዳሉ:: አማሮች ጠላቶቻችሁ ናቸው ሲባሉ ግራ ተጋብተዋል:: የትኞች አማሮች ናቸው የእኛ ጠላቶች ብለው መጠየቅ አይችሉም:: እንዲህ ያለ ሰው &#8220;የነፍጠኛ ሎሌ&#8221; ሊባል ይችላል:: አማሮች በየቦታው ሲታደኑ ብሄር ብሄረሰቦች ውስጣቸው በሀዘን ተኮማትሯል:: በየቦታው ተበትነው ባሉት አማሮች ላይ ጥቃት ለመፈጸም በወያኔና በአጋሮቹ ከተዘጋጁት ገዳይ ስኳዶች ግን ሊታደጓቸው አልቻሉም:: እና የብሄር ብሄረሰቦች አባ ዳውሎ (አማራ) ዘሩ እንዳይጠፋ ተደራጅቶ ድምጽን ከፍ አድርጎ መጮህ: ቀሪውን ወንድም ኢትዮጵያዊ ሀቁን ማስጨበጥና የትግል አጋር ማድረግ ያስፈልጋል::</p>
<p>&nbsp;</p>
<p>ሻለቃ ሀይለየሱስ በባህርዳር ልዩ ዞንና በምእራብ ጎጃም ዞን ከፍተኛ ሀላፊነት ተጥሎባቸዋል:: አባላትን መመልመል: ማደራጀት: የአባላት መዋጮ ማሰባሰብና ቢሮ መክፈት ይኖርባቸዋል:: ሰው የመቅረብ ልዩ ችሎታቸው ወሳኝ የሆኑ ሰዎችን ለማግኘት ረድቷቸዋል:: በጥቂት ወራቶች ውስጥ ምእራብ ጎጃምን እስከቀበሌ ድረስ ወርደው ማደራጀት ቻሉ:: ቢሮወች በበርካታ የወረዳ ከተሞች ተከፈቱ:: ቀስ በቀስ የህቡእ እንቅስቃሴው ገሀድ መውጣት ጀመረ:: የባህር ዳር ቢሮ በማእከልነት ያገለግል ጀመር:: ምንም እንኳ ሀይለየሱስ የምእራብ ጎጃምና የባህርዳር ልዩ ዞን አስተባባሪ ቢሆኑም በክልሉ ዋና ከተማ ተቀማጭ ስለሆኑ የአማራውን ችግር ከየዞኖች እየተቀበሉ ለበላይ የማሳወቅ ስራ በመስራት: መግለጫ በማውጣትና ህዝባዊ ስብሰባወችን በማካሄድ ግዙፍ ስራ ሰርተዋል:: በሰሜን ጎንደር: በደቡብ ጎንደር: በአዊና በምስራቅ ጎጃም ዞኖች ከአቶ አባይነህ ብርሀኑ ጋር በመሆን የዞን አስተባባሪወችን መልምለዋል- ቢሮወችን ከፍተዋል::</p>
<p>&nbsp;</p>
<p>የት ይደርሳሉ ብለው በንቀት ይመለከቷቸው የነበሩ የየደረጃው የወያኔ አንጋቾች ህዝቡ ቀስ በቀስ ከእጃቸው እያፈተለከ ወደ መዐሕድ እቅፍ መሰባሰቡን ሲያዩ መበራገግ ጀመሩ:: በሻለቃ ላይ ፈተናወች በዙ:: መጀመሪያ ምክር ቢጤ ተሰጣቸው:: &#8220;ምንህ ተነካ- ለምን አርፈህ አትቀመጥም&#8221; ተባሉ:: ቀጠሉ የወያኔ ተስፈኞች- &#8221; ብታርፍ ይሻልሀል:: አሊያ አወዳደቅህ ይከፋል&#8221; አሏቸው:: አልገባቸውም እንጅ ሀይለየሱስ አይደለም ለዛቻ ለጥይትም አይንበረከኩ:: ይህን ትግል ሲቀላቀሉ ብዙ ነገር ሊደርስባቸው እንደሚችል ተረድተው ነው የወሰኑት:: እና ሀይለየሱስ ይበልጥ ቀበቷቸውን ጠበቅ አድርገው ህዝብ የማደራጀቱን ስራ ገፉበት:: ፖሊሶችና የደህንነት ሀይሎች በየሄዱበት ይከታተሏቸዋል:: ሻለቃ ክፉ አይወጣቸውም:: ብቻ &#8220;እንዲያው ልፉ ብሏችሁ እኮ ነው&#8221; ይላሉ: ምንም ስህተት እንደማይገኝባቸው ለመግለጽ::</p>
<p>&nbsp;</p>
<p>&#8220;ማሸማቀቅ&#8221; የወያኔ አንዱ የትግል ስልት ነው:: አንድ ሰው ከሚፈጽመው ተግባር እንዲታቀብ ለማድረግ ሲፈለግ በስብሰባ ላይ የማስደንገጥ: በፖሊስና በደህንነት ክትትል የማስበርገግ ድርጊት ነው- ማሸማቀቅ:: ይህ ግን ሀይለየሱስ ዘንድ ሊሰራ አልቻለም:: ራሳቸው ሀይለየሱስም ሆኑ ቤተሰቦቻቸው በሌሉበት ቤታቸው በተደጋጋሚ ተፈትሿል:: ምን ይገኝባቸዋል? ምንም:: እርሳቸው እንደሆኑ የሰላም አርበኛ::</p>
<p>&nbsp;</p>
<p>ወያኔ መዐሕድን ለማጥቃት ሲንቀሳቀስ ብአዴኖች ግዳይ ጥለው ሊሾሙ ሊሸለሙ ተቁነጠነጡ:: በወቅቱ የተከሰቱ ችግሮች ሁሉ የመዐሕድ አፍራሽ እንቅስቃሴ ውጤቶች ተደርገው በመንግስት ሜዲያወች ይናፈሱ ጀመር:: መዐሕድ &#8220;ካለወቅቱ የመጣው ዝናብ በእኛ እንዳይሳበብ እየሰጋን ነው&#8221; ሲል ወያኔ እየፈጠረበት ያለውን ልብ ወለድ ክስ ነቀፈ:: ወያኔ ግን ሰቅጠጥም አላለ:: ይባስ ብሎ በፈጠራ ክስ የድርጅቱን መስራችና የአማራ ጠበቃ የነበሩትን ፕሮፌሰር አስራት ወ/የስን አሰረ:: የወያኔ አላማ መሪው ከጨዋታ ውጪ ከሆነ ተከታዩ ይበተናል የሚል የተሳሳተ አላማ ነበር:: ያ ዱሮ ቀረ:: ዱሮ የጦር መሪ ሲሞት ሰራዊቱ ትጥቁን ይፈታ ነበር አሉ:: &#8220;ንጉስህ ወይም መሪህ ተማርኳልና እጅህን ስጥ&#8221; ተብሎ ይለፈፋል:: በቃ በዚያው ጦርነቱ ያበቃል:: ያ ጊዜ አሁን አይደለም:: ሰላማዊ ፍልሚያው ይበልጥ ተጧጡፏል:: አባላት ይመዘገባሉ: ቢሮወች ይከፈታሉ: የፖለቲካ ትምህርት ይሰጣል::</p>
<p>&nbsp;</p>
<p>የመዐሕድ ጩኸት ፍሬ አሳየ:: አማሮችን በአማራነታቸው ብቻ ሰብስቦ መግደል ጋብ አለ:: ስለዚህ አሁን መዐሕድ ከአማራው አልፎ ለመላው ኢትዮጵያዊ ሊቆም የግድ ይላል የሚሉ ወገኖች ተበራከቱ:: እውነት ነው:: መጀመሪያምኮ ቢሆን መዐሕድ የተመሰረተው አማራ ተኮር የሆነ ግድያ በመስፋፋቱ ብቻ ነው:: ይህ ችግር ተንፈስ ካለ የሚቀጥለው ተግባር በኢትዮጵያ ላይ በጉልበቱ ነግሦ በዘርና በቋንቋ ህዝቡን እየከፋፈለ ያለውን ጸረ ህዝብና ጸረ ኢትዮጵያዊ ድርጅት ከኢትዮጵያውያን ጫንቃ ላይ አሽቀንሮ መጣል ይሆናል:: ይህ ውጤት ሊመጣ የሚችለው መላው ኢትዮጵያውያን በአንድ ላይ ተሰባስበው ለአንድ አላማ መሰለፍ ሲችሉ ብቻ ነው:: መዐሕድ ግቡን አሳክቷል:: ቀጣዩ ትግል ሁሉንም ኢትዮጵያዊ በእኩልነት የሚያሳትፍ ድርጅት መስርቶ በዚያው የሚካሄድ ይሆናል:: በዚህ መልኩ መኢአድ ተመሰረተ::</p>
<p>&nbsp;</p>
<p>ሻለቃ ሀይለየሱስ እጅጉ ኢትዮጵያዊ ወታደር ነበሩ:: ሲያደሙና ሲደሙ የነበሩት ለሀገራቸውና ለህዝባቸው ነው:: ሀገራቸው ኢትዮጵያ ህዝባቸውም ኢትዮጵያውያን ናቸው:: ቀዳሚ አላማቸውን ከመዐሕድ ጋር ያሳኩት ሀይለየሱስ ለቀጣይ ግዳጅ ከመኢአድ ጋር ተሰለፉ::</p>
<p>&nbsp;</p>
<p>ይቀጥላል</p>
<p>&nbsp;</p>
<p>&nbsp;</p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3162"     class="crp_title">ሰውየው &#8211; ክፍል 1</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1163"     class="crp_title">ሰላማዊ ትግል እና ኢትዮጵያውያን&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3164"     class="crp_title">የኢትዮጵያ ወጣቶች ብሄራዊ ንቅናቄ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3018"     class="crp_title">በእውነት ኢትዮጵያን እንመራለን&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1138"     class="crp_title">አገር ቤት ያሉ ተቃዋሚዎች&hellip;</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=82721</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>ባለ ራእዩ ወያኔ/ኢህአዴግ በሙስና ቅሌት እራሱን አጋለጠ</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3251</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3251#comments</comments>
		<pubDate>Thu, 16 May 2013 14:27:47 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3251</guid>
		<description><![CDATA[እስክንድር አሰፋ ከኖርዌይ ባለ ራእዩ የወያኔ  መንግስት ባልታወቀ ወይም ሆን ተብሎ በተሰራ የቴክኔክ ብልሽት በዚህ ሰሞን በአባላትና ጀሌዎቹ ላይ ለ22 አመታት ታይቶ በማይታወቅ የሙስና ቅሌት ሰበብ ወደ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት እያጎሯቸው ይገኛል። የሚገርመው ደጋፊዎቻቸው ከሐገር ቤት እስከ ዲያስፖራው  ብዙ ሲለፈልፉላቸው ይሰማ ነበር ልማታዊ መንግስታችን፤ ልማታዊ ሚኒስትሮቻችን ፤ ልማታዊው መሪያችን  በማለት ከሰብአዊ መብት ጥበቃ በፊት መንገድ ስራና የአፓርታማ ግንባታ ይቅደም በማለት  መቆሚያና [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1395">ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ 2ኛ ዓመት ቅጽ 2 ቁ</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2978">ሰላማዊ ትግላችንን ከፍ አድርገን&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2650">የተቃዋሚ ድርጅቶች ሰላማዊ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3007">ሰማያዊ ፓርቲ በአፍሪካ ሕብረት 50ኛ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2354">በደም የተከበረ የዓለም ሠራተኞች&#8230;</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p itemprop="name"><strong>እስክንድር አሰፋ</strong></p>
<p itemprop="name"><strong>ከኖርዌይ</strong></p>
<div itemprop="description articleBody">
<div dir="ltr">
<div><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/601712_579119188786834_121958311_n.jpg"><img class="alignleft size-full wp-image-3252" alt="601712_579119188786834_121958311_n" src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/601712_579119188786834_121958311_n.jpg" width="320" height="164" /></a>ባለ ራእዩ የወያኔ  መንግስት ባልታወቀ ወይም ሆን ተብሎ በተሰራ የቴክኔክ ብልሽት በዚህ ሰሞን በአባላትና ጀሌዎቹ ላይ ለ22 አመታት ታይቶ በማይታወቅ የሙስና ቅሌት ሰበብ ወደ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት እያጎሯቸው ይገኛል። የሚገርመው ደጋፊዎቻቸው ከሐገር ቤት እስከ ዲያስፖራው  ብዙ ሲለፈልፉላቸው ይሰማ ነበር ልማታዊ መንግስታችን፤ ልማታዊ ሚኒስትሮቻችን ፤ ልማታዊው መሪያችን  በማለት ከሰብአዊ መብት ጥበቃ በፊት መንገድ ስራና የአፓርታማ ግንባታ ይቅደም በማለት  መቆሚያና መቀመጫ አሳጥተውን ነበር አሁን ምን ይውጣቸው ይሆን? እንደ ለመዱት ልማታዊ ሙስና ነው ብለው እንዳያስደነግጡን እንፈራለን።</div>
<div>haገራችንን ኢትዮጵያን ወያኔ /ኢህአዴግ ከተቆጣጠራት ጊዜ ጀምሮ ማለትም እ.ኤ.አ ከ1991 ዓ.ም ሐገሪቷንና ህዝቧን በመሳሪያ አግቶ በዘር በሃይማኖት ከፋፍለው  እንዲሁም ከቁጥጥር ውጪ  በሆነ የሰብአዊ መብት እረገጣ እና የኢኮኖሚ ቀውስ አድርሰውባታል አሁንም እያደረሱባትም ይገኛሉ።</div>
<div></div>
<div>ዝባችንም ከተወለደበት እና ካደገበት ቀዬው ሰላምን ፍለጋና ኑሮውን ለመምራት ሲል እግሬ አውጪኝ በማለት ወደ ማያውቅበት ሐገር ለመኖር ሲሰደድ፤ በየበረሐው ሲደበደብ፤ እንዲሁም ሲገደል እና በህይወት እያለ ሰውነቱ እየተቀደደ የውስጥ አካሉ  ሲሸጥ  እያየንና እየሰማንም ነው።</div>
<div></div>
<div>ይህ ሁሉ በደል እና ስቃይ በህዝባችን እየደረሰ ባለበት ጊዜ ስልጣኑን ተቆጣጥረው ያሉት የወያኔ/ኢህአዴግ ባለስልጣናት እኛ እናውቅላችኋለን፤ እናስተዳድራችኋለን በማለት የባለ እራዩን የዘረኛውንና የገንጣዩን መለስ ዜናዊ አመራር  አላማ ለማስፈጸም እጅ ለእጅ ተያይዘን እንሰራለን በማለት በህግ ላይ ህግ በማውጣት ህዝቡ ቀና ብሎ  እንዳያያቸው በተበላሸና በከረፋ የህግ የበላይነት<br />
ስም ህዝቡን በማፈን፤ ለፍትህና ዲሞክራሲያዊ ስርዓት መስፈን የሚታገሉ ነገር ግን በአሸባሪነት ስም የታሰሩ ጋዜጠኞች፣ የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችና የእምነት ስርዓታችንንና የሃይማኖት መሪዎቻችንን ምርጫ እምነታችን በሚፈቅደው መንገድ ብቻ እናከናውን ያሉ የእስልምና ሃይማኖት ተከታይ ዜጎችን በአሸባሪነት በመወንጀልና በመክሰስ እንዲሁም በዋልድባ ገዳም አባቶቻችንን በማሳደድና በመዝረፍ ሲያሰቃዩ  እነሱ ግን  በቅሌትና በሙስና የሀገሪቷን ሃብት እና ንብረት  ለግል ጥቅማቸው በማዋል እንዲሁም የሀገሪቷን ጥሬ ሃብትና ንብረት ወደ ውጪ በማሽሽ  በውጪ በሚገኙ ዘመዶቻቸው ስምና የነሱ ተባባሪ ወዳጅ መንግስታት ሐገሮች ባንክ ውስጥ በማስቀመጥ ሐገራችንን ኢትዮጵያን  በአለም ታይቶ በማይታወቅ የኑሮ እድገት የኋልዮሽ እሽቅድምድም ውስጥ በማስገባት ለከፋ ችግር አጋልጠዋታል።</div>
<div></div>
<div></div>
<div>እውነት አሁን ወያኔ/ኢህአዴግ ሀገራችንን ኢትዮጵያ ይህን ሁሉ አመታት ከግብረ አበሮቹና ከጀሌዎቹ ጋር በመተባበር ሲያደማትና ሲበዘብዛት  ቆይቶ አሁን  በሙስና ቅሌት ያዝኳቸው በማለት ግብረ አበሮቹን በገሃድ ያጋለጠበትና አሳዶ  ወደ ወይኒ የወረወረበትን  ምክንያት እውነት ለሐገራች ተቆርቋሪነቱን ለማሳየት ይሆን ? ወይስ የማናውቀው መፍረክረክ ተፈጠረባቸው ? ይህንን ጥያቄ  እሱ እራሱ ባለጉዳዩ ይመልሰው ወይም እነሱ እንደ ጀመሩት እራስ በራሳቸው ተበላልተው ያልቁልናል ብለን ዝም ብለን እንመልከት?</div>
<div>እኔ እንደማስበው ወያኔ/ኢህአዴግ በአሁን ሰአት እያረጀ የመጣ ትልቅ የግራር ዛፍ ነው ብዬ አምናለሁ ምክንያቱም ስርአቱ ውስጥ የመፍረክረክ ሁኔታና የመበስበስ ባህሪይ ማሳየቱ ከውስጡ ያሉት ሞተር የነበሩት እራሳቸውን ወደ ማግለል ደረጃ ላይ ደርሰው እያየናቸው ነው ስለዚህ የበሰበሰውን ስርአት በደንብ እንዲበሰብስ አድርጎ የመጣል ሐላፊነት ያለብን ይመስለኛል ለዛም ዋና መፍትሄ የሚሆነው ስርአቱን ፊት ለፊት እና በተለያየ መንገድ የሚታገሉትን ድርጅቶችን ሆነ ግለሰቦችን አንድ በማድረግ ልዩ ነታችንን ትተን በአንድነት መፋለም ያስፈልጋል ብዬ አምናለው ያለ በለዚያ ስርአቱ በሰበሰ አረጀ እራሱ ይወድቃል ብለን ቁጭ ብለን የምንጠብቅ ከሆነ እራሳችን በስብሰን ከዚህ በበለጠ በከፋ  አገዛዝ እንደምንገዛ ጥርጥር የለኝም።</div>
<div></div>
<div></div>
<div><strong>መልክት ለወያኔ ደጋፊዎች </strong><br />
<strong></strong></div>
<div></div>
<div>በማወቅም ሆነ ባለማወቅ የወያኔን ስርአት የምትደግፉ ወገኑቻችን  በአሁን ሰአት አለማችን በቴክኖሎጂ አድጋ  አንድ ሆናለች  የትም ሆናችሁ የትም ስለ ሃገራችሁም ሆነ ስለምትፈልጉት ነገር ቤት ቁጭ ብላችሁ ማየትም መስማትም ትችላላችሁ  ስለዚህ ማሳሰብ የምፈልገው ነገር ሐገራችን ኢትዮጵያ ከየት ወዴት እንደምትሄድ እና በስርአቱ ውስጥ ምን ያህል እንዝላልነትና ሐላፊነት የጎደለው አገዛዝ እንዳለ ለናተም የተደበቀ ነገር ያለ አይመስለኝም እድሜ ለቴክኖሎጂ የለፈውን እንተወውና አሁን በቅርቡም በመገናኛ ቦዙሃን እንደሚደመጠው በሐገራች ላይ ምን ያህል ምዝበራና ዘረፋ እየተካሄደባትና ኢ ሰብአዊ ድርጊት በህዝባችን ላይ እየደረሰ እንደሆን ለናተ መንገር  ለቀባሪው አረዱት ማለት ነው  ስለዚህ ጠንቅቃችሁ ታቁታላችሁ ። እግዚአብሄር በሰጣችሁ ጭንቅላት በመጠቀም ወደ ሰውኛ አስተሳሰብ ተመልሳችሁ ጊዜው  ሳይረፍድ ከጭቁኑ ኢትዮጵያዊ ጋር ጎን ለጎን በመቆም በአፓርታይድ አገዛዝ ስር የወደቀችውን ሐገራችንን ነጻ ለማውጣት እንታገል   በማለት ወንድማዊ መልእክቴን አስተላልፋለሁ።</div>
<div>መረጃ ለማግኘትም ሆነ ለግንዛቤ ሰሞኑን ከወጡት ዜናዎች መካከል በጥቂቱ</div>
<div></div>
<div></div>
<div></div>
<div><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3201" >http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3201</a></div>
<div></div>
<div><a href="http://escondera.blogspot.no/2013/05/ethiopia-corruption-and-miseducation-of.html" >http://escondera.blogspot.no/2013/05/ethiopia-corruption-and-miseducation-of.html</a></div>
<div></div>
<div><a href="http://ethsat.com/video/" >http://ethsat.com/video/</a></div>
<div></div>
<div></div>
<div></div>
<div>ቸር ያሰማን</div>
<div></div>
<div></div>
<div>ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሄር ትዘረጋለች</div>
<div></div>
<div></div>
<div> ድል ለኢትዮጵያ ሞት ለወያኔ</div>
<div></div>
<div></div>
<div></div>
<div></div>
</div>
</div>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1395"     class="crp_title">ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ 2ኛ ዓመት ቅጽ 2 ቁ</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2978"     class="crp_title">ሰላማዊ ትግላችንን ከፍ አድርገን&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2650"     class="crp_title">የተቃዋሚ ድርጅቶች ሰላማዊ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3007"     class="crp_title">ሰማያዊ ፓርቲ በአፍሪካ ሕብረት 50ኛ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2354"     class="crp_title">በደም የተከበረ የዓለም ሠራተኞች&hellip;</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=82714</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>ድምጻዊት አበበች ደራራ አረፈች</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3241</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3241#comments</comments>
		<pubDate>Thu, 16 May 2013 12:43:01 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3241</guid>
		<description><![CDATA[ድምጻዊት አበበች ደራራ ከዚህ አለም በሞት መለየቷን የተለያዩ ድረ ገፆች እየዘገቡ ነው፡፡ ማለዳ ታይምስ ድረ ገፅ ድምጻዊት አበበች ደራራ በስደት አለም እስራኤል አገር ውስጥ በቴል አቪቭ ከተማ ኑሮዋን ካደረገችበት ጊዜ ጀምሮ በጤና መታወክ ለብዙ ጊዜ ስትሰቃይ መክረሟን ገልጾ በዛሬው እለት ህይወቷ ማለፉን እና የቀብር ስነስራቷ በእዚያው በቴል አቪቭ እንደሚፈጸም ጠቁሞአል። በተለይም ባሳልፍነው ስድስት ወራት ህመሟ [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/163">የአርቲስት ታምራት ሞላ የቀብር ሥነ-&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/13">ቦንድ ለመሸጥ ሳዑዲ የገባው ወያኔ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2536">በኖርዌይ የሚኖሩ ጀግና&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1690">አርቲስት ብርሃኑ ተዘራ በኢትዮጵያ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1478">በሮተርዳም ማራቶን ብርሃኑ ሽፈራው&#8230;</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p><iframe src="http://www.youtube.com/embed/YmISJlHG4g0" height="360" width="480" allowfullscreen="" frameborder="0"></iframe><br />
ድምጻዊት አበበች ደራራ ከዚህ አለም በሞት መለየቷን የተለያዩ ድረ ገፆች እየዘገቡ ነው፡፡ ማለዳ ታይምስ ድረ ገፅ ድምጻዊት አበበች ደራራ በስደት አለም እስራኤል አገር ውስጥ በቴል አቪቭ ከተማ ኑሮዋን ካደረገችበት ጊዜ ጀምሮ በጤና መታወክ ለብዙ ጊዜ ስትሰቃይ መክረሟን ገልጾ በዛሬው እለት ህይወቷ ማለፉን እና የቀብር ስነስራቷ በእዚያው በቴል አቪቭ እንደሚፈጸም ጠቁሞአል።<br />
<a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/AbebechDerara.jpg"><img class="alignleft size-full wp-image-3242" alt="AbebechDerara" src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/AbebechDerara.jpg" width="294" height="282" /></a>በተለይም ባሳልፍነው ስድስት ወራት ህመሟ በከፍተኛ ሁኔታ ላይ እንደነበር በተለያዩ ሚዲያዎች ከመገለጹም በላይ ለህክምና እርዳታ የሚሆናትን ገንዘብ እንዲሰባሰብ በተለያዩ አገራት ላይ እንዲከናወን መጠየቁ ይታወሳል ።ሆኖም ግን ምንም አይነት እንቅስቃሴ ከህብረተሰቡ ሲደረግ እንዳልታየ የሚታወቅ ነው ። አበበች ደራራ በራስ ቴአትር ሃገረሰብ የተሰኘ ቡደን በተቋቋመበት ወቅት ከነ ነዋይ ደበበ ጋር በመሆን በማቋቋም ስራዋን በከፍተኛ ደረጃ የጀመረች ድንቅ አርቲስት ነበርች በተለይም በመድረክ ላይ እንቅስቃሴዋ የሰውን ቀልብ ትስባለች እየተባለ የምትወደሰው ድምጻዊት ደራራ የራስ ቴአትር አምባሳደር ትባልም እንደነበር ያገኘነው ፋይል ይጠቁማል።በቴአትር ቤቶች ውስጥ በመድረቅ የሙዚቃ ስራን በመስራት ከፍተኛ አድናቆትን ያተረፈች ሲሆን ጥቂት የማይባሉ ሙዚቃዎችንም በካሴት አሳትማ ልህዝብ አቅርባለች ከነዚህም መካከል በሉ እንጂ ፣ተው ማነህ፣ገላዬ ፣ሰው በፍቅር ታሞ የተባሉት ጥቂቶቹ ናቸው።<br />
አበበች ደራራ በሕመም ተይዛ ለበርካታ ወቅት በአልጋ ላይ ከመቆየቷም ባሻገር ጨርሶ ከሰዎች ጋር ግንኙነት አቋርጣ በሽታዋን ለብቻዋ ስታስታምም እንደነበረች በቅርብ የሚያውቋት ይናገራሉ፡፡<br />
የአበበች ደራራ አስከሬን በኖረችበት የቴል አቪቭ ከተማ በዛሬው እለት ከቀኑ 3.00PM ላይ ወደ ቀብር በወዳጅ ዘመዶች ታጅቦ በመሄድ ሥርአተ ቀብርዋም እንደሚከናወን የደረሰን መረጃ ያመለክታል። (ምንጭ፡ ሸገር ትሪብዩን)</p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/163"     class="crp_title">የአርቲስት ታምራት ሞላ የቀብር ሥነ-&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/13"     class="crp_title">ቦንድ ለመሸጥ ሳዑዲ የገባው ወያኔ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2536"     class="crp_title">በኖርዌይ የሚኖሩ ጀግና&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1690"     class="crp_title">አርቲስት ብርሃኑ ተዘራ በኢትዮጵያ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1478"     class="crp_title">በሮተርዳም ማራቶን ብርሃኑ ሽፈራው&hellip;</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=82712</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>የአንድነት/መድረክ የፖለቲካ ግንኙነት እና የጋራ እንቅስቃሴ ከመቀናጀት እስከ ግንባር ያለው አጠቃላይ ሁኔታ ግምገማ</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3235</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3235#comments</comments>
		<pubDate>Thu, 16 May 2013 12:05:19 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3235</guid>
		<description><![CDATA[ሚያዝያ 19 ቀን 2005 ዓ.ም የአንድነት ፓርቲ ብ/ም/ቤት ባደረገው ስብሰባ ላይ ባስተላለፈው ውሳኔ መሰረት የአንድነት/መድረክ የፖለቲካ ግንኙነት እና የጋራ እንቅስቃሴ ከመቀናጀት እስከ ግንባር ያለው አጠቃላይ ሁኔታ ላይ የተዘጋጀውን ሰነድ ገምግሞ አፅድቋል፡፡ ሰነዱም ለመድረክና ለመድረክ አባል ፓርቲዎች እንዲሰጥ፣ አባላትና ደጋፊዎች እንዲያውቁት እንዲሁም ለህዝቡና ለመገናኛ ብዙሃን እንዲሰራጭ በተባለው ውሳኔ መሰረት እነሆ ሰነዱን አያይዘናል፡፡ ትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!! የአንድነት [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2557">አንድነት ፓርቲ በመድረክ ስር ያሉ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2280">የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2627">ዶ/ር መረራ ጉዲና እና አቶ ገብሩ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1535">አንድነት በህሊና እስረኞች ላይ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1775">ወደ ቅሊንጦ እስርቤት ያመሩት&#8230;</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/UDJ.png"><img class="alignleft  wp-image-3236" alt="UDJ" src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/UDJ.png" width="208" height="208" /></a>ሚያዝያ 19 ቀን 2005 ዓ.ም የአንድነት ፓርቲ ብ/ም/ቤት ባደረገው ስብሰባ ላይ ባስተላለፈው ውሳኔ መሰረት የአንድነት/መድረክ የፖለቲካ ግንኙነት እና የጋራ እንቅስቃሴ ከመቀናጀት እስከ ግንባር ያለው አጠቃላይ ሁኔታ ላይ የተዘጋጀውን ሰነድ ገምግሞ አፅድቋል፡፡ ሰነዱም ለመድረክና ለመድረክ አባል ፓርቲዎች እንዲሰጥ፣ አባላትና ደጋፊዎች እንዲያውቁት እንዲሁም ለህዝቡና ለመገናኛ ብዙሃን እንዲሰራጭ በተባለው ውሳኔ መሰረት እነሆ ሰነዱን አያይዘናል፡፡</p>
<p>ትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!!<br />
የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት</p>
<div dir="ltr">
<p><wbr /></p>
<p><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/Notes-on-Medrek-Strategic-and-Polatical-Issues_April_17_2013-1.pdf" ><strong> የአንድነት ብሔራዊ ምክር  ቤት አቋምን የሚያሳይ ሰነድ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ</strong></a></p>
</div>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2557"     class="crp_title">አንድነት ፓርቲ በመድረክ ስር ያሉ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2280"     class="crp_title">የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2627"     class="crp_title">ዶ/ር መረራ ጉዲና እና አቶ ገብሩ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1535"     class="crp_title">አንድነት በህሊና እስረኞች ላይ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1775"     class="crp_title">ወደ ቅሊንጦ እስርቤት ያመሩት&hellip;</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=82713</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>በምርጫ 97 የትዝታ ማህደር ውስጥ የልደቱ ቦታ</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3229</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3229#comments</comments>
		<pubDate>Thu, 16 May 2013 04:07:11 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3229</guid>
		<description><![CDATA[ከመሐመድ አሊ መሐመድ (ጋዜጠኛ) እስኪ በትዝታ ፈረስ ሽምጥ እንጋልብና የምርጫ 97ን ሂደት እንደዋዛ እንዳስሰው፡፡ ምርጫ 97 ሲነሳ ከትውስታ ማህደራችን ጎላ ብሎ የሚወጣው የሚያዚያ 30 ትዕይንተ ህዝብ ነው፡፡ ለነገሩማ ያ ታሪካዊ ዕለት እንዴት ይረሳል? ወደ መስቀል አደባባይ የሚያመሩ መንገዶች ሁሉ በለውጥ መንፈስ በተሞላ የህዝብ ጎርፍ የተጥለቀለቁበት፣ ያለማንም ቀስቃሽ ህዝብ ለመብቱና ለዴሞክራሲያዊ ለውጥ ሆ! ብሎ የወጣበት፣ ለዴሞክራሲያዊ [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2288">በዉጭ ያሉ ተቃዋሚዎችን ለማሰባሰብ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/998"> &#8211; በልጅግ ዓሊ</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2557">አንድነት ፓርቲ በመድረክ ስር ያሉ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1945">‹‹የ33ቱ ፓርቲዎች ጥያቄ በአጭር ቃል</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2433">“በሀገሪቱ የተደረገው ምርጫ&#8230;</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p>ከመሐመድ አሊ መሐመድ (ጋዜጠኛ)<br />
<a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/lidetu.jpg"><img src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/lidetu.jpg" alt="lidetu" width="222" height="258" class="alignleft size-full wp-image-3230" /></a>እስኪ በትዝታ ፈረስ ሽምጥ እንጋልብና የምርጫ 97ን ሂደት እንደዋዛ እንዳስሰው፡፡ ምርጫ 97 ሲነሳ ከትውስታ ማህደራችን ጎላ ብሎ የሚወጣው የሚያዚያ 30 ትዕይንተ ህዝብ ነው፡፡ ለነገሩማ ያ ታሪካዊ ዕለት እንዴት ይረሳል? ወደ መስቀል አደባባይ የሚያመሩ መንገዶች ሁሉ በለውጥ መንፈስ በተሞላ የህዝብ ጎርፍ የተጥለቀለቁበት፣ ያለማንም ቀስቃሽ ህዝብ ለመብቱና ለዴሞክራሲያዊ ለውጥ ሆ! ብሎ የወጣበት፣ ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ያለውን ብቃት ያረጋገጠበት፣ ኢትዮጵያዊ ጨዋነት ዓለምን ያስደመመበት ያ ታሪካዊ ዕለት እንዴት ይረሳል?<br />
ሚያዚያ 30ን ስናስታውስ አንድ ክስተትም አብሮ ይታወሳል፡፡ “ዴሞክራሲን እናወድስ” በሚል መሪ ቃል መስቀል አደባባይና ዙሪያ ገባውን ባጨናነቀው ህዝብ መሐል አንድት ፒክ-ኣፕ መኪና ወደ አደባባዩ እምብርት ዘለቀች፡፡ በመኪናዋ ላይ በኢትዮጵያ ባንዲራ ደምቆ የለውጥ ሀዋርያነቱን የሚያውጅ ሰው ነበር፡፡ ህዝቡም ያን የለውጥ ሀዋርያ በፍቅርና በስስት ስሜት እጁን ለመንካት ይረባረብ ነበር፡፡ እሱም እጆቹን በማውለብለብ አፀፋና ምስጋናውን ይገልፅ ነበር፡፡ በወቅቱ ስለዚያ የለውጥ ሃዋርያ አንዳች አሉታዊ አስተያየት መስጠት ትልቅ ዋጋ ያስከፍል ነበር፡፡<br />
ከምርጫው በኋላም ያ የለውጥ ሀዋርያ በድርጅቱ ጽ/ቤት ታገተ ተብሎ ህዝቡ በፆም በፀሎት ተጠመደ፡፡ በርካቶች ባገኙት ሚዲያና መንገድ ሁሉ እገታው የፈጠረባቸውን ስሜት በእንባና ሲቃ ሲገልፁ ተደመጡ፡፡ ግና በዚች ምድር ቋሚ ነገር የለምና ያ የለውጥ ሀዋርያ ተብሎ የተወደሰ ሰው ብዙም ሳይቆይ በካሀዲነት ተፈረጀ፡፡ ያ ሰው ማን እንደሆነ ግር የሚለው ሰው ይኖራል ብዬ አላስብም፡፡ ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ያለገደብ የተሞገሰና የተወገዘ! ግን ለምን?<br />
ስለልደቱ አያሌው ብዙ ተብሏል፡፡ እኔ የተባለውን ሁሉ አልጋራም፡፡ ነገር ግን ከፍተኛ የሆነ የስልጣን ጉጉት እንዳላቸው አውቃለሁ፡፡ ቢሆንም የፖለቲካ ትግል የመጨረሻ ግቡ ሥልጣን ይዞ ዓላማን ማስፈፀም በመሆኑ የሥልጣን ጥማት እንደነውር ሊታይ የሚገባው አይመስለኝም፡፡ ነውር የሚሆነው ዴሞክራሲያዊ ባልሆነ መንገድ ሥልጣን ለመያዝ ሲባል የቆሙለትን ዓላማ ጥያቄ ውስጥ እንዲገባ ማድረግ ነው፡፡ በተለይ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን ለማስፈን በሚደረግ ትግል ውስጥ ዴሞክራሲያዊ ባልሆነ መንገድ ሥልጣን ለመያዝ መሞከር የትግሉን ዓላማ ምን ያህል ሊጎዳው እንደሚችል መገመት አያስቸግርም፡፡<br />
ከዚህ አንፃር አቶ ልደቱ በተለያየ ጊዜ ከሥልጣን ሽኩቻ ጋር በተያያዘ ትግሉን የሚጎዱ አፍራሽ እርምጃዎች ወስደዋል፡፡ አቶ ልደቱ በቀድሞው መዐህድ (የመላው አማራ ህዝብ ድርጅት) አመራርና በወጣቶች መካከል በተፈጠረው አለመግባባት ሳቢያ ድርጅቱን ለቀው ሲወጡ የወሰዱት እርምጃ የድርጅቱን ገፅታ ከማጠልሸቱም በላይ በትግሉም ላይ ቀላል የማይባል ጉዳት አድርሷል፡፡ በኋላም ኢዴፓ ከተቋቋመ በኋላ በፓርቲው መሥራች አባላት መካከል በተፈጠረው አለመግባባት አቶ ልደቱ ተቀናቃኞቻቸውን ለማስወገድ የተከተሉት መንገድ ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ መቆማቸውን ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባ ነበር፡፡ በወቅቱ የሥልጣን ተቀናቃኞቻቸውን የፖለቲካ ሰብዕና ለመግደል/ሽባ ለማድረግ (character assassination/paralization) በእሳቸው ላይ ሲደርስ ያወገዙትን አሉባልታ የመንዛትና ስም የማጥፋት ስልት መከተላቸው አይዘነጋም፡፡<br />
አቶ ልደቱ የራሳቸው ምክንያት ቢኖራቸውም ፓርቲያቸው ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር በነበረው የትግልና የትብብር ግንኙነቶች ላይም የሚወስዷቸው አቋሞች እንደዚሁ ትግሉን የሚጎዱ ነበሩ ማለት ይቻላል፡፡ በተለይም በ1997 ዓ.ም በተፈጠረው #ቅንጅት$ ውስጥ አቶ ልደቱ ሲያሳዩት የነበረው ልታይ ልታይ ባይነትና አጉል #ብልጣብልጥነት$ በተቃውሞው ጎራ ውስጥ በዓይነ-ቁራኛ እንዲታዩ ሳያደርጋቸው አልቀረም፡፡ ቅንጅት በ1997 ምርጫ ሂደት በህዝብ ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነትና ድምፅ ካገኘ በኋላ ወደ ውህደት ሲያመራ የልደቱን የሥልጣን ፍላጎት ባለማርካቱ በእልህ ተነሳስተው የወሰዱት እርምጃ ታላቅ ታሪካዊ ስህተት ነበር ማለት ይቻላል፡፡ አቶ ልደቱ ለወሰዱት እርምጃ ምክንያት ቢኖራቸውም እርምጃውን የወሰዱበት ጊዜና መንገድ ከህዝብ እንዲነጠሉ በማድረግ ብዙ ፖለቲካዊ ዋጋ አስከፍሏቸዋል፡፡<br />
አቶ ልደቱ ለቅንጅት መፍረስ ምክንያት አለመሆናቸውን ለማሳመን ጥረት ቢያደርጉም በቀላሉ ሊሳካላቸው አልቻለም፡፡ የእሳቸው መከራከሪያ ቅንጅትን አንድ ልደቱ የሚያፈርሰው ከሆነ ከጅምሩም ቅንጅት የሚባል ጠንካራ ኃይል አልነበረም የሚል ነው፡፡ በእርግጥም ይህ ክርክር በደምሳሳው ሲታይ እውነትነት ያለው ይመስላል፡፡ ነገር ግን አቶ ልደቱ በውህደት ስምምነቱ ላይ መሐተም ለማሳረፍ አሻፈረኝ በማለታቸው የኢህአዴግ መንግሥት ያቋቋመው ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የቅንጅትን የህጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ለመከልከል ምክንያት አግኝቷል፡፡ አቶ ልደቱና ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የወሰዱት እርምጃ ቀደም ብሎ የተቀነባበረ ይሁን በድንገት የተፈጠረ ግጥምጥሞሽ ሊያስረዱን የሚችሉት አቶ ልደቱ ብቻ ናቸው፡፡<br />
አቶ ልደቱ ቅንጅት ከፈረሰ በኋላ #ሦስተኛ አማራጭ$ በሚል ያመጡት የፖለቲካ ፈሊጥ ብዙዎችን ግራ ያጋባና እሳቸውንም ለባሰ የፖለቲካ ክስረት የዳረገ ነው፡፡ በእርግጥ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ አማካይ ቦታ/#ሦስተኛ አማራጭ$ እንደሚያስፈልግ ቢታመንም ይህን አቋም ለማራመድ በወቅቱ አቶ ልደቱ ትክክለኛው ሰው ነበሩ ለማለት አይቻልም፡፡ ምክንያቱም የ1997 ምርጫን ተከትሎ በተፈጠረው ውጥረት የቅንጅት መሪዎች ለእስር እስከተዳረጉበት ጊዜ ድረስ በገዥው ፓርቲና በተቃዋሚዎች መካከል ለነበረው የተካረረ ግንኙነት አቶ ልደቱ ዋነኛው ተጠያቂ ናቸው፡፡<br />
ስለሆነም #የጭፍን ተቃውሞ$ ፖለቲካን ለማውገዝ/ከማውገዛቸው በፊት አቋማቸውን የቀየሩበትን አሳማኝ ምክንያት ማቅረብና ቀደም ሲል ሲያራምዱት በነበረው የተካረረ አቋም ሳቢያ ለደረሰው ጥፋት ሁሉ ኃላፊነት መውሰድና ይቅርታ መጠየቅ ነበረባቸው፡፡ ይህን ሳያደርጉ ድንገት ተነስተው #ሦስተኛ አማራጭ$ በማለታቸውና የተቃውሞውን ጎራ ተጠያቂ በማድረጋቸው ህዝብ ሊያምናቸው አልቻለም፡፡ ይልቁንም ከገዥው ፓርቲ ጋር ለመሞዳሞድ እንደፈጠሩት ሥልት ተቆጥሮ በካሃዲነት አስፈርጇቸዋል፡፡ አቶ ልደቱ በተሳሳተ ስሌት በእጃቸው ውስጥ የነበረውን መልካም ዕድል ካጡ በኋላ ተስፋ ሳይቆርጡ ቢፍጨረጨሩም እንደዋዛ ያመለጣቸውን ዕድል በቀላሉ መልሰው እጃቸው ውስጥ ሊያስገቡት አልቻሉም፡፡<br />
ይህም ሆኖ ግን አቶ ልደቱ አያሌው በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ሁነኛ ሥፍራ ያላቸውና የሚገባቸውም ሰው ናቸው፡፡ ወደተደራጀ የፖለቲካ ትግል ከገቡ ጀምሮ ያላቸውን ጊዜና አቅም አሟጥጠው ተጠቅመዋል፡፡ በተለይ የ97 ምርጫ ቅስቀሳ በእሳቸው ጫንቃ ላይ ያረፈ ነበር ማለት ይቻላል፡፡ በምርጫ ቅስቀሳው በአንድ በኩል የገዥውን ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች አንገት ሲያስደፉ በሌላ በኩል የተቃውሞውን ጎራ ደጋፊዎች አንጀት ያርሱ ነበር፡፡<br />
አቶ ልደቱ በትግሉ ውስጥ ያላቸው ቆይታ በአንፃራዊነት አጭር ሊባል የሚችል ቢሆንም ያካበቱት ልምድና እውቀት ቀላል የማይባል ነው፡፡ በእኔ እይታ አቶ ልደቱ የኢትዮጵያን ፖለቲካ ደርዝ ባለው መንገድ ለመገምገምና ለመተንተን ብቃት ካላቸው ጥቂት ኢትዮጵያውያን ተርታ የሚሰለፉ ናቸው፡፡ በእርግጠኝነት መናገር የሚቻለው አቶ ልደቱ የተቃዋሚ መሪዎችን ቁጥር በአንድ የሚያሳድጉ ሳይሆኑ በኢትየጵያ ፖለቲካ ውስጥ ትርጉም ያለው ሚና መጫወት የሚችሉ ሰው ናቸው፡፡ በእርግጥ አቶ ልደቱ የሚጫወቱት ሚና እንደየሰው አተያይ አዎንታዊ ወይም አሉታዊ ሊሆን ይችላል፡፡ ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ የ1997 ምርጫን ተከትሎ አቶ ልደቱን የገጠማቸው ከህዝብ የመነጠል ፈተናና ፈተናውን በአሸናፊነት ለመወጣት ተስፋ ሳይቆርጡ ያደረጉት ጥረትም ስለሰብዕናቸው የሚነግረን ቁም ነገር አለ፡፡<br />
አንዳንድ ሰዎች #ልደቱ ወደ ኢትዮጵያ ፖለቲካ ዳግም ላይመለስ የውድቀት ጽዋውን ተጎንጭቷል$ ሲሉ በኩራት ይናገራሉ፡፡ ነገር ግን የልደቱ ከህዝብ መነጠል ለተቃውሞው ጎራ ውድቀት እንጅ በኩራት የሚገለፅ ስኬት አይደለም፡፡ የአንዳንዶቻችን በልደቱ ውድቀት መደሰት ከተራ ምቀኝነት ያለፈ ትርጉም ላይኖረው ይችላል፡፡ ልደቱ ሰው ነውና ተሳሳተ፡፡ የሚሳሳተው ደግሞ የሚሰራ እንጅ ከዳር ቆሞ የሚታዘብ አይደለም፡፡<br />
በነገራችን ላይ የጊዜ ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር የቅንጅት መሪዎች ከእስር ከተፈቱ በኋላ የፈፀሙት ስህተት በምንም መመዘኛ ልደቱ ከፈፀመው ስህተት የሚያንስ አይደለም፡፡ ዱሮም ቢሆን ልደቱ የወሰደው እርምጃ የቅንጅትን ውድቀት አፋጠነው እንጅ ውሎ አድሮ ቅንጅትን ከመፈረካከስ የሚታደገው ኃይል አልነበረም፡፡ ምክንያቱም የቅንጅት አፈጣጠርም ሆነ የሰው ኃይል ጥንቅር ረጅም ርቀት መጓዝ የሚያስችለው አልነበረም፡፡<br />
እንደአለመታደል ሆኖ በቅንጅት ጥላ ሥር የተሰባሰቡት ሰዎች በኢትዮጵያ የፖለቲካ መድረክ መተያየት የማይፈልጉና አንዱ ሌላውን ጠልፎ ለመጣል የሚያደቡ ወይም በየጓዳ ጎድጓዳው የሚያሴሩ ስለመሆናቸው መሪዎቹ ከእስር በተፈቱ ማግሥት እውነቱ ገሀድ ሆኗል፡፡ ስለሆነም ለቅንጅት መፍረስ ልደቱን ብቻ ተጠያቂ ከማድረግ ይልቅ ሁላችንም ድርሻ ድርሻችንን መውሰድ ይኖርብናል፡፡ እኔ የድርሻዬን ለማንሳት ዝግጁ ነኝ፡፡ ያ ታሪካዊ ሂደት “ውሾን ያነሳ ውሾ ይሁን” በሚል ብሂል ተሸፋፍኖ መቅረት ያለበት አይመስለኝም፡፡ በግልፅ ልንነጋገርበትና ልንማርበት ይገባል ብዬ አምናለሁ፡፡ ስለተቃውሞው ፖለቲካ መፃኢ ዕድል መነጋገር ካለብን ደግሞ #አለባብሰው ቢያርሱ በአረም ይመለሱ$ እንዲሉ መሆን የለበትም፡፡</p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2288"     class="crp_title">በዉጭ ያሉ ተቃዋሚዎችን ለማሰባሰብ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/998"     class="crp_title"> &#8211; በልጅግ ዓሊ</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2557"     class="crp_title">አንድነት ፓርቲ በመድረክ ስር ያሉ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1945"     class="crp_title">‹‹የ33ቱ ፓርቲዎች ጥያቄ በአጭር ቃል</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2433"     class="crp_title">“በሀገሪቱ የተደረገው ምርጫ&hellip;</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=82671</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>የዓለም  ህዝብ ሥጋትና በዚሁ ሥጋት ውስጥ ተተብትባ የተያዘችው ኢትዮጵያ</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3226</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3226#comments</comments>
		<pubDate>Thu, 16 May 2013 01:59:10 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3226</guid>
		<description><![CDATA[ መንደርደሪያ  አገራችን  ኢትዮጵያ የረጅም ዘመን ታሪክ በተለይም ከአንደኛው እስከ ስድስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ድረስ ህዝቧ አምልኮ ፈጣሪውን የሚከተልና  የሃገሩን ፤ የወገኑን ክብር ሳያስደፍር የኖረ ታላቅ ህዝብ መሆኑን ያስመሰከረ  እንደሆነ ታሪክ ይመሰክራል ። ክ7ተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ  በዓለም ላይ ክፍተኛ የእድገት ደረጃውን ጠብቆ ሃገሩ በዓለም ዙሪያ እንድትታወቅ  ያደረገ ህዝብ  ለመሆኑ ቛሚ ምስክር የሆኑት ታሪካው ህንጻዎቹ [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/971">ለዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ኢትዮጵያ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2140">ኢትዮጵያ በፊፋ ያላት የእግር ኳስ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3192">“በኢንቨስትመንት ስም የሚፈጸም&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/908">ለዛች አገር የሚገባት እውን ይሄ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/382">በፊፋ የሃገራት የእግር ኳስ ደረጃ&#8230;</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p><b> <a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/02/Map-ethiopia.jpg"><img class="alignleft size-medium wp-image-640" alt="Map ethiopia" src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/02/Map-ethiopia-300x243.jpg" width="200" height="153" /></a></b><b>መንደርደሪያ</b></p>
<p><b> አገራችን </b> ኢትዮጵያ የረጅም ዘመን ታሪክ በተለይም ከአንደኛው እስከ ስድስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ድረስ ህዝቧ</p>
<p>አምልኮ ፈጣሪውን የሚከተልና  የሃገሩን ፤ የወገኑን ክብር ሳያስደፍር የኖረ ታላቅ ህዝብ መሆኑን ያስመሰከረ  እንደሆነ ታሪክ ይመሰክራል ። ክ7ተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ  በዓለም ላይ ክፍተኛ የእድገት ደረጃውን ጠብቆ ሃገሩ በዓለም ዙሪያ እንድትታወቅ  ያደረገ ህዝብ  ለመሆኑ ቛሚ ምስክር የሆኑት ታሪካው ህንጻዎቹ ምስክሮች ናቸው።</p>
<p>ለሃገራችው  የትውልድ ዓርዓያ ሆነው ያለፉት አባቶቻችንም በክብር  ዘውትር በጠላቶች ሲከበሩና ሲፈሩ የኖሩ ለመሆኑ በተደጋጋሚ ዓለም ያወቀው ፀሐይ የሞቀው የታሪክ ህያው ምስክር ነው ። ይህች ሃገር ለመላው  የጥቁር ዘር ኩራት  ሆና በጠላትነት የፈረጁዋት ጠላቶቿን ደግሞ እንደ እሳት  የፈጀች ታላቅና ውድ ሃገር ነች።ይህች ሃገር ለምን እንደሊሎቹ የአውሮፓውያን ሃገራት ለምን  በሥልጣኔ  ወደፊት እንዳልገፋች ኢትዮጵያውያን ስንጠይቅ መልሱ ምን ይሆን?</p>
<iframe src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/plugins/google-document-embedder/view.php?url=http%3A%2F%2Fwww.zehabesha.com%2Famharic%2Fwp-content%2Fuploads%2F2013%2F05%2Fየዓለም-ሥጋትና-ተጠፍራ-የ-ተያዘችው-ኢትዮጵያ.pdf&hl=&gpid=1&embedded=true" class="gde-frame" style="width:100%; height:300px; border: none;" scrolling="no"></iframe>
<p class="gde-text"><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/የዓለም-ሥጋትና-ተጠፍራ-የ-ተያዘችው-ኢትዮጵያ.pdf" class="gde-link">Download (PDF, 691KB)</a></p>
<p>&nbsp;</p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/971"     class="crp_title">ለዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ኢትዮጵያ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2140"     class="crp_title">ኢትዮጵያ በፊፋ ያላት የእግር ኳስ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3192"     class="crp_title">“በኢንቨስትመንት ስም የሚፈጸም&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/908"     class="crp_title">ለዛች አገር የሚገባት እውን ይሄ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/382"     class="crp_title">በፊፋ የሃገራት የእግር ኳስ ደረጃ&hellip;</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=82639</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>5 ሰዓታትን በቀድሞ ማዕከላዊ ፖሊስ (ፍሬው አበበ በአዜብ መስፍን ክስ ከተመረመረ በኋላ የፃፈው)</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3222</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3222#comments</comments>
		<pubDate>Thu, 16 May 2013 00:53:51 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3222</guid>
		<description><![CDATA[ፍሬው አበበ የሰንደቅ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ሰኞ ዕለት ከሰዓት በኋላ የተንቀሳቃሽ ስልኬ አንጫረረ፡፡ ሳነሳው ለስላሳ የሴት ድምጽ ፍሬው መሆኔን ማረጋገጫ ጠይቃኝ ስታበቃ የቀድሞ ማዕከላዊ ስለምፈለግ ደረስ ብዬ መምጣት እችል እንደሆን በፍጹም ትህትና ጠየቀቺኝ፡፡ በዕለቱ እንደማይመቸኝ፤ ዕረቡ ጠዋት ግን መገኘት እንደምችል ለደዋዬ ነግሬ ሰልኩን ዘጋሁ፡፡ እንግዲህ በፕሬስ ክስ ጉዳይ ለፖሊስ ቃሌን ስሰጥ ይኸኛው ለአራተኛ ጊዜ መሆኑ [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2069">ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ ወደ ዝዋይ ወህኒ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1464">Hiber Radio: ኢህአዴግ ለመለወጥ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/636">&#8220;ስብሰባው&#8221;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3159">Hiber Radio: የስዬ አብርሃ ወንድም ዳግም&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1777">የአቶ መለስ ልጅ መንግስትን በጣልቃ&#8230;</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<h3 itemprop="name"><span style="font-size: 13px;">ፍሬው አበበ</span></h3>
<div>
<div>የሰንደቅ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ</div>
</div>
<div itemprop="description articleBody">
<div dir="ltr">
<div>
<div id="attachment_637" class="wp-caption alignright" style="width: 170px"><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/02/Frew-alyu.jpg"><img class="size-full wp-image-637" alt="ጋዜጠኛ ፍሬው አበበ" src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/02/Frew-alyu.jpg" width="160" height="160" /></a><p class="wp-caption-text">ጋዜጠኛ ፍሬው አበበ</p></div>
</div>
<div>ሰኞ ዕለት ከሰዓት በኋላ የተንቀሳቃሽ ስልኬ አንጫረረ፡፡ ሳነሳው ለስላሳ የሴት ድምጽ ፍሬው መሆኔን ማረጋገጫ ጠይቃኝ ስታበቃ የቀድሞ ማዕከላዊ ስለምፈለግ ደረስ ብዬ መምጣት እችል እንደሆን በፍጹም ትህትና ጠየቀቺኝ፡፡ በዕለቱ እንደማይመቸኝ፤ ዕረቡ ጠዋት ግን መገኘት እንደምችል ለደዋዬ ነግሬ ሰልኩን ዘጋሁ፡፡ እንግዲህ በፕሬስ ክስ ጉዳይ ለፖሊስ ቃሌን ስሰጥ ይኸኛው ለአራተኛ ጊዜ መሆኑ ነው፡፡ ከቀድሞዎቹ ሶስት ክሶች አንዱ የስም ማጥፋት ሲሆኑ ሌላኛው በተሰረዘ ፈቃድ ሰርታችሃል፣ ሌላው ደግሞ ያለፈቃድ ጋዜጣ ታትማላችሁ የሚል ነበር፡፡ በአጋጣሚ ሁለቱ የቀድሞ ክሶች ከፖሊስ ያላለፉ ሲሆን አንደኛው ማለትም የኒቲ የኒቨርሲቲ ያሳትመው የነበረው “ኤቢቢአይ ዊክሊ” የተባለው ጋዜጣ በተሰረዘ ፈቃድ ሰርታችሃል በሚል ክስ ከተመሰረተባቸው 14 ያህል ሰራተኞች አንዱ ሆኜ አንድ ዓመት ተኩል ጊዜያት ያህል ፍ/ቤት ከተመላለስኩ በኋላ እኔን ጨምሮ 13 ተከሳሾችን ፍ/ቤቱ መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነጻ ይሰናበቱ ሲል ውሳኔ በመስጠቱ ነጻ መሆን ችያለሁ፡፡ (እዚህ ምድብ ውስጥ የአዲስ ነገሩ አብርሃም በጊዜው ይገኝበት ነበር)</div>
<div>ዛሬ ረቡዕ በጠዋት ማልጄ በመነሳት ቁርስ ቀማምሼ ወደተጠራሁበት የቀድሞ ማዕከላዊ ፖሊስ 3፡15 ሰዓት ላይ ደረስኩ፡፡ ማልጄ መነሳቴ ወድጄ አልነበረም፤የሄድኩበትን የምርመራ ጣጣ ከምሳ በፊት ባጠናቅቅ በሚል ጉጉት ነበር ፤አልሆነም እንጂ፡፡ መርማሪዬ ትሁት ሴት ፖሊስ መሆኑዋ ጭንቀቴን ለጊዜውም ቢሆን እንድረሳ ረድቶኛል፡፡ ያው የተለመደውን አሰልቺ ቅጽ መሙላት ግን የግድ ነበር፡፡ ሙሉ ስም፣አድራሻ፣የእናት ሙሉ ስም፣የአባት ሙሉ ስም፣የትውልድ ቦታ፣ የትውልድ ቦታ አድራሻ፣ብሔር፣የባለቤቴ ስም፣አድራሻ፣ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ስም፣የት/ቤቱ አድራሻ፣የተማርኩበት ጊዜ፤የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ስም፣አድራሻ፣ የተማርኩበት ጊዜ፣ የከፍተኛ ትምህርት የተማርኩበት ዩኒቨርሲቲ ስም፣አድራሻ፣የተማርኩበት ጊዜ፣የቀድሞ መ/ቤት ስም፣የነበረኝ ኃላፊነት፣የነበረኝ ደመወዝ መጠን፣ የአሁን መ/ቤት ስም፣ያለኝ ኃላፊነት፣ያለኝ የደመወዝ መጠን፣ የጋብቻ ሁኔታ፣የልጆች ብዛት፣ዕድሜያቸው፣አጠቃላይ ክሱ እና በክሱ ላይ ያለኝ ምላሽ፣ የተጠረጠርኩበትን መፈጸም አለመፈጸሜን (የእምነት ክህደት ቃል) ወዘተ….እጅግ አድካሚ ዶሴ ተሞላና ጨረስኩ ስል አሻራና ፎቶግራፍ መነሳት የግድ ነው ተባልኩ፡፡ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ ሰጥቻለሁ ብልም ሰሚ አልነበረም፡፡ እዚያም የእያንዳንዱ ጣት አሻራ(የግራ የቀኝ) ፣ ፎቶ ፊትፊት በግራና ቀኝ መነሳት ግድ ነበር፡፡ ይህ ሁሉ ግን በፕሬስ ተፈጸመ ተብሎ በአንድ ሰው በቀረበ አቤቱታ መነሻነት ገና ለገና ተጠርጣሪ ነው የተባለው ፕሬስ ዋናአዘጋጅ የመጀመሪያዋ ቀላል ፈተና መሆኑ ነው፡፡</div>
<div>ፖሊስ ቃል ከመስጠቴ በፊት ሁለት ጥያቄዎች እንዲመለሱልኝ ለመርማሪዬ ጥያቄ አቀረብኩኝ፡፡ አንዱ የተከሰስኩበት ጉዳይ እና ከሳሼ ማን እንደሆነ ነበር፡፡ የተከሰስኩበት ጉዳይ በቀድሞው ጠ/ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ባለቤት ወ/ሮ አዜብ መስፍን ከቤተመንግስት አለመውጣታቸውን ጠቅሰህ ጽፈሃል፣በዚህ ስም አጥፍተሃል የሚል ይዘት ያለው መሆኑ ተነገረኝ፡፡ ዜናው የተሰራው በአበሻ አቆጣጠር መስከረም 30 ቀን 2005 ዓ.ም ሲሆን በጠቅላው ወደስምንት ወር ገደማ ሆኖታል፡፡</div>
<div>
<div id="attachment_637" class="wp-caption alignleft" style="width: 170px"><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/02/Frew-alyu.jpg"><img class="size-full wp-image-637" alt="ጋዜጠኛ ፍሬው አበበ" src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/02/Frew-alyu.jpg" width="160" height="160" /></a><p class="wp-caption-text">ጋዜጠኛ ፍሬው አበበ</p></div>
<p>የዜናው ይዘትም በአጭሩ ወ/ሮ አዜብ መስፍን ከቤተመንግስት አለመውጣታቸውን በአንድ በኩል በሌላ በኩል በወቅቱ ከተሾሙ 19 ቀናት የሞላቸው ጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ መኖሪያ ቤታቸው ከሚገኝበት ሳር ቤት አካባቢ በየዕለቱ ትራፊክ እያዘጉ በመውጣትና በመግባት ላይ መሆናቸው፣ የአካባቢውን ህብረተሰብ የመንቀሳቀስ ነጻነት ላይ ችግር መፍጠሩን፣ለደህንነታቸውም ቢሆን አስጊ መሆኑን፣ ወ/ሮ አዜብ መስፍን ቤተመንግስቱን እንዲለቁ በተደጋጋሚ ተጠይቀው ባልታወቀ ምክንያት ፍቃደኛ አለመሆናቸውን የሚያትት ነበር፡፡ ዜናውን ስንሰራው በትልቁ ታሳቢ ያደረግነውና እንደጋዜጠኛ ሙያዊ ነጻነታችን ተወጥተኛል ብለን የምናስበው የጠ/ሚኒስትር ኃ/ማርያም ደሳለኝ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ስራቸውን ማከናወን በምንም መልኩ ተቀባይነት ያልነበረውና ደህንነታቸውንም በእጅጉ ለአደጋ ያጋለጠ የመሆኑ ጉዳይ ነበር፡፡ የዚህ ዜና መውጣት በአገር ውስጥና በውጪ መነጋገሪያ ርዕሰ ጉዳይ ሆኖ በመቆየቱ ወ/ሮ አዜብ በክብር ወደተዘጋጀላቸው ቦታ እንዲዛወሩ፣አቶ ኃ/ማርያምም ወደቤተመንግስት እንዲገቡ በማድረግ ረገድ ሁለቱንም ወገኖችን የጠቀመ ውጤት አስገኝቷል ብለን እናምናለን፡፡ በዚህ ዜና መሸለም እንጂ መጉላላትና ክስ ይቀርብብናል ብለን አስበንም አናውቅም፡፡</p></div>
<div>ሌላው መርማሪዬን የጠየኳት ጉዳይ ከሳሼ ማን ነው የሚል ነበር፡፡ ይህን ጥያቄ በቀጥታ ለመመለስ አልፈለገችም፡፡ምናልባትም አለቆችዋ እንዳትነግር አስጠንቅቀዋት ሊሆን ይችላል፡፡ እኔ ግን እንደተከሳሽ ቃሌን ለመስጠት ቢያንስ ከሳሼ ማን እንደሆነ የማወቅ መብቴ ሳይከበርልኝ ቀርቷል፡፡ በድፍኑ “ከሳሽ ፖሊስም ሊሆን ይችላል” ተብዬአለሁ፡፡ በስም ማጥፋት ክስ ጉዳይ ግለሰብ ከሆነ ራሱ በሚያቀርበው አቤቱታ፣የመንግስት ሹመኛ ከሆነ በዓቃቤ ሕግ በኩል ክስ ሊቀርብ እንደሚችል ያለውን ድንጋጌ አንስቶ መከራከር እዚህ ቦታ ላይ ዋጋ አልነበረውም፡፡ ያም ሆነ ይህ ከሳሼን የማወቅ መብቴ ተከልክዬ እነሆ ቃሌን ለመስጠት በቃሁ፡፡</div>
<div> በዚህ ሁኔታ ጠዋት 3፡15 ገደማ የቀድሞ ማዕካዊ የገባሁ የአምስት ሺ ብር ዋስ እስካቀርብ ድረስ የቁም አስረኛ ሆኜ ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ገደማ ግቢውን ለቅቄ ወጥቻለሁ፡፡</div>
<div>ፍሬው አበበ</div>
<div>የሰንደቅ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ</div>
</div>
</div>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2069"     class="crp_title">ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ ወደ ዝዋይ ወህኒ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1464"     class="crp_title">Hiber Radio: ኢህአዴግ ለመለወጥ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/636"     class="crp_title">&#8220;ስብሰባው&#8221;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3159"     class="crp_title">Hiber Radio: የስዬ አብርሃ ወንድም ዳግም&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1777"     class="crp_title">የአቶ መለስ ልጅ መንግስትን በጣልቃ&hellip;</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=82638</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>ለፌደረሽን ምክር ቤት ህገ መንግስት አጣሪ ጉባዔ – ጉዳዩ፤ ህገመንግሰትዊ የመብት ጥሰት ስለተካሄደብን የቀረበ አቤቱታ</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3214</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3214#comments</comments>
		<pubDate>Wed, 15 May 2013 22:11:29 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3214</guid>
		<description><![CDATA[ለፌደረሽን ምክር ቤት ህገ መንግስት አጣሪ ጉባዔ እንደሚታወቀው እኛ ባለፈዉ አመት ከመጋቢት እስከ ሰኔ 2004 ዓም ድረስ ከመኖሪያ ቀያችን ከደቡብ ኢትዮጵያ ስንባረር የነበርን ዜጎች ነን:: የመባርርና የመገፋታችን ጉዳይ ግን እስከ አሁን 2005 ዓም ድረስ ቀጥሎአል:: በቅርቡም የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስተር አቶ ሀይለማሪያም ደሳለኝ ከልዩ ልዩ ቦታዎች በህገወጥ መንገድ እየተፈናቀልን ስላለነዉ አማሮች በፓርላማ ተጠይቀዉ ሲመልሱ ማንኛዉም ዜጋ [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1505">Ethiopia: Muslim Protesters Face Unfair Trial</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2678">ግልጽ ደብዳቤ ለብፁዓን ወቅዱሳን&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1529">ርዕዮት አለሙ በወህኒቤቱ አስተዳደር</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1395">ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ 2ኛ ዓመት ቅጽ 2 ቁ</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1976">ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ 2ኛ ዓመት ቅጽ 2 ቁ</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<div id="attachment_3219" class="wp-caption alignleft" style="width: 310px"><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/Federation-Council-and-Regional-Government.jpg"><img class="size-medium wp-image-3219 " alt="Federation Council and Regional Government" src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/Federation-Council-and-Regional-Government-300x181.jpg" width="300" height="181" /></a><p class="wp-caption-text">Federation Council and Regional Government</p></div>
<p><strong>ለፌደረሽን ምክር ቤት ህገ መንግስት አጣሪ ጉባዔ</strong><br />
እንደሚታወቀው እኛ ባለፈዉ አመት ከመጋቢት እስከ ሰኔ 2004 ዓም ድረስ ከመኖሪያ ቀያችን ከደቡብ ኢትዮጵያ ስንባረር የነበርን ዜጎች ነን:: የመባርርና የመገፋታችን ጉዳይ ግን እስከ አሁን 2005 ዓም ድረስ ቀጥሎአል:: በቅርቡም የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስተር አቶ ሀይለማሪያም ደሳለኝ ከልዩ ልዩ ቦታዎች በህገወጥ መንገድ እየተፈናቀልን ስላለነዉ አማሮች በፓርላማ ተጠይቀዉ ሲመልሱ ማንኛዉም ዜጋ በየትኛዉም የኢትዮጵያ ክልል የመኖር ህገ መንግስታዊ መብት እናዳለዉ ገልጸዉ በእኛ ላይ እየተወሰድ ያለዉ እርምጃ ግን ጸረ ህገ መንግስት መሆኑን አስረግጠዉ ተናገረዋል::</p>
<h2><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/Constitutional-Inquiry.pdf" > የቀረበውን አቤቱታ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ</a></h2>
<p>&nbsp;</p>
<p>&nbsp;</p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1505"     class="crp_title">Ethiopia: Muslim Protesters Face Unfair Trial</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2678"     class="crp_title">ግልጽ ደብዳቤ ለብፁዓን ወቅዱሳን&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1529"     class="crp_title">ርዕዮት አለሙ በወህኒቤቱ አስተዳደር</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1395"     class="crp_title">ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ 2ኛ ዓመት ቅጽ 2 ቁ</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1976"     class="crp_title">ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ 2ኛ ዓመት ቅጽ 2 ቁ</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=82635</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>በሙስና ተጠርጥረው የታሰሩት ‘‘አያያዛችን ህገ-መንግስታዊ ሥርዓቱን የተከተለ አይደለም’’ አሉ (የፍርድ ቤት ውሎ)</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3201</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3201#comments</comments>
		<pubDate>Wed, 15 May 2013 14:18:35 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3201</guid>
		<description><![CDATA[‘‘አያያዛችን ህገ-መንግስታዊ ሥርዓቱን የተከተለ አይደለም’’ ተጠርጣሪዎች *‘‘እስካሁን ተከሳሽ የሚባል የለም፤ እነዚህ ሰዎች ተጠርጣሪዎች ናቸው’’ ፍርድ ቤቱ *‘‘በሚዲያ የሚተላለፈው ሪፖርት በቤተሰቦቻችን ላይ ጫና እየፈጠረ ነው’’ ተጠርጣሪዎች በአሸናፊ ደምሴ በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው የፌዴራሉ ሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን መርማሪዎች ማጣራት እያካሄዱባቸው የሚገኙት 24 ግለሰቦች የዋስትና መብታቸውን በተመለከተ በትናንትናው ዕለት የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 2ኛ ወንጀል ችሎት ቀርበው ውሳኔ ተሰጣቸው። [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3148">የናዝሬት ጉምሩክ የህግ ማስከበር&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3070">ወያኔ ባለስልጣናቱን አቶ መላኩ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3087">የታሰሩት ባለስልጣናት እና ነጋዴዎች</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1778">በአሰቃቂ ሁኔታ የቀድሞ ባለቤቱ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3198">የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በተጠርጣሪዎቹ&#8230;</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<div align="center"><b>‘‘አያያዛችን ህገ-መንግስታዊ ሥርዓቱን የተከተለ አይደለም’’</b></div>
<div><b><i>ተጠርጣሪዎች</i></b></div>
<div><b><i>*‘‘እስካሁን ተከሳሽ የሚባል የለም፤ እነዚህ ሰዎች ተጠርጣሪዎች ናቸው’’</i></b></div>
<div><b><i>ፍርድ ቤቱ</i></b></div>
<div><b><i>*‘‘በሚዲያ የሚተላለፈው ሪፖርት በቤተሰቦቻችን ላይ ጫና እየፈጠረ ነው’’</i></b></div>
<div><b><i>ተጠርጣሪዎች</i></b><b></b></div>
<div></div>
<div><b>በአሸናፊ ደምሴ</b></div>
<div></div>
<div><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/Melaku-Fenta-and-Gebrewahid-Woldegiorgis.jpg"><img class="alignleft size-medium wp-image-3202" alt="Melaku-Fenta-and-Gebrewahid-Woldegiorgis" src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/Melaku-Fenta-and-Gebrewahid-Woldegiorgis-300x153.jpg" width="300" height="153" /></a>በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው የፌዴራሉ ሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን መርማሪዎች ማጣራት እያካሄዱባቸው የሚገኙት 24 ግለሰቦች የዋስትና መብታቸውን በተመለከተ በትናንትናው ዕለት የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 2ኛ ወንጀል ችሎት ቀርበው ውሳኔ ተሰጣቸው።</div>
<div>በትናንትናው ዕለት የኮሚሽኑ መርማሪ በሦስት ክሶች ከፋፍሎ ክስ የመሰረተባቸው 24 ተጠርጣሪዎች በፍርድ ቤቱ የተገኙ ሲሆን፤ ከትናንት በስቲያ በነበረው የቃል ክርክር ወቅት ተነስቶ የነበረውን የዋስትና ጥያቄ ምላሽ ተሰጥቶበታል። በዚህም የፌዴራል ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መላኩ ፈንታ ሕገ-መንግስታዊ ስርዓቱን በጠበቀ መልኩ ከምክር ቤት አባልነታቸው መታገዳቸውን የሚያስረዳ ደብዳቤ ሊቀርብ ይገባል ያለው ፍርድ ቤቱ፤ ይህንንም ለማጣራት ለግንቦት 9 ቀን 2005 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። በመሆኑም በአንደኛ ክስና በሁለተኛ ክስ ስር የተዘረዘሩት ተጠርጣሪዎች በሙሉ ለግንቦት 19 ቀን 2005 ዓ.ም የምርመራው ፈቃድ ፀንቶባቸው የተቀጠሩ ሲሆን፤ አቶ መላኩ ፈንታን ጨምሮ በናዝሬት ጉምሩክ ባልደረቦች ስር የተጠረጠሩት ግለሰቦች ለግንቦት 9 ተቀጥረዋል።</div>
<div>በፌዴራሉ የሥነ ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን መርማሪዎች በናዝሬት ጉምሩክ ባልደረቦች ላይ የተለያዩ የኮንትሮባንድ ዕቃዎችን ወደሀገር ውስጥ እንዲገቡ በማድረግ ያልተገባ ሀብት አግኝተዋል ሲል ክሱን የዘረዘረ ሲሆን፤ ከስድስቱ ተጠርጣሪ መካከል ሁለቱ ብቻ ጠበቆቻቸውን ማግኘታቸውን በመጥቀስ ቀሪዎቹ ከጠበቆች ጋር እንዳልተገናኙ በመግለፅ ለፍርድ ቤቱ ያስረዱ በመሆናቸው፤ ፍርድ ቤቱም ከጠበቆቻቸው ጋር እንዲገናኙና ሀሳባቸውን አደራጅተው እንዲቀርቡ በማለት ለግንቦት 9 ቀን 2005 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።</div>
<div>ፍርድ ቤቱ ከትላንት በስቲያ በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት ተጠርጣሪዎቹ ለምን ከጠበቆች ጋር አልተገናኙም ለሚለው የፍርድ ቤቱ ጥያቄ በተሰጠው ምላሽ፤ በማረሚያ ቤት የሚገኙ ሰዎች ረቡዕና አርብ ብቻ በጠበቆቻቸው ጋር የሚገናኙበት አሰራር መኖሩ ተብራርቷል። በዚህም ላይ ፍርድ ቤቱ ተጨማሪ ማብራሪያ እንዲሰጠው በመጠየቅ ለግንቦት 9 ቀን 2005 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።</div>
<div>ፍርድ ቤት ከቀረቡት ተጠርጣሪዎች መካከል አብዛኞቹ በጠበቆቻቸው አማካኝነት ጉዳያቸውን ያስረዱ ሲሆን፤ ስለተከሰስንበት ወንጀል በቅጡ የምናውቀው ነገር የለም። አያያዛችን ህገ-መንግስታዊ ሥርዓቱን የተከተለ አይደለም። ሰሞኑን በሚዲያ እየተነገረ ያለው ነገር ትክክል ያልሆነና የቤተሰቦቻችንን አንገት ያስደፋ ነው ሲሉ ቅሬታቸውን አሰምተዋል።</div>
<div>ፍርድ ቤቱ በበኩሉ ‘‘በምንም መልኩ ቢሆን እስካሁን ተከሳሽ የሚባል ነገር የለም፤ እነዚህ ሰዎች ተጠርጣሪዎች ናቸው’’ ሲል ዐቃቤ ሕግ ክስ ባልመሰረተበት ሁኔታ ተጠርጣሪዎቹ በተሳሳተ ስም መጠራት የለባቸውም ብሏል።</div>
<div>በኮሚሽኑ መርማሪዎች ሁለተኛ ክስ ስር የፌዴራሉ የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ገብረዋህድ ወልደጊዮርጊስን ጨምሮ ባለቤታቸው ኮሎኔል ሃይማኖት ተስፋዬ እና እህታቸው ወ/ሮ ንግስት ተስፋዬን ከነልጅዋ እንዲሁም ሌሎች በድምሩ 12 የሚደርሱ ተጠርጣሪዎች የቀረቡ ሲሆን፤ የተጠረጠሩበት ወንጀልም ወደሀገር ውስጥ እንዳይገባ የተከለከለን ሲሚንቶ እንዲገባ በማድረግ፣ በኮንትሮባንድ የተሰማሩ ሰዎችን በማገዝ፣ ከተጠርጣሪዎችም መካከል የሁለቱን ክስ የሚደግፉ ሠነዶችን ማሸሽ በሚሉ ወንጀሎች እጠይቃቸዋለሁ ይላል።</div>
<div>አቶ ገብረዋህድ ወልደጊዮርጊስ በጠበቃቸው አማካኝነት እንዳስረዱት ‘‘ቤተሰቤ ተበትኗል፤ ልጄ ለትምህርት የሚገለገልበት ላፕቶፕ ተወስዶበታል። ባለቤቴንም ህጉን ባልተከተለ መንገድ ልብስ አስወልቀው ጭምር ፈትሸዋታል፤ ልታሸሽ ነበር ተብሎ የተያዘውም ካርታ ፎቶ ኮፒው መሆኑንና ዋናው በፌዴራሉ ሥነ-ምግባና ፀረ-ሙስና መርማሪዎች እጅ እንደሚገኝም ጭምር አስረድተዋል።</div>
<div>በሌላም በኩል ተጠርጣሪዎቹም በማረሚያ ቤት የተቀበላቸው አያያዝ መልካም አለመሆኑን በመጥቀስ ለፍርድ ቤቱ ያስረዱ ሲሆን፤ ፍርድ ቤቱም ተጠርጣሪዎቹ በማረሚያ ቤት ቆይታቸው ሕገ-መንግሥታዊ መብታቸው እንዲጠበቅላቸው ሲል ትዕዛዝ ሰጥቷል።</div>
<div>የፌዴራሉ የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና መርማሪ ቡድን በሙስና ተጠርጥረው ጉዳያቸውን ለፍርድ ለማቅረብ በተሰናዳባቸው 24 ግለሰቦች ላይ ሦስት ክሶችን የመሰረተ ሲሆን፤ በ1ኛ ክስ ስር በእነ አቶ መላኩ ፈንታ መዝገብ ውስጥ የሚገኙት 7 ተጠርጣሪዎች አቶ እሸቱ ወ/ሰማያት፣ አቶ መርክነህ አለማየሁ፣ አቶ አስመላሽ ወ/ማርያም፣ አቶ ከተማ ከበደ፣ አቶ ስማቸው ከበደ እና ዶክተር ፍቅሩ ማሩ ይገኙበታል። እነዚህ ቀረጥና ታክስን በማጭበርበርና አራጣ በማበደር የተከሰሱ ግለሰቦች እንዲቋረጥ በማድረግ ወንጀል ተከሰዋል።</div>
<div>በሁለተኛው የክስ ዝርዝር ውስጥ አቶ ገብረዋህድ ወልደጊዮርጊስን ጨምሮ አቶ በላቸው በየነ፣ አቶ ጥሩነህ በርታ፣ አቶ ተስፋዬ አበበ፣ አቶ ነጋ ገ/እግዚአብሔር፣ አቶ ምህረተአብ ካሳ፣ አቶ ሙሌ ጋሻው፣ አቶ አሞኘ ታገለ፣ ኮሎኔል ሃይማኖት ተስፋዬ፣ አቶ ሀብቶም ገብረመድህን እና ወ/ሮ ንግስቲ ተስፋዬን ጨምሮ በመጨረሻ የተቀላቀሉትን 12ኛ ተከሳሽ አቶ ተወልደ ብስራትን ያጠቃልላል። በዚህም ክስ ስር ተጠርጣሪዎቹ ፈፀሙት የተባለው ወንጀል ወደሀገር ውስጥ እንዳይገባ የተከለከለን ሲሚንቶ እንዲገባ በማድረግ፣ በኮንትሮባንድ የተሰማሩ ግለሰቦችን በማገዝ፣ ከተጠርጣሪዎች መካከል የሁለቱን ክስ የሚደግፍ ሰነድ ለማሸሽ ጭምር የሚል ይገኝበታል።</div>
<div>በሦስተኛ ክስነት የተጠቀሰው የናዝሬት ጉምሩክ ባለስልጣናትን የሚመለከት ሲሆን፤ በዚህም ስር አቶ መሃመድ ኢሳን ጨምሮ 6 ተጠርጣሪዎች የተዘረዘሩ ሲሆን፤ እነሱም አቶ ሰመረ ንጉሴ፣ አቶ ዘሪሁን ዘውዴ፣ ወ/ሮ ማርሸት ተስፋዬ፣ አቶ ሙሉቀን ተስፋዬ እና አቶ ዳኜ ስንሻው ይገኙበታል። የተጠረጠሩበት የወንጀል ክስም በኮንትሮባንድ የተለያዩ ዕቃዎች ወደሀገር ውስጥ እንዲገቡ በማድረግና ያልተገባ ሀብትን ማካበት የሚሉት ይጠቀሳሉ።</div>
<div>በትናንትናው ዕለት በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 2ኛ ወንጀል ችሎት ጉዳዩን ለመከታተል ከተገኘው በመቶዎች የሚቆጠር ሕዝብ መካከል ወደ ችሎት መግባት የቻለው ጥቂቱ ሲሆን፤ በአዳራሹ ጠባብነት ምክንያት በተለይም ጋዜጠኞች ቦታ ሊያገኙ አለመቻላቸው ትኩረትን ስቦ ነበር። አንዳንድ የተጠርጣሪዎቹ ቤተሰቦችም ችሎቱ በሰፊ አዳራሽ ቢካሄድ የተሻለ ይሆን እንደነበር አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።n (ምንጭ ሰንደቅ ጋዜጣ የዛሬ ሜይ 15 2013 ዕትም)</div>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3148"     class="crp_title">የናዝሬት ጉምሩክ የህግ ማስከበር&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3070"     class="crp_title">ወያኔ ባለስልጣናቱን አቶ መላኩ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3087"     class="crp_title">የታሰሩት ባለስልጣናት እና ነጋዴዎች</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1778"     class="crp_title">በአሰቃቂ ሁኔታ የቀድሞ ባለቤቱ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3198"     class="crp_title">የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በተጠርጣሪዎቹ&hellip;</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=82623</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በተጠርጣሪዎቹ ላይ  በጥንቃቄ የታጀበ መግለጫ ሰጠ</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3198</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3198#comments</comments>
		<pubDate>Wed, 15 May 2013 14:16:16 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3198</guid>
		<description><![CDATA[·        ተጠርጣሪዎቹን ለመያዝ የታሰበው ከአቶ መለስ ህልፈት በፊት ነው ·        ተጨማሪ እርምጃ እንደሚወሰድ ኮሚሽነሩ ፍንጭ ሰጥተዋል ·        በተጠርጣሪዎቹ ላይ የተወሰደው እርምጃ ታስቦበት እንጂ በግርግር አይደለም ብለዋል በዘሪሁን ሙሉጌታ  የፌዴራል የስነ-ምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ዓሊ ሱሌይማን ሰሞኑን በድንገት በቁጥጥር ስር በዋሉት ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናትና ባለሀብቶችን በተመለከተ በጥንቃቄ የተሞላ መግለጫ ሰጡ። በመግለጫው ላይ በርካታ ጋዜጠኞች ተገኝተው ለኮሚሽነሩ በርካታ ጥያቄዎች ለማቅረብ [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/705">የጁኔይዲ ሳዶን ወደ ኬኒያ መሰደድ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/588">ደውሉ ይጮሐል!!</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/180">የኢሕአዴግ ከፍተኛ የመንግስት&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1538">ለጠቅላይ ሚኒስትሩ አቤቱታ ያቀረቡ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3201">በሙስና ተጠርጥረው የታሰሩት&#8230;</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<div align="center">·        <b><i>ተጠርጣሪዎቹን ለመያዝ የታሰበው ከአቶ መለስ ህልፈት በፊት ነው</i></b></div>
<div align="center">·        <b><i>ተጨማሪ እርምጃ እንደሚወሰድ ኮሚሽነሩ ፍንጭ ሰጥተዋል</i></b></div>
<div align="center">·        <b><i>በተጠርጣሪዎቹ ላይ የተወሰደው እርምጃ ታስቦበት እንጂ</i></b></div>
<div align="center"><b><i>በግርግር አይደለም ብለዋል</i></b></div>
<div></div>
<div><b><i>በዘሪሁን ሙሉጌታ </i></b></div>
<div></div>
<div><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/Commission.jpg"><img class="alignleft size-thumbnail wp-image-3199" alt="Commission" src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/Commission-150x150.jpg" width="150" height="150" /></a>የፌዴራል የስነ-ምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ዓሊ ሱሌይማን ሰሞኑን በድንገት በቁጥጥር ስር በዋሉት ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናትና ባለሀብቶችን በተመለከተ በጥንቃቄ የተሞላ መግለጫ ሰጡ።</div>
<div>በመግለጫው ላይ በርካታ ጋዜጠኞች ተገኝተው ለኮሚሽነሩ በርካታ ጥያቄዎች ለማቅረብ ቢፈልጉም ጋዜጣዊ መግለጫው በአጭሩ እንዲከናወን ተደርጓል። በዚሁ ጥንቃቄ በተደረገበት መግለጫ ላይ ኮሚሽነር ዓሊ ተጠርጣሪዎችን ለመያዝ ጥናትና ክትትል ሲደረግ የቆየው ከሁለት ዓመት በፊት አቶ መለስ በህይወት በነበሩበት ወቅት መሆኑን አረጋግጠዋል። ኮሚሽኑ በቀጣይም እርምጃ እንደሚወስድ ፍንጭ የሰጡ ሲሆን በተጠርጣሪዎቹ ላይ የተወሰደው እርምጃ ታስቦበት እንጂ “በቱማታ” አይደለም ሲሉ ተናግረዋል።</div>
<div>ችግሩ የቆየ ከሆነ አሁን ለምን እርምጃ ተወሰደ ተብለው የተጠየቁት ኮሚሽነሩ ሲመልሱ፤ “ጠመንጃ የያዘ ሰው “ኮሽ” ባለ ቁጥር አይተኩስም” እርምጃ ከመውሰዱ በፊት ግምት ውስጥ መግባት ያለባቸው ጉዳዮች ነበሩ። ከነዚህም ውስጥ ደግሞ የዜጎችን ሕገ-መንግስታዊ መብት ሳይነካ በቂ ማስረጃ መሰብሰብ በማስፈለጉ ነው” ብለዋል። ሙስናም ቀጣይ ትግል በመሆኑ እርምጃው ዘግይቷል ሊባል አይቻልም ሲሉ ተናግረዋል። በሌሎችም መስሪያቤቶች ክትትሉ ይቀጥላል ሲሉ አረጋግጠዋል።</div>
<div>“ትልልቅ የመንግስት ኃላፊዎችን መያዝ ድፍረቱ ከዬት ተገኘ?” ለሚለው የጋዜጠኞች ጥያቄ ኮሚሽነሩ ሲመልሱ ከዚህ በፊትም ትላልቅ የመንግስት ኃላፊዎች ክስ ሲመሰርት መቆየቱን ጠቅሰው የኮሚሽኑ ትኩረት ወንጀሉ ላይ እንጂ ግለሰቦቹ ላይ አለመሆኑን ተናግረዋል።</div>
<div>በቂ ማስረጃ ካላችሁ ለምን ተጨማሪ የጊዜ ቀጠሮ መጠየቅ አስፈለጋችሁ ለተባሉት ኮሚሽነሩ ሲመልሱ ይዞ ለመመርመር የሚያበቃ ማስረጃ እና ለፍርድ ቤት አሳማኝ ማስረጃ ማቅረብ የተለያዩ በመሆኑ ነው ብለዋል።</div>
<div>የተጠርጣሪዎቹን ልጆች (ተማሪዎች) ለምን ያዛችሁ ለሚለው ጥያቄም የማውቀው ነገር የለም ብለዋል። ምርመራውም በተጠርጣሪዎቹ ላይ ብቻ እንደሆነ ገልፀዋል።<a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/ali.jpg"><img class="alignright size-full wp-image-3207" alt="ali" src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/ali.jpg" width="183" height="276" /></a></div>
<div>በቁጥጥር ስር ከዋሉ ተጠርጣሪዎች መካከል ያለመከሰስ መብታቸው ሳይነሳ ለምን አሰራችሁ? ተብለው ኮሚሽነሩ ቢጠየቁም ያለመከሰስ መብት ሊነሳ ይችላል በሚል ብዙም ግልፅ ያልሆነ መልስ ሰጥተዋል።</div>
<div>ተጠርጣሪዎቹን ለመያዝ የባለሥልጣናት የሐብት ምዝገባው አግዟችኋል ወይ ለተባሉት “አግዞናል” በሚል አጭር መልስ ሰጥተዋል። ወደፊትም በግብር ጉዳይ ላይ ኮሚሽኑ ያተኩራል ብለዋል። እርምጃው የፖለቲካ ጉዳይ ስለመሆኑም ተጠይቀው በሀገራችን ብቻ ባይሆን በሌሎች አገሮችም የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣን ሲያዙ ጉዳዩ “ፖለቲካ ነው” መባሉ አይቀርም። ወደፊት የፖለቲካ ኬዝ እንዳልሆነ በፍርድ ቤቱ ውሳኔ እናሳያለን በማለት በአጭሩ መልሰዋል።</div>
<div>ከሀገር ውጪ ስለኮበለለ ሀብትም ተጠይቀው ለጊዜው አስፈላጊ አይደለም። ነገር ግን በርካታ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር ተጋግዘን እንሰራለን ሲሉ መልሰዋል።¾  (ምንጭ  ሰንደቅ ጋዜጣ የዛሬ ዕትም)</div>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/705"     class="crp_title">የጁኔይዲ ሳዶን ወደ ኬኒያ መሰደድ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/588"     class="crp_title">ደውሉ ይጮሐል!!</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/180"     class="crp_title">የኢሕአዴግ ከፍተኛ የመንግስት&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1538"     class="crp_title">ለጠቅላይ ሚኒስትሩ አቤቱታ ያቀረቡ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3201"     class="crp_title">በሙስና ተጠርጥረው የታሰሩት&hellip;</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=82624</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>ሰር አሌክስ ፈርጉሰን በቁጥሮች</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3204</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3204#comments</comments>
		<pubDate>Wed, 15 May 2013 13:21:18 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3204</guid>
		<description><![CDATA[ከይርጋ አበበ 26 : 38 በስታዲየሙ የተሰቀለው የውጤት ማሳያ ኤሌክትሮኒክስ ሰሌዳ የፈርጉሰንን ከኦልድ ትራፎርድ መለዬት በማስመልከት ያስነበበው ጽሑፍ ነው ።ለዚህ ጽሑፌ ርዕስ ያደረኩት ይህ ቁጥር አሰልጣኙ በክለቡ የቆዩባቸውን ዓመታት እና ያገኟቸውን ዋንጫዎች ብዛት ለመግለፅ የተጠቀሙበት ገለፃ ነው። በሃያ ስድስት ዓመታት የተገኙ ሰላሳ ስምንት ዋንጫዎችን ወደ ክለቡ የዋንጫ መደርደሪያ ማምጣት የቻሉት ሰር አሌክስ ፣ከጨዋታው በኋላ በስታዲየሙ [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3067">ዴቪድ ሞይስ ሰር አሌክስ ፈርጉሰንን&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2614">አሥሩ ዋንጫዎች:- አሥሮቹ ጀግኖችና&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2663">አሥሩ ዋንጫዎች:- አሥሮቹ ጀግኖችና&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2289">የማንቸስተር ዩናይትድ አስገራሚ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3103">የ2012/2013 የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ&#8230;</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p>ከይርጋ አበበ</p>
<p><strong><em>26 : 38 በስታዲየሙ የተሰቀለው የውጤት ማሳያ ኤሌክትሮኒክስ ሰሌዳ የፈርጉሰንን ከኦልድ ትራፎርድ መለዬት በማስመልከት ያስነበበው ጽሑፍ ነው ።ለዚህ ጽሑፌ ርዕስ ያደረኩት ይህ ቁጥር አሰልጣኙ በክለቡ የቆዩባቸውን ዓመታት እና ያገኟቸውን ዋንጫዎች ብዛት ለመግለፅ የተጠቀሙበት ገለፃ ነው።</em></strong><br />
<strong><em>በሃያ ስድስት ዓመታት የተገኙ ሰላሳ ስምንት ዋንጫዎችን ወደ ክለቡ የዋንጫ መደርደሪያ ማምጣት የቻሉት ሰር አሌክስ ፣ከጨዋታው በኋላ በስታዲየሙ ለታደሙት የክለቡ ደጋፊዎች እና ተጫዋቾች ንግግር አድርገዋል ። በንግግራቸውም እስካሁን በክለቡ ለነበራቸው ቆይታ የተደረገላቸውን እንክብካቤ አድንቀዋል ፤ለክለቡ ውጤት ቀጣይነት ሲባል ለሳቸው የተደረገው ለተተኪው አሰልጣኝም እንዲደረግላቸው ደጋፊዎቹን ተማጽነዋል። ተጫዋቾቹም ለለበሱት ማሊያ ፍቅር እንዲኖራቸው እና ለክለባቸው ውጤት ማማር ጠንክረው እንዲሰሩ አሳስበዋል።</em></strong><br />
<strong><em>  ህዳር ወር መጨረሻ ላይ ማሰልጠን የጀመሩትን ክለብ ለመሰናበት ጫፍ ላይ የደረሱት አሰልጣኝ ሰር አሌክስ ፈርጉሰን በማንቸስተር የመጨረሻ ዓመት ቆይታቸው የመጨረሻ ዋንጫቸውን በኦልድ ትራፎርድ ያደረጉትን የመጨረሻ ጨዋታ የዌልሱን ክለብ ሁለት ለባዶ በማሸነፍ መጨረሻቸውን አሳምረው ለመውጣት በቅተዋል።  በታላቁ ኦልድ ትራፎርድ ስታዲየም በልዩ ትዕይንት የተጀመረውና ከሰባ ሺ በላይ ቀያይ ባንዲራዎች አሸብርቆ በከፍተኛ ድጋፍ የታጀበው የእሁድ ምሽቱ ጨዋታ ከሰር አሌክስ በተጨማሪ አንጋፋውን ፖል ስኮልስንም ለሁለተኛ ጊዜ ለመሸኘት የተመቸ አጋጣሚ ነበር።  የሰቀለውን ጫማ በሰር አሌክስ ልመና አውርዶ በማጥለቅ ለቀያይ ሰይጣኖቹ ከፍተኛ አገልግሎትን መስጠት የቻለው ፖል ስኮልስ ከአሰልጣኙ ጋር በክብር ለመሸኘት ችሏል።</em></strong><br />
<strong>  ሰር አሌክስ ፈርጉሰን በቁጥሮች</strong><br />
<a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/fergusen.jpg"><img class="alignleft size-medium wp-image-3011" alt="fergusen" src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/fergusen-300x185.jpg" width="300" height="185" /></a>2ፈርጊ ከማንቸስተር ዩናይትድ ጋር ማግኘት የቻሉት የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫ ብዛት<br />
5 በፈርጉሰን የሰለጠኑቡድኖች ብዛት ሲሆን፡ ኢስት ስቲርሊንግ፣ ሴይንት ሜሪ፣ አበርዲን፣ የስኮትላንድ ብሄራዊ ቡድን እና ማንቸስተር ዩናይትድ<br />
6 በተጫዋችነት ዘመናቸው ሰር አሌክ የተጫወቱባቸው ክለቦች፡ ኩይን ፓርክ፣ ሴይንት ጆንስተን፣ ደንፈርምሊን፣ ፋልክሪክ እና አይር የተባሉ የስኮትላንድ ክለቦች<br />
9 የሰባ አንድ ዓመቱ የቀድሞ የማንቸስተር ዩናይትድ አሰልጣኝ ያገኟቸው የኤፍ ኤ ካፕ ዋንጫዎች ቁጥር አምስቱን በማን ዩናይትድ አራቱን በአበርዲን<br />
26 ስኮትላንዳዊው አዛውንት በኦልድ ትራፎርዱ ክለብ የነበራቸው ቆይታ በዓመት፡- ይህንን ያህል ዓመት ማንቸስተር ዩናይትድን ያሰለጠነ አሰልጣኝ የለም።<br />
38 የእንግሊዙ ክለብ ባለፉት ሃያ ስድስት ዓመታት በሰር አሌክስ ፈርጉሰን አሰልጣኝነት ያገኛቸው ዋንጫዎች ብዛት፡- ይህንን ያህል የዋንጫ ብዛት መደርደሪያው ላይ የሰቀለ አሰልጣኝ ሲቪው ላይ የተፃፈለት አሰልጣኝ ከሰር አሌክስ ውጪ ማንም የለም።<br />
104 ሰር አሌክስ በሃያ ስድስት ዓመታት ቀዩን ማሊያ ለማልበስ ወደ ክለባቸው ያስመጧቸው ተጫዋቾች፡- ለመጨረሻ ጊዜ ያስፈረሙት ትውልደ አይቮሪኮስታዊው ክሪስቶፎር ዛሃ ሲሆን ባለፈው ጃንዋሪ ወር በተከፈተው የተጫዋቾች ዝውውር በ15ሚሊዮን ፓውንድ ገዝተው ለአሳዳጊ ክለቡ በውሰት ሰጥተውታል። በፈርጊ ተገዝቶ ለፈርጉሰን ቡድን መጫወት ያልቻለ ተጫዋች።<br />
170 ውጤታማው አሰልጣኝ በተጫዋችነት ዘመኑ ለተሰለፈባቸው ክለቦች ያስቆጠሩት ግብ ድምር፡-  ፈርጊ ላለፉት ሃያ ስድስት ዓመታት ወደ ማንቸስተር ካዘዋወሯቸው 104 ተጫዋቾች ውስጥ የሚበዛውን ቁጥር የሚይዙት አጥቂዎች መሆናቸው አሰልጣኙ ውጤታማ የአጥቂ መስመር ተጫዋች እንደነበሩ ማሳያ ነው ሲሉ የሚያውቋቸው ይናገራሉ።<br />
370 ቁምጣና ማሊያ ለብሰው ወደ ሜዳ የገቡበት የጨዋታ ብዛት፡- ለስድስት ክለቦች በአጠቃላይ መሰለፍ የቻሉት የጨዋታ ብዛት 370 ብቻ ሲሆን በነዚህ ጨዋታዎች 170 ግቦችን ማስቆጠር መቻላቸው እውነተኛ የጎል ማሽን ነበሩ ያስብላል።<br />
1499 ማንቸስተር ዩናይትድን እየመሩ ወደሜዳ የገቡባቸው ጨዋታዎች፡- ከሳምንት በኋላ 1500ኛ ጨዋታቸውን የሚያደርጉ ሲሆን፡- እስካሁን ግን 1499 ጨዋታዎችን አድርገው 895ቱን ማሸነፍ ችለዋል።<br />
የፈርጉሰን ምርጥ አስራ አንድ<br />
የእንግሊዙ ዘ ኢንዲፔንደንት ጋዜጣ የሃያ ስድስት ዓመት የሰር አሌክስ ፈርጉሰንን ምርጥ 11 ፈራሚዎች እንዲመረጡ በበተነው መጠይቅ መሰረት የአብላጫውን ድምፅ ያገኙትን አስራ አንድ ተጫዋቾች እንዲህ እናቀርባቸዋለን።<br />
1. ፒተር ሺማይክል ምርጡ የፈርጊ ግብ ጠባቂ<br />
2. ጋሪ ኔቭል ዝምተኛው ጀግና<br />
3. ፓትሪስ ኢቭራ የፈርጉሰንን ክፍተት የደፈነ ምርጥ የኋላ መስመር ተጫዋች<br />
4. ያፕ ስታም ደፋር እና አይደክሜ ሆላንዳዊ<br />
አማካይ መስመር<br />
5 . ክርስቲያኖ ሮናልዶ የዓለማችን ውዱ ተጫዋች የፈርጊ ምርጥ ፖርቹጋላዊ ፈራሚ<br />
6 . ሪያን ጊግስ የአንድ ክለብ ማሊያ ብቻ ገላው የለመደው ዌልሳዊ ምርጥ ባለ ግራ እግር<br />
7 . ሮይ ኪን አየርላንዳዊው ጉልበተኛ በማንቸስተር አሻራው የማይተካ ሚና ነበረው<br />
8. ፖል ስኮልስ ምርጡ እንግሊዛዊ ለፈርጉሰን ቡድን ያልከፈለው አልነበረም<br />
የአጥቂ መስመር<br />
10. ዋይኒ ማርክ ሩኒ በማንቸስተር ያለው ቆይታ ያልተረጋገጠው የኤቨርተን አካዳሚ ፍሬ ከምርጦቹ የፈርጊ ፈራሚዎች አንዱ ለመሆን ጊዜ አለፈጀበትም<br />
11. ኤሪክ ካንቶና የአንድ ሚሊዮን ፓውንድ ወጪ የሆነበት ፈረንሳዊ አመለ ብልሹ ከ1995-98 የማንቸስተር ዩናይትድ ውጤት ግምባር ቀደም ተጠቃሽ ነበር።</p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3067"     class="crp_title">ዴቪድ ሞይስ ሰር አሌክስ ፈርጉሰንን&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2614"     class="crp_title">አሥሩ ዋንጫዎች:- አሥሮቹ ጀግኖችና&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2663"     class="crp_title">አሥሩ ዋንጫዎች:- አሥሮቹ ጀግኖችና&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2289"     class="crp_title">የማንቸስተር ዩናይትድ አስገራሚ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3103"     class="crp_title">የ2012/2013 የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ&hellip;</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=82625</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>ከሙስናው በስተጀርባ (ከኢየሩሳሌም አርአያ)</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3194</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3194#comments</comments>
		<pubDate>Wed, 15 May 2013 12:11:21 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3194</guid>
		<description><![CDATA[ከኢየሩሳሌም አርአያ በሕወሐት የተፈጠረው የቀውስ ማእበል አድማሱን እየለጠጠ መሔዱን ተከትሎ «ታማኝ» ሆነው በሙስና ሲያገለግሉ የቆዩትን ጭምር እየበላ እንደሚገኝ የቅርብ ምንጮች አስታወቁ። በቀዳሚነት የሚያነሱት በጉምሩክ ቁልፍ ስልጣን የነበረውን የሕወሐት አባል ገ/ዋህድ ወ/ጊዮርጊስን ሲሆን እንዴትና በማን ወደስልጣን እንደመጣ እንዲሁም ምን-ምን ተግባራት ይፈፅምና ያስፈፅም እንደነበረ ምንጮቹ ሂደቱን እንደሚከተለው ይገልፁታል። ገ/ዋህድ በ1993ዓ.ም ፓርቲው ለሁለት መሰንጠቁን ተከትሎ ወደ ስልጣን እንዲመጣ [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/799">የሰላማዊ ትግል በብዙሃን መጋናኛ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3087">የታሰሩት ባለስልጣናት እና ነጋዴዎች</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1124">የ255ቱን የኢሕአዴግ ሥራ አስፈጻሚዎች</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/contact-us">Contact Us</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1845">ልጆችን ማሳደግ በምዕራብ ሀገር &#8211;</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p><em><span style="font-size: large;">ከኢየሩሳሌም አርአያ</span></em></p>
<p><span style="font-size: large;"><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/tplf-rotten-apple-245x300.png"><img class="size-thumbnail wp-image-3195 alignright" alt="tplf-rotten-apple-245x300" src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/tplf-rotten-apple-245x300-150x150.png" width="150" height="150" /></a>በሕወሐት የተፈጠረው የቀውስ ማእበል አድማሱን እየለጠጠ መሔዱን ተከትሎ «ታማኝ» ሆነው በሙስና ሲያገለግሉ የቆዩትን ጭምር እየበላ እንደሚገኝ የቅርብ ምንጮች አስታወቁ። በቀዳሚነት የሚያነሱት በጉምሩክ ቁልፍ ስልጣን የነበረውን የሕወሐት አባል ገ/ዋህድ ወ/ጊዮርጊስን ሲሆን እንዴትና በማን ወደስልጣን እንደመጣ እንዲሁም ምን-ምን ተግባራት ይፈፅምና ያስፈፅም እንደነበረ ምንጮቹ ሂደቱን እንደሚከተለው ይገልፁታል።</span></p>
<p><span style="font-size: large;">ገ/ዋህድ በ1993ዓ.ም ፓርቲው ለሁለት መሰንጠቁን ተከትሎ ወደ ስልጣን እንዲመጣ ተደረገ። ከጉምሩክ ሃላፊነት በተጨማሪ የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ምክትል ዳይሬክተርነት ስልጣን እንዲጨብጥ የተደረገው በአቶ መለስ በተለይ በአዜብ ይሁንታ ጭምር እንደነበረ ምንጮቹ ይጠቁማሉ። ገ/ዋህድ ለዚህ ስልጣን የበቃው ለአቶ መለስ ቡድን በከፈለው መስዋእትነት ሲሆን በክፍፍሉ ማግስት የሙስና ዘመቻ ተከፍቶ እነአባተ ኪሾና ሌሎች እስር ቤት እንዲገቡ ቀጥተኛ ትእዛዝ ከመስጠት አንስቶ ራሱ ክስ አዘጋጅ፣ምስክርና ፈራጅ..በመሆን የላቀ ሚና መጫወቱን ያስታውሳሉ። በዚህ ተግባሩ የበለጠ ታማኝነቱን በማሳየቱ ከአዜብ በሚሰጠው ቀጥታ ትእዛዝ ሙስናውን ማከናወን መቀጠሉን ምንጮቹ አያያዘው ይጠቁማሉ። በ10ሺህ ቶን የሚገመት ቡና ከአዜብ በተቀበለው ትእዛዝ በህገወጥ መንገድ ከአገር ተዘርፎ የተሸጠበትና ጉዳዩም በፓርላማ ተነስቶ በጠ/ሚ/ሩ «የሌቦቹን እጅ እንቆርጣለን» የሚል አስቂኝ ምላሽ መሰጠቱን ያስታውሳሉ። በተጨማሪ በጉምሩክ ለረጅም አመት በመምሪያ ሃላፊነት ሽፋን የተቀመጠውና የቢሮውን የበላይ ሃላፊዎች በጥብቅ ከመቆጣጠር ጀምሮ እያንዳንዱን የሙስና ተግባር ከጀርባ ሆኖ የሚያስፈፅመው የአዜብ የቅርብ ስጋ ዘመድ ፍትሃነገስት ክንደያ እንደሚጠቀስና ግለሰቡ ቀረጥ ያልተከፈለባቸው 500 ሳተላይት ዲሾች እንዲገቡና በአዜብ በበላይነት ይመራ ለነበረው የዘረፋ ቡድን ለሰባት አመታት በየወሩ 20ሚሊዮን ከቴሌ በህገወጥ መንገድ እንዲዘረፍ ያደረገና በኋላም ከነገ/ዋህድ ጋር ሆኖ በርካታ ሙስናዎችን በዋናነት በማስፈፀም እንደሚጠቀስ ያመለክታሉ።</span></p>
<p><span style="font-size: large;">በሌላም በኩል የገ/ዋህድ ባለቤት ኰ/ል ሃይማኖት ስትጠቀስ ከሕወሐት አንጋፋ ሴት ታጋዮች አንዷ ናት፤ ከጡረታ ጋር በተያያዘ ከመከላከያ በመልቀቅ በአዜብ የበላይነት በሚመራው የሴቶች እና ኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ቢሮ መስራት ቀጠለች። ለዚህ ቢሮ ከአሜሪካ መንግስት ብቻ በአመት እስከ 240ሚሊዮን ዶላር ይለገሳል። ገንዘቡ ለሚመለከታቸው ወገኖች ሳይሆን የሚውለው የነአዜብ ኪስ ማደለቢያ ሆኖ እንደሚዘረፍ ያመለከቱት ምንጮች ይህም ጉዳይ በፓርላማ ለቀድሞ ጠ/ሚ/ር ተነስቶ « ከእንግዲህ ቁጥጥር እናደርጋለን» የሚል የተድበሰበሰ ምላሽ እንድተሰጠ ያስታውሳሉ። ባልና ሚስቱን በተለያየ ወጥመድ በማስገባት የሙስና ጋሻ-ጃግሬ አድርገው የቆዩት አዜብ እንዲሁም ሌሎቹ ቱባ ባለስልጣናት መጠነ-ሰፊ ዘረፋና ሙስና ጉዳይ ሳይነካ ግልገሎቹን ብቻ (ያውም በአስፈፃሚነት ራሳቸው የመደቧቸውን) ተጠያቂ ማድረግ ተራ ድራማ ነው ሲሉ ምንጮቹ ያጣጥሉታል። በማስረጃነትም፥ 400 ሚሊዮን ብር ለ«ራዲሰን ሆቴል ግንባታ» በሚል ሽፋን በመፍቀድ 150ሚሊዮን ኪሳቸው ከከተቱትና በርካታ ብድሮችን በመፍቀድ (የስጋ ዘመዶቻቸውን ደላላ በማድረግ…) በሙስና የደለቡት አባይ ፀሃዬ ጨምሮ፣ የበታች ሙሰኞች ላይ &lt;ምስክር&gt; ሆነው የቀረቡትና ከአዜብ ጋር በሙስና የሰከሩት አባዱላ ገመዳ፣ የተለያዩ ድርጅቶች ባለቤት ስብሃት ነጋ፣ የቱጃሩን የቢሊዮን ብድር በግል ከመፍቀድ አንስቶ የታዋቂ ባለሃብቶች &lt;ቀኝ እጅ&gt; የሆኑትና ሚስታቸውን ጭምር በሙስና ያሰማሩት በረከት ስምኦን፣ ሶፍያን አህመድ፣ እንዲሁም ቪላዎችን ከ8 እስከ 10 ሚሊዮን ብር ወጪ በማስገንባትና በማከራየት የአገር ሃብት የሚዘርፉ ሁሉም የገዢው ትላልቅ ባለስልጣናት የሙስና ጉዳይ በዋቢነት ይጠቅሳሉ። ባጠቃላይ የስርአቱ ቁንጮዎች የሚያናቁራቸው የገዛ ጥቅምን ከማስጠበቅና አንዱ ጎራ ከሌላው በልጦ በሙስና የሚከብርበትን መንገድ ለማመቻቸት ብሎም ሌላኛውን በመጨፍለቅ ስልጣኑን ከነታማኝ ተከታዮቹ አስጠብቆ የሚቀጥልበትን ብቻ እንደሚያልም የጠቆሙት ምንጮቹ፣ ስርአቱ የአስተዳደር፣የፖለቲካ፣ የፖሊሲ…ወዘተ ልዩነት እንደሌለበት ያሰምሩበታል።</span></p>
<p><span style="font-size: large;">ሌላው ዘብጥያ የወረዱት ባለሃብት አቶ ነጋ ገ/እግዚያብሄር ናቸው፤ የአቶ ነጋ ባለቤት የቀድሞ የሜጋ ኪነጥበብ ሃላፊ እቁባይ በርሄ እህት ናት። ከጥቂት ወራት በፊት ከሙስና ጋር በተያያዘ አስገራሚ ፍርድ የተሰጠውና ጥፋተኛ ተብሎ የተለቀቀው እቁባይ ያንን አይን ያወጣ «ፍርድ» እንዲያገኝ የተደረገው ከአዜብ በተሰጠ ቀጭን ትእዛዝ ነው ያሉት ምንጮቹ ይህ ሊሆን የቻለው አዜብ ከአቶ ነጋ ጋር ባላቸው የቢዝነስ ትስሥር ጭምር መሆኑን አያይዘው ይገልፃሉ። (ሌላም አሳፋሪ ቁርኝት ቢኖራቸውም ለጊዜው ማለፍ ይመረጣል)…</span></p>
<p><span style="font-size: large;">በሌላም በኩል የስዬ አብርሃ ወንድም ምህረተአብ አብርሃ እንዲሁም አይነስውሩ አስመላሽ ወ/ስላሴ ይጠቀሳሉ፤ ምህረተአብ ከስዬ ጋር ተፈርዶበት የተለቀቀው ከአምስት አመት በፊት ሲሆን አሁን ደግሞ ከነገ/ዋህድ ክስ ጋር በተያያዘ አብሮ እንዲቀላቀል ተደርጎዋል።…. አይነስውሩ አስመላሽ (በቅፅል ስማቸው አባይ ነብሶ) በፓርላማ የሕግ ጉዳይ ቢሮን ሲመሩ የቆዩ ናቸው፤ በሕወሐት ክፍፍል ጊዜ እያለቀሱ ፓርቲው እንዳይፈርስ ሲማፀኑ እንደነበር ያስታወሱት ምንጮቹ በተለይ በአንድ ቀን ተፅፎ እንዲወጣ የተደረገውንና አንድ ሰው ለማጥቃት ሲባል ብቻ አዋጅ ሆኖ እንዲፀድቅ የተደረገውን ዋስትና የሚከለክል ሕግ ካረቀቁት አንዱ እንደሆኑ ይገልፃሉ። የአስመላሽ ባለቤት በጠ/ሚ/ሩ ቢሮ ተመድባ በፀሓፊነት የቆየችና በተለይ «ሚስጥራዊ» የሚባሉ ዶክመንቶችንና የአቶ መለስ ፅሁፎችን (በብእር ስም ይወጡ የነበሩትን ጭምር) በመተየብ በታማኝነት ስታገለግል እንደቆየች አመልክተዋል።</span></p>
<p><span style="font-size: large;">ይህ በእንዲህ እንዳለ በመከላከያ ጄኔራሎችና የበታች ከፍተኛ መኮንኖች ግምገማ ላይ መሆናቸው ታውቋል። ከጥቂት ወራት በፊት ለመጠቆም እንደተሞከረው የሚባረሩ ጄኔራሎች እንዳሉ መገለፁ ይታወሳል። በዚህ መሰረት ከአዜብ ጋር የከረረ ፀብ ውስጥ የገቡት ጄ/ል ታደሰ ወረደን ጨምሮ ሶስት የሕወሐትና ሁለት የብአዴን ጄ/ሎች በሳሞራ ውሳኔ መባረራቸውን ምንጮች ገልፀዋል። በቅርቡ የተጀመረውና « የመለስን ራዕይ እናስፈፅማለን» በሚል መሪ አጀንዳ የቀጠለው ግምገማ ተጨማሪ የመከላከያ የጦር አዛዦችንና የበታች መኮንኖችን ለማባረር ቅድመ ዝግጅት አድርጎ ማጠናቀቁ ታውቋል። በሳሞራ የተወሰነው ሌላው ጉዳይ ለመከላከያ ከሩሲያ የመጡ የመሳሪያ ባለሙያዎች በተለያዩ ቦታዎች እንዲመደቡ መደረጉ ሲታወቅ ይህም የሆነው « አገሪቱ ውስጥ ችግር ከተፈጠረ ልንቋቋም አንችልም » በማለት ሳሞራ ድምዳሜ ላይ በመድረሳቸውና ከአየር ሃይል አንስቶ ያለው ወታደራዊ ክፍል እምነት ሊጣልበት ባለመቻሉ እንደሆነ ምንጮቹ አስረድተዋል። የጦር ሃይሎች ጠ/አዛዥነቱ ስልጣን የጠ/ሚ/ሩ እንደሆነ ሕገ መንግስቱ ቢደነግግም ነገር ግን ለአቶ ሃ/ማርያም ይህ ስልጣን እንዳልተሰጣቸው፣ ጄ/ሎች ሲባረሩ ከእርሳቸው እውቅና ውጭ እንደሆነ፣ ውሳኔው በሳሞራ እንደሚከናወን ምንጮቹ አስረድተዋል።</span></p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/799"     class="crp_title">የሰላማዊ ትግል በብዙሃን መጋናኛ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3087"     class="crp_title">የታሰሩት ባለስልጣናት እና ነጋዴዎች</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1124"     class="crp_title">የ255ቱን የኢሕአዴግ ሥራ አስፈጻሚዎች</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/contact-us"     class="crp_title">Contact Us</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1845"     class="crp_title">ልጆችን ማሳደግ በምዕራብ ሀገር &#8211;</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=82622</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>“በኢንቨስትመንት ስም የሚፈጸም የመሬት ነጠቃ፤ በኢትዮጵያ” ጥናት ትርጉም (117 ገጾች – ጥብቅ ምስጢር)</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3192</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3192#comments</comments>
		<pubDate>Wed, 15 May 2013 03:17:21 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3192</guid>
		<description><![CDATA[<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3187">“በኢንቨስትመንት ስም የሚፈጸም&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/440">How Soccer Explains Ethiopia</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1505">Ethiopia: Muslim Protesters Face Unfair Trial</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/107">Nigeria won the Africa Cup of Nations for the third time</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/230">ወንዶችን እንዴት ማማለል ይቻላል?</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/cover-6.jpg"><img src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/cover-6.jpg" alt="cover 6" width="500" height="420" class="alignnone size-full wp-image-3188" /></a><br />
<iframe src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/plugins/google-document-embedder/view.php?url=http%3A%2F%2Fwww.zehabesha.com%2Famharic%2Fwp-content%2Fuploads%2F2013%2F05%2FFinal-Amharic-Understanding-Land-Investment-Deals-in-Africa-Ethiopia.pdf&hl=&gpid=1&embedded=true" class="gde-frame" style="width:100%; height:300px; border: none;" scrolling="no"></iframe>
<p class="gde-text"><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/Final-Amharic-Understanding-Land-Investment-Deals-in-Africa-Ethiopia.pdf" class="gde-link">Download (PDF, 1.93MB)</a></p></p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3187"     class="crp_title">“በኢንቨስትመንት ስም የሚፈጸም&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/440"     class="crp_title">How Soccer Explains Ethiopia</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1505"     class="crp_title">Ethiopia: Muslim Protesters Face Unfair Trial</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/107"     class="crp_title">Nigeria won the Africa Cup of Nations for the third time</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/230"     class="crp_title">ወንዶችን እንዴት ማማለል ይቻላል?</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=82617</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>“በኢንቨስትመንት ስም የሚፈጸም የመሬት ነጠቃ፤ በኢትዮጵያ” ጥናት ትርጉም ይፋ ሆነ (ሊያነቡት የሚገባ)</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3187</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3187#comments</comments>
		<pubDate>Wed, 15 May 2013 03:09:31 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3187</guid>
		<description><![CDATA[ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ግንቦት 5፣ 2005ዓም በኢንቨስትመንት ስም የአገር ሃብትና ትውልድን እየበላ ስላለው የመሬት ነጠቃ አስመልክቶ የኦክላንድ ተቋምና ድርጅታችን ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ በጋራ ያዘጋጁት ጥናታዊ ዘገባ ይፋ ሆነ። የጋራ ንቅናቄያችን ዋና ዳይሬክተር ጥናቱ በትክክለኛ ጭብጥ ላይ ተመስርቶ እንዲዘጋጅ ለህይወታቸው ሳይሳሱ መረጃ በመስጠት ለተባበሩ ዜጎች “ታላቅ ክብር ይሁንላችሁ። አሁን አትታወቁም። ግን ከቶውንም አትረሱም። [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3192">“በኢንቨስትመንት ስም የሚፈጸም&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3053">የኖርዌይ ፖሊስ በኢትዮጵያውያን&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2889">ኦባንግ የኢህአዴግ ደጋፊ ስደተኞችን</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3164">የኢትዮጵያ ወጣቶች ብሄራዊ ንቅናቄ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2044">በኢትዮጵያ ፓርላማ ብቸኛው ተቃዋሚ&#8230;</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/cover-6.jpg"><img src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/cover-6.jpg" alt="cover 6" width="500" height="320" class="alignnone size-full wp-image-3188" /></a><br />
ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን)<br />
ግንቦት 5፣ 2005ዓም</p>
<p>በኢንቨስትመንት ስም የአገር ሃብትና ትውልድን እየበላ ስላለው የመሬት ነጠቃ አስመልክቶ የኦክላንድ ተቋምና ድርጅታችን ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ በጋራ ያዘጋጁት ጥናታዊ ዘገባ ይፋ ሆነ። የጋራ ንቅናቄያችን ዋና ዳይሬክተር ጥናቱ በትክክለኛ ጭብጥ ላይ ተመስርቶ እንዲዘጋጅ ለህይወታቸው ሳይሳሱ መረጃ በመስጠት ለተባበሩ ዜጎች “ታላቅ ክብር ይሁንላችሁ። አሁን አትታወቁም። ግን ከቶውንም አትረሱም። ክብር ለማትታወቁት ግን ለማትረሱት የአገር ጀግኖች” በማለት ምስጋና አቅርበዋል።<br />
ኢህአዴግን በደፈናው መቃወምን ዓላማው ያላደረገው ይህ ጥናታዊ ዘገባ ዜጎችን ካደጉበት፣ ከኖሩበት፣ ከቀያቸው፣ ከህልውናቸው፣ ከርስታቸው፣ ወዘተ ያለ አንዳች ውይይት፣ ምክክርና ንግግር በማፈናቀል ለውጪ ኩባንያዎችና ለራሱ ለባለጠመንጃው አገዛዝ ሰዎችና ባለሟሎች መሬት ማከፋፈሉን በማስረጃ ያሳያል። የራሱ የኢህአዴግ አካላትም በሪፖርቱ ውስጥ በአግባቡ ድምጻቸው ተካትቷል። የሚጠቀሙባቸው አዋጆችና ህጎችም አልተዘለሉም።<br />
“የውጪ ባለሃብቶችና ኩባንያዎች ወደ አገር ውስጥ መግባታቸው ለቴክኖሎጂ ዝውውር፣ በአገሪቱ ያለውን የምግብ እጥረት ለማስወገድ ይረዳል” የሚሉ ምክንያቶች እያቀረበ ያለው ኢህአዴግ በተግባር ሲፈተሽ ተግባሩና ዓላማው ምን እንደሆነ የሚያመለክተው ጥናቱ የስርዓቱ ሰለባዎች፣ የኢህአዴግ ባለስልጣናት፣ ኢንቨስተሮች፣ ጉዳዩ የሚመለከታቸው ክፍሎች፣ የቅርብ ምስክሮች፣ የተለያዩ ከዓለምአቀፍ ተቋማት የተገኙ መረጃዎች፣ አገዛዙ ራሱ ይፋ ያደረጋቸው መረጃዎችና ለጥናቱ አስፈላጊ የተባሉ አኻዞች የተካተቱበት በመሆኑ እውነታውን ህዝብና ማናቸውም ወገኖች እውነቱን ለመረዳት ያስችላቸዋል ተብሎ በጉልህ ታምኖበታል።<br />
በምሳሌ ለማሳያነት የተጠቀሰው የሳዑዲ ስታር ኩባንያ የሚያመርተውን ሩዝ ደብረዘይት በገነባው ተቋሙ አማካይነት ሩዙን የመለየትና ለኤክስፖርት የማዘጋጀት ስራ ይሰራል። የተመረጠውና መለኪያውን የሚያሟላው ሩዝ ኤክስፖርት የሚደረግ ሲሆን፣ ደቃቃውና በሚሊሜትር ተለክቶ ለኤክስፖርት ደረጃ የማይበቃው አገር ቤት እንዲቀር ይደረጋል። ከዚህ አንጻር እንኳ ቢታይ የመሬት ኢንቨስትመንት የተባለው ዓለም ጠንቅቆ ለሚያውቀው የአገራችን የምግብ እጥረት ችግር መፍትሄ ሊሆን አይችልም። በጥናቱ ዝርዝር ጉዳዩ አለ።<br />
ኢህአዴግ በፖለቲካው ውድማ ላይ ቆሞ የሚያወራውና በተግባር የሚሆነውን እውነት ከሰለባዎቹ አንደበት በመቅዳት ሊስተባበል በማይችልበት ደረጃ ያቀረበው ጥናት፣ ዜጎች ከቀያቸው  ከመፈናቀላቸው በፊት ምክክርና የስነልቦና ዘግጅት እንዲደረግ ጊዜ እንደሚሰጥ በህግ የተደነገገ ስለመሆኑ፣ ነግር ግን እውነታው የተገላቢጦሽ መሆኑንን ጥናቱ በማስረጃ ያትታል። ዜጎች ነገ ስለሚሆነው እንኳ ሊያውቁ በማይችሉበት ደረጃ ማለዳ ካረፉበት ሲነቁ ዶዘር ማሳቸውን፣ የጓሮ አትክልታቸውን፣ የኑሯቸው መሰረት የሆነውን ደናቸውን፣ ቤታቸውን ሲጠርግ እንደሚያዩ እነዚሁ መከረኞች ለህይወታቸው ሳይሳሱ መናገራቸውን ጥናቱ ትኩረት ሰጥቶ አቅርቦታል።<br />
የመሬት ካሳ እንኳ ባግባቡ የማያገኙት ወገኖች በራሳቸው አንደበት፣ በግብር የደረሰባቸውንና ከፊት ለፊታቸው ያለውን አደጋ አስመልክቶ በዝርዝር ሚዛናዊ በማድረግ ያቀረበው ጥናት ኢህአዴግ ለማስተባበል ከፈለገ በዜናና በተራ ጩኸት ሳይሆን በመረጃ የተደገፈ፣ ሁሉንም ወገኖች ያካተተ  ሚዛናዊ ሪፖርት ካቀረበ ብቻ ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) በማስተባበያነት እንደሚቀበለው አስቀድሞ ለመግለጽ ይወዳል።<br />
በአገርና በግለሰብ ደረጃ መረጃ ለማዳረስ፣ በተመሳሳይ ኢህአዴግ የሚያሰራጨውን የሃሰት ፕሮፓጋንዳ ማጋለጥ፣ የሰብአዊ መብት ጥሰቱን ማሳየት፣ የተሳሳተውን ፖሊሲ ማስቀየር ዋናው የጥናቱ ዓላማ ነው። በጥናቱ በቀረበው ጭብጥ መሰረት የዓለም ባንክ፣ ወዳጅ አገሮች፣ አበዳሪ አገሮች ፖሊሲ አውጪዎች ወዘተ አካሄዳቸውን እንዲመረምሩ ለማስቻል ሰፊ ስራ የተሰራ መሆኑንን በዚህ አጋጣሚ እንጠቁማለን። በተለያዩ አጋጣሚዎች የተለያዩ የውጪና የአገር ውስጥ ሚዲያዎች እንደዘገቡት ሰፊ ስራ የተሰራ ቢሆንም፣ በዋናነት የጉዳዩ ባለቤት የሆነው የኢትዮጵያ ህዝብ ምን እየተሰራ እንደሆነ ሲረዳ ትግሉን ማቅለል፤ ውጤቱንም ማቅረብ ይቻላል የሚል እምነት አለን።<br />
በዚህና በሌሎችም ተዛማጅ ምክንያቶች በከፍተኛ የሃላፊነት ስሜት፣ ረዥም ጊዜ ተወስዶ የተሰራው የትርጉም ሰራ ሰውን የሚያክል ክቡር ፍጥረት ከማደሪያው እንዲወጣ ተደርጎ እንዴት ወደ ጉድጓድ እንደሚወረወር ለመጪው ትውልድ በታሪክነት፣ አሁን ላለነው በመረጃነት፣ ከሁሉም በላይ ከጩኸትና ከመረጃ አልባ ክስ የምናገኘው ጥቅም አለመኖሩን በመረዳት አቋቋምን ለማስተካከል ይረዳል፣ ታላቅ ምሳሌም ይሆናል ብለን እናምናለን።<br />
ጥናቱን በማሰራጨትና ዜጎች እጅ እንዲደርስ በማድረጉ በኩል የሁሉም ወገኖች ያልተቆጠበ ጥረት እጅግ አስፈላጊ እንደሆነ ለመግለጽ እንወዳለን። በዚህ አጋጣሚ እናወጣዋለን ብለን ካሰብንበት ጊዜ በማለፍ ተጨማሪ ሳምንታት በማዘግየታችን ታላቅ ይቅርታ እንጠይቃለን፡፡ በአገራችን ካለው የመረጃ አፈና አኳያ የጥናቱ መጠን ሰብሰብና አጠር ባለ መጠን በኢሜይል እንደሚሰራጭ ሆኖ በአዲስ መልክ ሲቀናበር ተጨማሪ ሳምንታትን መውሰዱ የግድ ሆኗል፡፡<br />
የጋራ ንቅናቄያችን ጽሁፉን የማሰራጨቱ ስራ በጨዋነት፣ ለጽሁፉ ባለቤቶች (ለእንግሊዝኛው የኦክላንድ ተቋም ለአማርኛው ደግሞ አኢጋን) አስፈላጊውን እውቅና በመስጠት እንዲሆን በዚህ አጋጣሚ አበክረን እንሳስባለን። ከመሬት ነጠቃ በላይ የከፋ ወንጀል የለም። ዜጎችን በምድራቸው ወደ ባርነት የሚያሸጋግረው የመሬት ነጠቃ የአገሪቱን ሃብትና ንብረት እየበላ ነው። ይህንን ወደር የሌለው ወንጀል ለማጋለጥ፣ ለመታገል፣ ለመቃወምም ሆነ ተዛማጅነት ያላቸው ተግባራት ለማከናወን ለሚፈልጉ ተቋማት፣ ግለሰቦችና ሚዲያዎች ይረዳ ዘንድ (Land Grab &#8211; http://landgrabsmne.wordpress.com) የሚባል ብሎግ እንዲሁም በፌስቡክ Land Grab/መሬት ነጠቃ መከፈቱን ለማሳወቅ እንወዳለን። በቅርቡ የሚሻሻለው ይህ ብሎግና የፌስቡክ ገጽ ከመሬት ወረራ ጋር በተያያዘ ሁሉም ዓይነት ማስረጃዎች የሚታተሙበት ስለሚሆን መረጃ ለሚፈልጉ ወገኖች ሁሉ መልካም አጋጣሚ ይሆናል። <iframe src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/plugins/google-document-embedder/view.php?url=http%3A%2F%2Fwww.zehabesha.com%2Famharic%2Fwp-content%2Fuploads%2F2013%2F05%2FFinal-Amharic-Understanding-Land-Investment-Deals-in-Africa-Ethiopia.pdf&hl=&gpid=1&embedded=true" class="gde-frame" style="width:100%; height:300px; border: none;" scrolling="no"></iframe>
<p class="gde-text"><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/Final-Amharic-Understanding-Land-Investment-Deals-in-Africa-Ethiopia.pdf" class="gde-link">Download (PDF, 1.93MB)</a></p><br />
 በኢሜይል ለማግኘት የሚፈልጉ በሙሉ በሚከተለው አድራሻ (media@solidaritymovement.org) ቢጠይቁን በቀጥታ የምንልክ መሆናችንን እናሳውቃለን፡፡<br />
በመጨረሻም የጋራ ንቅናቄያችን ዋና ዳይሬክተር ለተርጓሚው ከሁሉም በላይ ግን የስርዓቱ ላንቃ ስር ሆነው የህይወት ዋጋ በመክፈል መረጃ ለሰጡት ወገኖች የአክብሮት ምስጋና አቅርበዋል። አቶ ኦባንግ በመልዕክታቸው &#8220;በቦታው ላይ ሆናችሁ ለህይወታችሁ ሳትፈሩ ይህንን መረጃ የሰጣችሁ ሁሉ የአገር ጀግኖች ናችሁ፤ አሁን አትታወቁም። አሁን ልንገልጻችሁ አንችልም። ጊዜና ወቅት ጀግንነታችሁን እስኪገልጹት ግን አትረሱም። ልትረሱም አትችሉም። ብዙ ባይነገርላችሁና ባይዘመርላችሁም ታላቅ ስራ ሰርታችሁዋልና ክብር ይሁንላችሁ&#8221; ብለዋል፡፡<br />
ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ<br />
የሚዲያና ሕዝብ ግንኙነት ግብረኃይል<br />
*********************************************************************************************************<br />
ለዚህ ደብዳቤ ምላሽም ሆነ ለተጨማሪ መረጃ ዋና ዳይሬክተሩን ለሚዲያ ክፍሉ (media@solidaritymovement.org) በመጻፍ ወይም ድረገጻችንን (www.solidaritymovement.org) በመጎብኘት ለመረዳት ይችላሉ፡፡</p>
<iframe src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/plugins/google-document-embedder/view.php?url=http%3A%2F%2Fwww.zehabesha.com%2Famharic%2Fwp-content%2Fuploads%2F2013%2F05%2FFinal-Amharic-Understanding-Land-Investment-Deals-in-Africa-Ethiopia.pdf&hl=&gpid=1&embedded=true" class="gde-frame" style="width:100%; height:300px; border: none;" scrolling="no"></iframe>
<p class="gde-text"><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/Final-Amharic-Understanding-Land-Investment-Deals-in-Africa-Ethiopia.pdf" class="gde-link">Download (PDF, 1.93MB)</a></p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3192"     class="crp_title">“በኢንቨስትመንት ስም የሚፈጸም&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3053"     class="crp_title">የኖርዌይ ፖሊስ በኢትዮጵያውያን&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2889"     class="crp_title">ኦባንግ የኢህአዴግ ደጋፊ ስደተኞችን</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3164"     class="crp_title">የኢትዮጵያ ወጣቶች ብሄራዊ ንቅናቄ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2044"     class="crp_title">በኢትዮጵያ ፓርላማ ብቸኛው ተቃዋሚ&hellip;</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=82618</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
	</channel>
</rss>

<!-- Dynamic Page Served (once) in 0.383 seconds -->
<!-- Cached page served by WP-Cache -->
