<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?>
<rss version="2.0"
	xmlns:content="http://purl.org/rss/1.0/modules/content/"
	xmlns:wfw="http://wellformedweb.org/CommentAPI/"
	xmlns:dc="http://purl.org/dc/elements/1.1/"
	xmlns:atom="http://www.w3.org/2005/Atom"
	xmlns:sy="http://purl.org/rss/1.0/modules/syndication/"
	xmlns:slash="http://purl.org/rss/1.0/modules/slash/"
	>

<channel>
	<title>Ethiopian Review</title>
	<atom:link href="http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=61638" rel="self" type="application/rss+xml" />
	<link>http://www.ethiopianreview.com/amharic</link>
	<description>Amharic News</description>
	<lastBuildDate>Thu, 23 May 2013 23:49:15 +0000</lastBuildDate>
	<language>en-US</language>
	<sy:updatePeriod>hourly</sy:updatePeriod>
	<sy:updateFrequency>1</sy:updateFrequency>
	<generator>http://wordpress.org/?v=3.4.2</generator>
		<item>
		<title>አቡነ ማቲያስ (አባ ተክለማርያም አስራት) ማናቸው?</title>
		<link>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?p=83438</link>
		<comments>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?p=83438#comments</comments>
		<pubDate>Thu, 23 May 2013 23:44:47 +0000</pubDate>
		<dc:creator>EthiopianReview.com</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.ethiopianreview.com/amharic/?p=83438</guid>
		<description><![CDATA[አቡነ ማቲያስ (አባ ተክለማርያም አስራት) ማናቸው? በዐይናለም ግዛው ከአየሩሳሌም  ጽሁፉን በ ፒ.ዲ.ኤፍ. ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ። አቡነ ማቲያስ &#160;]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p style="text-align: center;">አቡነ ማቲያስ (አባ ተክለማርያም አስራት) ማናቸው?</p>
<p style="text-align: center;">በዐይናለም ግዛው</p>
<p style="text-align: center;">ከአየሩሳሌም</p>
<p style="text-align: center;"> ጽሁፉን በ ፒ.ዲ.ኤፍ. ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ። <a href="http://www.ethiopianreview.com/2011/Abune-Mathias.pdf">አቡነ ማቲያስ</a></p>
<p>&nbsp;</p>
]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=83438</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>ሰማያዊ ፓርቲ በግንቦት 17፥2005 ዓ.ም የጠራውን ሰላማዊ ሰልፍ በመደገፍ  የተሰጠ አቋም መግለጫ</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3543</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3543#comments</comments>
		<pubDate>Thu, 23 May 2013 19:24:34 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3543</guid>
		<description><![CDATA[ከዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ ቀን፣ 23/05/13 ሰማያዊፓርቲበግንቦት 17፥2005 ዓ.ምየጠራውንሰላማዊሰልፍበመደገፍ ከዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ የተሰጠ አቋምመግለጫ! የሰማያዊ ፓርቲ ግንቦት 17 ቀን 2005 ዓ.ም በአፍሪካ ህብረት ፅ/ቤት ፊት ለፊት ጥቁር በመልበስ እና ፍፁም ሰላማዊ የሆነ ሰልፍ ለማድረግ ማቀዱ ይታወቃል በመሆኑም እንዲህ አይነት ሰላማዊ የህዝብ የመብት፣ የፍትህ እና የዲሞክራሲ ጥያቄን የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3164">የኢትዮጵያ ወጣቶች ብሄራዊ ንቅናቄ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/588">ደውሉ ይጮሐል!!</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2245">በኖርዌይ ስታቫንገር ከተማ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2621">አማራን ላሞራ-የወያኔ ሴራ!</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1138">አገር ቤት ያሉ ተቃዋሚዎች&#8230;</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<h3 style="text-align: left;" align="center">ከዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ</h3>
<p style="text-align: left;" align="center">ቀን፣ 23/05/13</p>
<h3 style="text-align: left;" align="center"><strong>ሰማያዊፓርቲበግንቦት 17፥2005 ዓ.ምየጠራውንሰላማዊሰልፍበመደገፍ ከዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ የተሰጠ አቋምመግለጫ!</strong></h3>
<p><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/united-we-stand-1.jpg"><img class=" wp-image-3544 alignleft" alt="united we stand" src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/united-we-stand-1.jpg" width="145" height="152" /></a>የሰማያዊ ፓርቲ ግንቦት 17 ቀን 2005 ዓ.ም በአፍሪካ ህብረት ፅ/ቤት ፊት ለፊት ጥቁር በመልበስ እና ፍፁም ሰላማዊ የሆነ ሰልፍ ለማድረግ ማቀዱ ይታወቃል በመሆኑም እንዲህ አይነት ሰላማዊ የህዝብ የመብት፣ የፍትህ እና የዲሞክራሲ ጥያቄን የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ የሚደግፈው መሆኑን ስንገልጽ::</p>
<p>በተለይ የሰማያዊ ፓርቲ “በአገዛዙ ምላሽ የተነፈጋቸው የተለያዩ አንገብጋቢና መሰረታዊ የሆኑ የኢትዮጵያ ህዝብ የመብት፣ የፍትህ እና የዲሞክራሲ ጥያቄዎችን የዓለም ዓቀፍ ማሕበረሰብ ትኩረት እንዲሰጣቸው በሚል ሃሳብ በአዲስ አበባ የሚከበረውን የአፍሪካ ሕብረት 50ኛ ዓመት በዓልን አጋጣሚ በመጠቀም ድምፃቸውን ለአለም አቀፍ ድርጅቶች፣ ለሃገር መሪዎች እና ለታላላቅ ሚዲያዎች ለማሰማት በማቀዳቸው ከጎናቸው ሆነን ድጋፋችንን እንገልፃለን::</p>
<p>እንደሚታወቀው የወያኔ አገዛዝ ባፀደቀው ህገመንግስቱ ላይ የመሰብሰብ፥ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብት የተደነገገ ሲሆን፥ ከ1997 ምርጫ በኋላ በግልፅ በከፍተኛ ደረጃ በውርደት የተሸነፈው የወያኔ አገዛዝ በአቶ መለስ ዜናዊ ትእዛዝ ብቻ ለራሳቸው በሚያመች ሁኔታ ያረቀቁት ህገመንግስቱ ከተሻረ በኋላ የዜጎች የመሰብሰብ፥ ሰላማዊ ሰልፍ የማረግ እንዲሁም ተዛማች መብቶች ከተገፈፈ እነሆ ስምንት አመታት ተቆጥሯል::</p>
<p>በመሆኑም ይህንን አንገብጋቢና መሰረታዊ የሆነ የመብት፣ የፍትህ እና የዲሞክራሲ ጥያቄ ሁሉም ነጻነት የተጠማ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ሊደግፈው ይገባል ብለን እናምናለን፣ ሰለሆነም ሙሉ አጋርነታችንን ለማሳየት የየዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዎይ የሥራ አስፈጻሚዎች፣ አባላት እንዲሁም ደጋፊዎች ቀኑን የጥቁር ልብስ በመልበስ ለሰማያዊ ፓርቲ ጥያቄ ድጋፍችንን እናሳያለን፣ በማያያዝም በኖርዌይ ለሚኖሩ መላ ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮጵያ ወዳጆች ሁሉ ቀኑን የጥቁር ልብስ በመልበስ ለሰማያዊ ፓርቲ ጥያቄ ድጋፋችሁን እንድታሳዩ ድርጅታችን ጥሪውን ያቀርባል::</p>
<p>&nbsp;</p>
<p>ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ</p>
<p>&nbsp;</p>
<p>የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ</p>
<p>ኖርዌይ፣ ኦስሎ፣ ግንቦት 23፣ 2013</p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3164"     class="crp_title">የኢትዮጵያ ወጣቶች ብሄራዊ ንቅናቄ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/588"     class="crp_title">ደውሉ ይጮሐል!!</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2245"     class="crp_title">በኖርዌይ ስታቫንገር ከተማ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2621"     class="crp_title">አማራን ላሞራ-የወያኔ ሴራ!</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1138"     class="crp_title">አገር ቤት ያሉ ተቃዋሚዎች&hellip;</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=83437</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>ግንቦት 7, 97 የታየውን የለውጥ መነሳሳት ለመድገም ጠንካራ ሰላማዊ ትግል የግድ ይላል</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3538</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3538#comments</comments>
		<pubDate>Thu, 23 May 2013 18:11:24 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3538</guid>
		<description><![CDATA[ፍኖተ ነፃነት ግንቦት በሀገራችን ታሪክ ወሳኝ ፖለቲካዊ ሁነቶች የተከሰቱበት ነው፡፡ ከሌሎቹ ፖለቲካዊ  ሁነቶች መካከል፣ ኢትዮጵያን ከአምባገነኖች መዳፍ ነፃ ለማውጣት የተስፋ ጭላንጭል የታየበት የግንቦት 7, 97 ምርጫ ጎላ ብሎ የሚጠቀስ ነው፡፡ በወቅቱ ገዢው ፓርቲ በአንፃራዊነት ከፍቶት በነበረው የውድድር ሜዳ የተጠቀሙት ተቃዋሚ ፓርቲዎች ዳር እስከዳር ህዝቡን ለማስተባበር የቻሉበት ነበር፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብም ለውጥ እንደሚፈልግና የሰለጠነ ፖለቲካ ለውጥ ማምጣት [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3164">የኢትዮጵያ ወጣቶች ብሄራዊ ንቅናቄ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3229">በምርጫ 97 የትዝታ ማህደር ውስጥ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1775">ወደ ቅሊንጦ እስርቤት ያመሩት&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2978">ሰላማዊ ትግላችንን ከፍ አድርገን&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3518">ሕገ ወጥነት ከዓላማችን አይገታንም!!!</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<h3></h3>
<p><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/2005-kinijit-demonstration-picture.jpg"><img class="size-full wp-image-3539 aligncenter" alt="2005-kinijit-demonstration-picture" src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/2005-kinijit-demonstration-picture.jpg" width="500" height="375" /></a></p>
<h3><strong>ፍኖተ ነፃነት</strong></h3>
<p>ግንቦት በሀገራችን ታሪክ ወሳኝ ፖለቲካዊ ሁነቶች የተከሰቱበት ነው፡፡ ከሌሎቹ ፖለቲካዊ  ሁነቶች መካከል፣ ኢትዮጵያን ከአምባገነኖች መዳፍ ነፃ ለማውጣት የተስፋ ጭላንጭል የታየበት የግንቦት 7, 97 ምርጫ ጎላ ብሎ የሚጠቀስ ነው፡፡ በወቅቱ ገዢው ፓርቲ በአንፃራዊነት ከፍቶት በነበረው የውድድር ሜዳ የተጠቀሙት ተቃዋሚ ፓርቲዎች ዳር እስከዳር ህዝቡን ለማስተባበር የቻሉበት ነበር፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብም ለውጥ እንደሚፈልግና የሰለጠነ ፖለቲካ ለውጥ ማምጣት እንደሚችል ለኢህአዴግም ሆነ ለመላው የአለም አቀፍ ህብረተሰብ ያረጋገጠበት ነው፡፡</p>
<p>ግንቦት 7 ተደርጎ የነበረው ታሪካዊ ምርጫ በኢህአዴግ አምባገነናዊ አፈናና በተቃዋሚ ፓርቲዎቹ ፖለቲካዊ ብስለት ማጣት ምክንያት ለውጤት አለመብቃቱ የሚያስቆጭ ነው፡፡ ሆኖም ከስምንት አመታት በኋላም የህዝቡ የለውጥ ፍላጎት የመጨመር እንጂ የመቀነስ ሁኔታ አይታይበትም፡፡</p>
<p>ኢህአዴግ በግንቦት 97ቱ ምርጫ ያጋጠመውን ኪሳራ ካሰላ በኋላ በሀገር አቀፍም ሆነ በወረዳና በከተማ ደረጃ ካሄዳቸውን ምርጫዎች ሙሉ ለሙሉ ለውድድር የማይመቹ እንዲሆኑ በማድረግ በህዝቡ የለውጥ ፍላጎት ላይ ቀዝቃዛ ውሀ ቸልሷል፡፡</p>
<p>በዘንድሮው የአካባቢና የከተማ ምክር ቤት ምርጫም ኢህአዴግ በከፍተኛ ውጤት ማሸነፉን ገዢው ፓርቲ እንዳሻው የሚዘውረው ብሔራዊው ምርጫ ቦርድባሳለፍነው ሳምንት ለህዝብ ይፋ አድርጓል፡፡ ኢህአዴግ ያለተፎካካሪ ብቻውን የሮጠበትን የምርጫ ሂደትና ያገኘው ውጤት ከግንቦት 7, 97 ምርጫ ጋር ሲተያይ የሀገራችን የዴሞክራሲ ጉዞ ምን ያክል ወደ ኋላ እንደተመለሰ ያመላክተናል፡፡</p>
<p>የሀገራችን ዴሞክራሲያዊ ጉዞ የተሳካ እርምጃ እንዲሄድ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ማለትም ዜጎች፣መንግስት፣ገዢው ፓርቲ፣ምርጫ ቦርድ፣ ተቃዋሚ ፓርቲዎች፣የሲቪክ ተቋማትና የሌሎች የጋራ ተሳትፎ ወሳኝ ነው፡፡ መንግስት እና ገዢው ፓርቲ ፀረ ዴሞክራሲያዊ እርምጃዎችን ሲያደርጉ፣ ብሔራዊው ምርጫ ቦርድም የድርጊቱ ተባባሪ ሲሆን ሌሎቹ ባለድርሻ አካላት በዝምታ መመልከት የለባቸውም፡፡ በሀገራችን በገሀድ እየታየ ያለው ሀቅ ግን ተቃዋሚ ፓርቲዎችን ጨምሮ ሁሉም ባለድርሻ አካላት መንግስትና ገዢው ፓርቲ የሚያደርጉትን ፀረዴሞክራሲያዊ ተግባራት ከማውገዝ ያለፈ ተግባራዊ ስራ፣  ሲሰሩ አይታዩም፡፡ ይልቁኑም ገዢው ፓርቲ ያሻውን እንዲያደርግ የተውት እስኪመስል ድረስ ከመግለጫ ያለፈ ተግባራዊ ሰላማዊ ትግል ከማድረግ ተቆጥበዋል፡፡ ይህ ሁኔታ በምንም አይነት መቀጠል የለበትም፤ በመሆኑም የኢህአዴግን በተለይም የገዢውን ቡድን አምባገነናዊ አፈና ከማማረር ባለፈ ግንቦት 7, 97 የታየውን የለውጥ መነሳሳት ለመድገም ጠንካራ ሰላማዊ ትግል ይኖርበታል፡፡ግንቦት 7, 97ቱን የለውጥ እንቅስቃሴ ለመድገም ምቹ ሁኔታዎች እንዳሉ ለመረዳት የሀገራችንን ወቅታዊ ነባራዊ ሁኔታ መመዘን ያስችለናል፡፡</p>
<p>ሀገራችን የገባችበት የማህበራዊ፣ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ምስቅልቅል ከስምንት አመት በፊት ከነበረው እጅግ የባሰ ነው፡፡ ህዝባችን የእምነት፣የመደራጀት፣የመናገር፣በፍትሀዊነት የመዳኘት መብቶቹን ከ1997ዓ.ም በባሰ መልኩ በገዢው ቡድን ተነጥቋል፡፡ የሲቪክ ተቋማትና መንግስት ባወጣው አሳሪ ህግ ለዴሞክራሲያዊ ስርአት ግንባታ አስተዋፅኦ እንዳይኖራቸው ተደርገዋል፡፡ ነፃውን ፕሬስ በአፋኝ የፕሬስ ህግ በማዳከም እንዲሁም ጋዜጠኞች በፀረሽብርተኝነት ህግ ሰበብ የሚጠበቅባቸውን ያህል እንዳይሰሩ ተደርገዋል፣ በርካታ ጋዜጠኞች በተቀነባበረ የሽብር ክስ ታስረዋል፣ ጋዜጦች አታሚ በማጣት ከገበያ እንዲወጡ ተደርገዋል፡፡የፖለቲካ ፓርቲዎች ከደጋፊዎቻቸውና ከህዝብ ጋር እንዳይወያዩ አዳራሽ ከመከልከል ጀምሮ አመራሮቻቸውን በተፈበረከ ክስ ታስለውባቸዋል፡፡ እነዚህ ሁሉ ዘርፈ ብዙ አፈናዎች በ1997 ዓ.ም ከነበረው አፈና ጋር ሲተያይ የአሁኑ እጅግ የከፋ ነው፡፡ ይህ ዘርፈ ብዙ አፈና በህዝቡ ውስጥ የፈጠረውን ብሶት ወደ ሰላማዊ ህዝባዊ ዕምቢተኝነት መለወጥ አማራጭ የሌለው መፍትሄ ነው፡፡</p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3164"     class="crp_title">የኢትዮጵያ ወጣቶች ብሄራዊ ንቅናቄ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3229"     class="crp_title">በምርጫ 97 የትዝታ ማህደር ውስጥ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1775"     class="crp_title">ወደ ቅሊንጦ እስርቤት ያመሩት&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2978"     class="crp_title">ሰላማዊ ትግላችንን ከፍ አድርገን&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3518"     class="crp_title">ሕገ ወጥነት ከዓላማችን አይገታንም!!!</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=83436</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>ብሔራዊ ስሜትን ያልተላበሰ ተቃውሞ</title>
		<link>http://www.ethiopiazare.com/articles-55/opinion/2938-abay-dam-by-semeneh-tamerat</link>
		<comments>http://www.ethiopiazare.com/articles-55/opinion/2938-abay-dam-by-semeneh-tamerat#comments</comments>
		<pubDate>Thu, 23 May 2013 17:23:23 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ኢትዮጵያ ዛሬ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.ethiopiazare.com/articles-55/opinion/2938-abay-dam-by-semeneh-tamerat</guid>
		<description><![CDATA[ስሜነህ ታምራት (ከስዊድን)
ከጥቂት ሣምንታት በፊት ለዐባይ ግድብ ማስፈጸሚያ የሚውል የገንዘብ ማስገኛ ስብሰባን ለማደናቀፍ በኖርዌይ ሁለት ተቃውሞዎች ተ]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<div class="feed-description"><p><span style="color: #0000ff;"><em><span style="font-size: 12px; line-height: 1.5;"><img style="border: 1px solid #992424; float: right;" src="http://www.ethiopiazare.com//images/doc/images/articles/2013/130523-abay-dam.jpg" alt="ዐባይ ግድብ Abay dam" width="200" />ስሜነህ ታምራት (ከስዊድን)</span></em></span></p>
<p><span style="font-size: 12px; line-height: 1.5;">ከጥቂት ሣምንታት በፊት ለዐባይ ግድብ ማስፈጸሚያ የሚውል የገንዘብ ማስገኛ ስብሰባን ለማደናቀፍ በኖርዌይ ሁለት ተቃውሞዎች ተደርገዋል። ለዚህ ጽሑፍ መነሻ የሆነኝ ይህ ሚዛን የጎደለው ተቃውሞ ብቻ ሳይሆን፤ ይልቁንም ተቃዋሚዎቹ ከስዊድን ራዲዮ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ "እኛ የኖርዌይ ጀግኖች ነን!" ሲሉ መደመጣቸው ነው።</span></p>
<p class="feed-readmore"><a  href ="/articles-55/opinion/2938-abay-dam-by-semeneh-tamerat">ሙሉውን አስነብበኝ ...</a></p></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=83433</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>Zehabesha Amharic 2013-05-23 11:31:30</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3526</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3526#comments</comments>
		<pubDate>Thu, 23 May 2013 15:31:30 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3526</guid>
		<description><![CDATA[ፍኖተ ነፃነት በኢትዮጵያና በአዲስ አበባ ወጣቶች ስም በተመሰረቱ ማህበራቶችና ፎረሞች ውስጥ ተደራጅተው ከነበሩ ወጣቶች መካከል የተወሰኑት የሚገኙባቸው ማህበራት ‹‹ነጻነት››የማይጨበጥ ሲሆንባቸው ‹‹የባለ ራዕይ ወጣቶች ማህበርን››መሰረቱ፡፡ከመስራቾቹ አንዱም ወጣት ብርሃኑ ተክለያሬድ ነው፡፡ብርሃኑ ማህበሩን በተቀዳሚ ምክትል ፕሬዘዳንትነትና በህዝብ ግኑኝነት በማገልገል ላይ የሚገኝ ከመሆኑም በላይ በተለያዮ የህትመት ውጤቶች አማካኝነት ሀሳብን የመግለጽ መብቱን ይጠቀማል፡፡ ማህበሩ በየጊዜው የሚያነሳቸው የመብት ጥያቄዎችና አገራዊ አጀንዳዎች [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1040">መንግስት ለግራዚያኒ ሀውልት&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/16">ሰበር ዜና -የባለራዕይ ወጣቶች&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1690">አርቲስት ብርሃኑ ተዘራ በኢትዮጵያ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2790">የሠራተኛ ማህበሩ ሊቀመንበርና&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3476">የኢሕአዴግ የአ.አ ወጣቶች ማህበር 15&#8230;</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<h3>ፍኖተ ነፃነት</h3>
<p><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/Birhanu-Tekele-Yared.jpg"><img class="alignright size-full wp-image-3528" alt="Birhanu-Tekele-Yared" src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/Birhanu-Tekele-Yared.jpg" width="115" height="135" /></a>በኢትዮጵያና በአዲስ አበባ ወጣቶች ስም በተመሰረቱ ማህበራቶችና ፎረሞች ውስጥ ተደራጅተው ከነበሩ ወጣቶች መካከል የተወሰኑት የሚገኙባቸው ማህበራት ‹‹ነጻነት››የማይጨበጥ ሲሆንባቸው ‹‹የባለ ራዕይ ወጣቶች ማህበርን››መሰረቱ፡፡ከመስራቾቹ አንዱም ወጣት ብርሃኑ ተክለያሬድ ነው፡፡ብርሃኑ ማህበሩን በተቀዳሚ ምክትል ፕሬዘዳንትነትና በህዝብ ግኑኝነት በማገልገል ላይ የሚገኝ ከመሆኑም በላይ በተለያዮ የህትመት ውጤቶች አማካኝነት ሀሳብን የመግለጽ መብቱን ይጠቀማል፡፡</p>
<p>ማህበሩ በየጊዜው የሚያነሳቸው የመብት ጥያቄዎችና አገራዊ አጀንዳዎች ያላስደሰተው አካል የእነ ብርሃኑን የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ በአይነ ቁራኛ ሲከታተል ቆይቷል፡፡ወጣቱ የመብት ታጋይ ዛሬ ማለዳ ከሚኖርበት ወረዳ 11 በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሏል፡፡ ከሰዓት በኋላ ለደቂቃዎች በቤተሰቦቹ እንዲጎበኝ የተደረገው ብርሃኑ ‹‹ያሰሩኝ በቅርቡ ሰላማዊ ሰልፍ ለመጥራት አስባችኋል ብለውኛል ፡፡ ነገር ግን እኛ (ባለ ራዕይ ማህበር)ሰላማዊ ሰልፍ አልጠራንም ሰልፉን የጠሩት ሰማያዊ ፓርቲዎች ናቸው ስላቸው ይህንን ወረቀት ታዲያ ለምን በተንክ ብለው ከዚህ በፊት ተመልክቼው የማላውቀውን ወረቀት አሳዮኝ እኛ ሰልፍ ብንጠራ በህቡዕ ሳይሆን በአደባባይ እንደምናደርገው ነግሬያቸዋለሁ፡፡››በማለት የእስሩን ምክንያት ተናግሯል፡፡ የመኖሪያ ቤቱ መፈተሹን የጠቆሙት የፍኖተ ነጻነት ምንጮች ፖሊሶች ግንቦት 7/2005 ተበትኗል ያሉትን ወረቀት ‹‹ የኤርትራ ጉዳይ ›› በተሰኘ የዘውዴ ረታ መጽኀፍ ውስጥ አገኘን ማለታቸውንና ብርሃኑም ተገኘ የተባለው ወረቀት ቤት ፈታሾቹ ሆን ብለው ያስቀመጡት ካልሆነ በቀር እርሱ እንዳላስቀመጠው በመግለጽ ፖሊሶች ‹‹የእኔ ነው ብለህ ፈርም ሲሉት›› እምቢ ማለቱን በኋላም አሁን ፈርምና ፍርድ ቤት በምትቀርብበት ወቅት የአንተ አለመሆኑን ትናገራለህ በሚል ማግባቢያ ቤተሰቦቹን ማስጨነቅ ባለመፈለጉ መፈረሙን ምንጮቻችን ፡፡ብርሃኑ በአሁኑ ሰዓት ጉለሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ጣብያ እንደሚገኝ ታውቋል፡፡</p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1040"     class="crp_title">መንግስት ለግራዚያኒ ሀውልት&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/16"     class="crp_title">ሰበር ዜና -የባለራዕይ ወጣቶች&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1690"     class="crp_title">አርቲስት ብርሃኑ ተዘራ በኢትዮጵያ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2790"     class="crp_title">የሠራተኛ ማህበሩ ሊቀመንበርና&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3476"     class="crp_title">የኢሕአዴግ የአ.አ ወጣቶች ማህበር 15&hellip;</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=83427</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>ፀረሙስና ኮሚሽን የባለስልጣናትን የሀብት ዝርዝር ላለማሳወቅ እያንገራገረ ነው</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3521</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3521#comments</comments>
		<pubDate>Thu, 23 May 2013 15:28:03 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3521</guid>
		<description><![CDATA[ፍኖተ ነፃነት የፌደራል ስነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን የባለስልጣኖችን የሀብት በዝርዝር ይፋ ለማድረግ ማመንታቱ በፓርላማ መነጋገሪያ ሆነ፡፡ የፌደራል ስነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አሊ ሱሌማን ባለፈው ሳምንት ግንቦት 6 ቀን 2005 ዓ.ም ለፓርላማ ባቀረቡት የ2005 በጀት የአስር ወር የዕቅድ አፈፃፀም ባቀረቡበት ወቅት የመንግስት ባለስልጣናትን ሀብት በዝርዝር ይፋ ለማድረግ ማመንታታቸው አነጋጋሪ ሆኗል፡፡ ኮሚሽነሩ ባለፈው አመትም [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3198">የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በተጠርጣሪዎቹ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2280">የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1034">በአዲስ አበባ አምስቱም መውጫዎች&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/705">የጁኔይዲ ሳዶን ወደ ኬኒያ መሰደድ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/517">ሰበር ዜና፡ ጳጳሳት የፓትርያርክ&#8230;</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<h3>ፍኖተ ነፃነት</h3>
<p>የፌደራል ስነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን የባለስልጣኖችን የሀብት በዝርዝር ይፋ ለማድረግ ማመንታቱ በፓርላማ መነጋገሪያ ሆነ፡፡</p>
<p><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/321589_109993089111063_1484315227_a.jpg"><img class="alignright size-full wp-image-3523" alt="321589_109993089111063_1484315227_a" src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/321589_109993089111063_1484315227_a.jpg" width="160" height="160" /></a>የፌደራል ስነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አሊ ሱሌማን ባለፈው ሳምንት ግንቦት 6 ቀን 2005 ዓ.ም ለፓርላማ ባቀረቡት የ2005 በጀት የአስር ወር የዕቅድ አፈፃፀም ባቀረቡበት ወቅት የመንግስት ባለስልጣናትን ሀብት በዝርዝር ይፋ ለማድረግ ማመንታታቸው አነጋጋሪ ሆኗል፡፡ ኮሚሽነሩ ባለፈው አመትም ተመሳሳይ ሪፖርት ሲያቀርቡ “በቅርቡ የመንግስት ባለስልጣናትን ሀብት በዝርዝር ይፋ እናደርጋለን” ቢሉም በያዝነው አመትም ይፋ አለመደረጉ ጥያቄ አስነስቷል፡፡ ኮሚሽነሩ ሲመልሱም በአስደንጋጭ ሁኔታ “የሚገለፅና የማይገለፅ አለው” ብለዋል፡፡<br />
ብቸኛው የተቃዋሚ ወኪል የሆኑ አቶ ግርማ ሰይፉ “የተሽዋሚዎች ሀብት የሚገለጽና የማይገለፀው ምንድነው?” የሚል ጥያቄ ቢያቀርቡም በቂ ምሳሽ እንዳላገኙ ለፍኖተ ነፃነት ተናግረዋል፡፡ ጨምረውም “ፀረ ሙስና ኮሚሽን አሁንም የመንግስት ባለስልጣናትን ሀብትና መረጃ ይፋ ለማድረግ ተጨማሪ ጊዜ መውሰድ የለበትም” ካሉ በኋላ፣ ባለስልጣናቱን በሚመለከት የሚገለፅና የማይገለፅ መረጃ ሊኖር እንደማይገባ አሳስበዋል፡፡</p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3198"     class="crp_title">የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በተጠርጣሪዎቹ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2280"     class="crp_title">የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1034"     class="crp_title">በአዲስ አበባ አምስቱም መውጫዎች&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/705"     class="crp_title">የጁኔይዲ ሳዶን ወደ ኬኒያ መሰደድ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/517"     class="crp_title">ሰበር ዜና፡ ጳጳሳት የፓትርያርክ&hellip;</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=83428</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>የሰማያዊ ፓርቲ ጥሪ ከወዲሁ ያስመዘገባቸው ድሎች</title>
		<link>http://www.ethiopiazare.com/articles-55/opinion/2934-semayawi-party-teri-by-girma-kassa</link>
		<comments>http://www.ethiopiazare.com/articles-55/opinion/2934-semayawi-party-teri-by-girma-kassa#comments</comments>
		<pubDate>Thu, 23 May 2013 12:53:57 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ኢትዮጵያ ዛሬ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.ethiopiazare.com/articles-55/opinion/2934-semayawi-party-teri-by-girma-kassa</guid>
		<description><![CDATA[ግርማ ካሳ
አገር ውስጥ በሰላም የሚንቀሳቀሰው የሰማያዊ ፓርቲ፣ ግንቦት 17 ቀን 2005 ዓ.ም.፣ በአፍሪካ ሕብረት ጽ/ቤት ፊት ለፊት ሰላማዊ ሰልፍ አውጇል። ከግን]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<div class="feed-description"><p><span style="color: #0000ff;"><em><span style="font-size: 12px; line-height: 1.5;">ግርማ ካሳ</span></em></span></p>
<p><span style="font-size: 12px; line-height: 1.5;">አገር ውስጥ በሰላም የሚንቀሳቀሰው የሰማያዊ ፓርቲ፣ ግንቦት 17 ቀን 2005 ዓ.ም.፣ በአፍሪካ ሕብረት ጽ/ቤት ፊት ለፊት ሰላማዊ ሰልፍ አውጇል። ከግንቦት 15 እስከ 17 ባሉት ቀናት ደግሞ፣ ኢትዮጵያውያን ጥቁር አልባሳት በመልበስ፣ አገዛዙ በሚያራምዳቸውን ጎጂ ተግባራት ላይ፣ ያላቸውን ተቃውሞ እንዲገልጹ ጥሪ አስተላልፏል።</span></p>
<p class="feed-readmore"><a  href ="/articles-55/opinion/2934-semayawi-party-teri-by-girma-kassa">ሙሉውን አስነብበኝ ...</a></p></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=83423</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>&quot;እኛ ስንስተካከል ዓለምና የፍርድ ሚዛንዋ ወደ እኛ ያዘማሉ&quot; አቶ ኦባንግ ሜቶ</title>
		<link>http://www.ethiopiazare.com/interview/interview/2933-obang-meto-with-tila-magazine</link>
		<comments>http://www.ethiopiazare.com/interview/interview/2933-obang-meto-with-tila-magazine#comments</comments>
		<pubDate>Thu, 23 May 2013 12:49:40 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ኢትዮጵያ ዛሬ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.ethiopiazare.com/interview/interview/2933-obang-meto-with-tila-magazine</guid>
		<description><![CDATA["የኢህአዴግ ባለስልጣናትን ዓለምአቀፍ ፍርድ ቤት የማቅረቡ ጉዳይ ከመለስ ሞት ጋር የሚሞት አይሆንም"&#160;አቶ ኦባንግ ሜቶ የአኢጋን ዋና ስራ አስፈፃሚ
በጀር...]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<div class="feed-description"><p style="text-align: center;"><strong><span style="font-size: 12px; line-height: 1.5;"><img style="border: 1px solid #992424; float: right;" src="http://www.ethiopiazare.com//images/doc/images/interview/2013/130223-obang-meto.jpg" alt="አቶ ኦባንግ ሜቶ Obang Meto" width="212" height="150" />"የኢህአዴግ ባለስልጣናትን ዓለምአቀፍ ፍርድ ቤት የማቅረቡ ጉዳይ ከመለስ ሞት ጋር የሚሞት አይሆንም"</span></strong><span style="color: #0000ff;"><em><span style="font-size: 12px; line-height: 1.5;">&nbsp;</span>አቶ ኦባንግ ሜቶ የአኢጋን ዋና ስራ አስፈፃሚ</em></span></p>
<p>በጀርመን ሀገር የሚታተመው "ጥላ" መጽሔት በሁለተኛ ዓመት ቁጥር 6 ዕትሙ ከአቶ ኦባንግ ሜቶ *የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ሥራ አስጻሚ) ጋር ቃለምልልስ አድርጓል። ሙሉውን ቃለምልልስ እንደሚከተለው ያገኙታል። <em>መልካም ንባብ!</em></p>
<p class="feed-readmore"><a  href ="/interview/interview/2933-obang-meto-with-tila-magazine">ሙሉውን አስነብበኝ ...</a></p></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=83424</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>ሕገ ወጥነት ከዓላማችን አይገታንም!!! (ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ ማብራሪያ)</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3518</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3518#comments</comments>
		<pubDate>Thu, 23 May 2013 12:46:32 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3518</guid>
		<description><![CDATA[ሕግ ምን ይላል? አዋጅ ቁጥር ፫/፲፱፻፹፫ ዓ.ም ስለ ሰላማዊ ሰልፍና ሕዝባዊ ስብሰባ ሥነ ሥርዓት የወጣ አዋጅ፤ ሰላማዊ ሰልፍ የጠራው አካል ስላለበት ግዴታ በአንቀጽ ፬ ላይ እንዲህ ይላል አንቀጽ ፬፤የማሳወቅ ግዴታ፤ ፩/ ሰላማዊ ሰልፍ ወይም ህዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባ የሚያዘጋጀው ማንኛውም ግለሰብ፣ ቡድን ወይም ድርጅት የታሰበው ሰላማዊ ሰልፍ ወይም ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባ ከሚካሄድበት ጊዜ ቢያንስ ከ፵፰ ሰዓታት [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3007">ሰማያዊ ፓርቲ በአፍሪካ ሕብረት 50ኛ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2044">በኢትዮጵያ ፓርላማ ብቸኛው ተቃዋሚ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2978">ሰላማዊ ትግላችንን ከፍ አድርገን&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/180">የኢሕአዴግ ከፍተኛ የመንግስት&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3164">የኢትዮጵያ ወጣቶች ብሄራዊ ንቅናቄ&#8230;</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p>ሕግ ምን ይላል?<br />
አዋጅ ቁጥር ፫/፲፱፻፹፫ ዓ.ም<br />
ስለ ሰላማዊ ሰልፍና ሕዝባዊ ስብሰባ ሥነ ሥርዓት የወጣ አዋጅ፤ ሰላማዊ ሰልፍ የጠራው አካል ስላለበት ግዴታ በአንቀጽ ፬ ላይ እንዲህ ይላል<br />
አንቀጽ ፬፤የማሳወቅ ግዴታ፤<br />
፩/ ሰላማዊ ሰልፍ ወይም ህዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባ የሚያዘጋጀው ማንኛውም ግለሰብ፣ ቡድን ወይም ድርጅት የታሰበው ሰላማዊ ሰልፍ ወይም ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባ ከሚካሄድበት ጊዜ ቢያንስ ከ፵፰ ሰዓታት በፊት በጽሑፍ የማሳወቅ ግዴታ አለበት፡፡<br />
፪/ የማሳወቂያው ጽሑፍ ሰላማዊ ሰልፉ ወይም ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባ በከተማ ከሆነ የሚደረገው ለከተማው አስተዳደር ጽ/ቤት፤ ከከተማ ውጭ ከሆነ ለአውራጃው አስተዳደር ጽ/ቤት ይሆናል፡፡<br />
መልስ ሰጪው አካል የከተማ ወይም የአውራጃው አስተዳደር ጽ/ቤት ያለበትን ግዴታና ኃላፊነት አንቀጽ ፮ ላይ እንዲህ ብሎ ደነግጋል፡፡<br />
አንቀጽ ፮፤ የከተማው ወይም አውራጃው አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊነት፣<br />
፩/ ከተማው ወይም የአውራጃው አስተዳደር ጽ/ቤት የሰላማዊ ሰልፍ ወይም ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባ ጥያቄ በጽሑፍ ሲቀርብለት ሰላምን ከማስፈን ጸጥታን ከማስጠበቅና የሕዝቡን ዕለታዊ ኑሮ እንዳይሰናከል ከማድረግ አንጻር አስፈላጊውን ዝግጅት ሁሉ የማድረግ ኃላፊነት አለበት፡፡<br />
፪/ ከተማው ወይም የአውራጃው አስተዳደር ጽ/ቤት በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፮ ንዑስ አንቀጽ ፩ የተመለከቱትን ሁኔታዎች በማገናዘብ ሰላማዊ ሰልፉ ወይም ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባ በሌላ ጊዜ ወይም በሌላ ሥፍራ ቢደረግ ይሻላል የሚል አስተያየት ካለው ምክንያቱን በመግለጽ ይህንኑ ጥያቄው በደረሰው በ፲፪ ሰዓት ውስጥ በጽሑፍ ለአዘጋጁ ማሳወቅ ኃላፊነት አለበት፡፡ ሆኖም የከተማው ወይም አውራጃው አስተዳደር ጽ/ቤት ሰላማዊ ሰልፉ ወይም ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባው ምን ጊዜም በየትኛውም ቦታ ሊካሄድ አይችልም ማለት አይችልም፡፡</p>
<p><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/semayawi-party1.jpg"><img class="alignleft size-medium wp-image-3519" alt="semayawi party" src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/semayawi-party1-218x300.jpg" width="218" height="300" /></a>ምን ተደረገ?<br />
ሰማያዊ ፓርቲ የጠራውን የተቃውሞ ሰልፍ ማወቅ የሚገባው በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት የሰላማዊ ሰልፍና የህዝባዊ ስብሰባ ማሰወቂያ ቢሮ እንዲያውቅ የሚያደርግበትን ደብዳቤ ግንቦት 14 ቀን 2005 ዓ.ም ከጧቱ 4፡00 ሰዓት የተጠቀሰው ቢሮ ድረስ አቅርቧል፡፡ የቢሮው ኃላፊ ደብባቤ አልቀበልም በማለታቸው ከሰዓት በኋላም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ላይ ደብዳቤውን እንደገና አቅርቦ አሁንም አልቀበልም በማለታቸው ጉዳዩ ይመለከታቸዋል የተባሉ የተለያዩ አካላት እስከ ከንቲባው ፅ/ቤት ኃላፊና የካቢኔ ጉጋዮች ምክትል ኃላፊ ድረስ በመሄድ ደብዳቤውን እንዲቀበሉ ቢጠየቁም “ደብዳቤ እንዳንቀበል ከበላይ ታዘናል” በማለት በቃል ተመሳሳይ የአንቀበልም መልስ ሰጥተዋል፡፡ ከብዙ ጥረት በኋላ ከፓርቲው በኩል ሦስት ሰዎች ከማዘጋጃ ቤቱ ደግሞ ሦስት ሰዎች የአይን ምስክርነት ባሉበት በሰላማዊ ሰልፍና የህዝባዊ ስብሰባ ማሰወቂያ ቢሮ ኃላፊ ጠረጴዛ ላይ አስቀምጠው ወጥተዋል፡፡ ከዚህም በጠጨማሪ ደብዳቤው በፖስታ ቤት በኩል በሪኮመንዴ እንዲደርስ ተልኳል፡፡<br />
ምን ይደረጋል?<br />
ሰማያዊ ፓርቲ በሕግ የተቋቋመ ህግ የሚያከብር ፓርቲ ነው፡፡ ፓርቲው የሚገዛው ለህግ እንጅ ለውንብድና ባለመሆኑ ሰልፉን በዚህ መልኩ ለማሰናከል የማይቻል መሆኑን የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ እንዲያውቁት ማሳሰብ ይፈልጋል፡፡ ሰልፉን ለማድረግ እስከ አሁኗ ሰዓት ድረስ በህግ በኩል የጎደለ አንድም ቅንጣት ነገር ባለመኖሩ ሰልፉ በታቀደው ቦታና ስዓት የሚካሔድ መሆኑን ያሳውቃል፡፡</p>
<p>ግንቦት 15 ቀን 2005 ዓ.ም<br />
አዲስ አበባ</p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3007"     class="crp_title">ሰማያዊ ፓርቲ በአፍሪካ ሕብረት 50ኛ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2044"     class="crp_title">በኢትዮጵያ ፓርላማ ብቸኛው ተቃዋሚ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2978"     class="crp_title">ሰላማዊ ትግላችንን ከፍ አድርገን&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/180"     class="crp_title">የኢሕአዴግ ከፍተኛ የመንግስት&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3164"     class="crp_title">የኢትዮጵያ ወጣቶች ብሄራዊ ንቅናቄ&hellip;</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=83420</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>የሙስናው እስር ምስጢር!</title>
		<link>http://www.ethiopiazare.com/articles-55/opinion/2932-yemusenaw-eser-mestir-by-solomon-tesema-g</link>
		<comments>http://www.ethiopiazare.com/articles-55/opinion/2932-yemusenaw-eser-mestir-by-solomon-tesema-g#comments</comments>
		<pubDate>Thu, 23 May 2013 12:22:40 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ኢትዮጵያ ዛሬ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.ethiopiazare.com/articles-55/opinion/2932-yemusenaw-eser-mestir-by-solomon-tesema-g</guid>
		<description><![CDATA[ማረ በላዎቹ ርስ-በርስ ተበላሉ!
ሰሎሞን ተሰማ ጂ.&#160;
ለብዙዎች "ሙስና" የሚለው ቃል በ1989 ዓ.ም ወዲህ የተፈጠረ ሃይለ-ቃል ይመስላቸዋል። ነገር ግን አይደለም]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<div class="feed-description"><p style="text-align: center;"><strong><span style="font-size: 12px; line-height: 1.5;"><img style="border: 1px solid #992424; float: left;" src="http://www.ethiopiazare.com//images/doc/images/articles/2013/130523-addis-guday-special-issue.jpg" alt="አዲስጉዳይ መጽሔት ቅጽ 7፣ ቁ. 164 Addis Guday " width="110" height="150" />ማረ በላዎቹ ርስ-በርስ ተበላሉ!</span></strong></p>
<p><span style="color: #0000ff;"><em><span style="font-size: 12px; line-height: 1.5;">ሰሎሞን ተሰማ ጂ.&nbsp;</span></em></span></p>
<p><span style="font-size: 12px; line-height: 1.5;">ለብዙዎች "ሙስና" የሚለው ቃል በ1989 ዓ.ም ወዲህ የተፈጠረ ሃይለ-ቃል ይመስላቸዋል። ነገር ግን አይደለም። ቃሉ ግዕዝ ነው። ትርጉሙም፣ "ጥፋት" ማለት ነው። በአማረኛም የኖረ ሕዝባዊ ግጥም/አባባል አለ፤ እንዲህ የሚል ነው።</span></p>
<p><em>"የከንሯ ለዛ፣ የጉንጯ ሙስና፤</em><br /><em>"ዐርብ ሮብ ያስክዳል፣ እንኳን ዐሙስንና።"</em> ይላል - አዝማሪም።</p>
<p class="feed-readmore"><a  href ="/articles-55/opinion/2932-yemusenaw-eser-mestir-by-solomon-tesema-g">ሙሉውን አስነብበኝ ...</a></p></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=83425</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>ፓትርያሪክ መርቆርዮስ ለምን እንደተሰደዱ ምላሽ የሚሰጥ ባለ 63 ገጽ መጽሐፍ ታትሞ ወጣ (ይዘነዋል)</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3509</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3509#comments</comments>
		<pubDate>Thu, 23 May 2013 12:16:35 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3509</guid>
		<description><![CDATA[(ዘ-ሐበሻ) ማርች 5 ቀን 2013 በአዲስ አበባ የሚገኘው ሲኖዶስ &#8220;ቤተክህነታዊ ሃረካት&#8221; ሲሉ ምእመናን የተቹትን ባለ 52 ገጽ መጽሐፍ በስደተኛው ሲኖዶስ ዙሪያ አሳትሞ መበተኑን በወቅቱ ዘ-ሐበሻ መዘገቧ አይዘነጋም። በስደት የሚገኘው ሲኖዶስም ለዚህ መጽሐፍ ምላሽ የሆነ ባለ 63 ገጽ ትንሽ መጽሐፍ አሳትሞ በትኗል። ይህ መጽሐፍ በኢሜይል፣ በድረ ገጽ እንዲሁም ታትሞ እየተሠራጨ ሲሆን አቡነ መርቆርዮስ ለምን ሊሰደዱ እንደቻሉና [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/892">የአ.አበባው ሲኖዶስ ታዛቢዎች&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2871">ፓትርያርክ አቡነ መርቆሬዎስ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2678">ግልጽ ደብዳቤ ለብፁዓን ወቅዱሳን&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/722">በስደት ላይ የሚገኘው ሲኖዶስ በአ.አ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1972">(ሰበር ዜና) የዊኒፔግ ካናዳዋ ማርያም</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/abune-merekoriwos-150x150.jpg"><img class="alignleft size-full wp-image-2682" alt="abune-merekoriwos-150x150" src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/abune-merekoriwos-150x150.jpg" width="150" height="150" /></a>(ዘ-ሐበሻ) ማርች 5 ቀን 2013 በአዲስ አበባ የሚገኘው ሲኖዶስ &#8220;ቤተክህነታዊ ሃረካት&#8221; ሲሉ ምእመናን የተቹትን ባለ 52 ገጽ መጽሐፍ በስደተኛው ሲኖዶስ ዙሪያ አሳትሞ መበተኑን በወቅቱ ዘ-ሐበሻ መዘገቧ አይዘነጋም። በስደት የሚገኘው ሲኖዶስም ለዚህ መጽሐፍ ምላሽ የሆነ ባለ 63 ገጽ ትንሽ መጽሐፍ አሳትሞ በትኗል። ይህ መጽሐፍ በኢሜይል፣ በድረ ገጽ እንዲሁም ታትሞ እየተሠራጨ ሲሆን አቡነ መርቆርዮስ ለምን ሊሰደዱ እንደቻሉና እንዴት እንደተሰደዱ? ለቀድሞው ጠ/ሚ/ር መለስ ዜናዊና ታምራት ላይኔ ጽፈዋቸው የነበሩ ደብዳቤዎች፣ እንዲሁም ሕወሓት በበርሃ በነበረበት ወቅት ለሰላም እንዲሰሩ የጻፏቸውን ደብዳቤዎች ሁሉ ይዟል።</p>
<p>በስደት የሚገኘው ሲኖዶስ ይህን ለአዲስ አበባው ሲኖዶስ ላሳተመው &#8220;ቤተክህነታዊ ሃረካት&#8221; ምላሽ የሚሆን መጽሐፍ የዘ-ሐበሻ አንባቢዎች እንዲያነቡት ልኮልናል እንደሚከተለው አስተናግደነዋል።</p>
<p><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/Response_to_false_claim_from_Ethiopia.pdf">መጽሐፉን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ (PDF)</a></p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/892"     class="crp_title">የአ.አበባው ሲኖዶስ ታዛቢዎች&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2871"     class="crp_title">ፓትርያርክ አቡነ መርቆሬዎስ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2678"     class="crp_title">ግልጽ ደብዳቤ ለብፁዓን ወቅዱሳን&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/722"     class="crp_title">በስደት ላይ የሚገኘው ሲኖዶስ በአ.አ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1972"     class="crp_title">(ሰበር ዜና) የዊኒፔግ ካናዳዋ ማርያም</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=83421</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>አቡነ ሕዝቅኤል የ6ኛው ፓትርያሪክ ምርጫ ድጋፍ ነፍገውኛል ያሏቸውን እየተበቀሉ የሚያስመስል ድርጊት እየፈጸሙ ነው ተባለ</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3506</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3506#comments</comments>
		<pubDate>Thu, 23 May 2013 12:06:01 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3506</guid>
		<description><![CDATA[በሀ/ስብከቱ የአቡነ ሕዝቅኤል አስተዳደር ሙስናና ጎጠኝነት ባስነሣው ቀውስ ተዘፍቋል የሊቀ ጳጳሱ ዘመዶች ከደብር እልቅና እስከ ዕቅብና በከፍተኛ ደመወዝ ተቀጥረዋል ሊቀ ጳጳሱ ሥራ አስኪያጁን ያገዱበት ርምጃ የሀ/ስብከቱን አድባራት ተቃውሞ ቀስቅሷል ንቡረ እድ ኤልያስ ኣብርሃ በታገዱት ሥ/አስኪያጅ ምትክ ለመመደብ ከሊቀ ጳጳሱ ጋራ እየተሸማገሉ መኾናቸው ተሰምቷል ፓትርያሪኩ እግዱ ተነሥቶ ሥ/አስኪያጁ ወደ ሓላፊነታቸው እንዲመለሱና የእግዱ አግባብነት እንዲጣራ ለጠ/ቤ/ክህነቱ ጽ/ቤት የሰጡት መመሪያ አልተፈጸመም፤ ዋ/ሥ/አስኪያጁ [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/732">(ሰበር ዜና )አቡነ ማትያስ የኢትዮጵያ</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/493">ስለ መንበረ ፕትርክናው ዕጩዎች&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/683">የ5ቱ እጩ ፓትርያርክ ማንነት በጥቂቱ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/241">ኮሚቴው የፓትርያሪክ ምርጫ ሕገ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3294">ጠ/ቤተ ክህነት የመምህር ግርማ&#8230;</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<ul>
<li><b>በሀ/ስብከቱ የአቡነ ሕዝቅኤል አስተዳደር ሙስናና ጎጠኝነት ባስነሣው ቀውስ ተዘፍቋል</b></li>
<li><b>የሊቀ ጳጳሱ ዘመዶች ከ<i>ደብር እልቅና </i>እስከ <i>ዕቅብና</i> በከፍተኛ ደመወዝ ተቀጥረዋል</b></li>
<li><b>ሊቀ ጳጳሱ ሥራ አስኪያጁን ያገዱበት ርምጃ የሀ/ስብከቱን አድባራት ተቃውሞ ቀስቅሷል</b></li>
<li><b>ንቡረ እድ ኤልያስ ኣብርሃ በታገዱት ሥ/አስኪያጅ ምትክ ለመመደብ ከሊቀ ጳጳሱ ጋራ እየተሸማገሉ መኾናቸው ተሰምቷል</b></li>
<li><b>ፓትርያሪኩ እግዱ ተነሥቶ ሥ/አስኪያጁ ወደ ሓላፊነታቸው እንዲመለሱና የእግዱ አግባብነት እንዲጣራ ለጠ/ቤ/ክህነቱ ጽ/ቤት የሰጡት መመሪያ አልተፈጸመም፤ </b><b>ዋ</b><b>/ሥ/አስኪያጁ እግዱን ለማስፈጸም ዳተኛ ሲኾኑ ሊቀ ጳጳሱ ደግሞ ላልተገባ ርምጃቸው ድጋፍ ለማግኘት የሀ/ስብከቱን አጥቢያ አብ/ክርስቲያን ሓላፊዎች ነገ ስብሰባ ጠርተዋል</b></li>
<li><b>አቡነ ሕዝቅኤል በዕጩነት በቀረቡበት የስድስተኛው ፓትርያሪክ ምርጫ <i>ድጋፍ ነፍገውኛል </i>ያሏቸውን እየተበቀሉ ነውን?</b></li>
</ul>
<p><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/02/abune-hizekel1-221x300.jpg"><img class="alignleft size-full wp-image-40" alt="abune-hizekel1-221x300" src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/02/abune-hizekel1-221x300.jpg" width="221" height="300" /></a>የጥቅምት 2005 ዓ.ም ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት በአራት አህጉረ ስብከት እንዲከፈል ሲወስን በሀ/ስብከቱ የተንሰራፋውን <b>የሙስናና የመልካም አስተዳደር ችግር በዘላቂነት እንደሚፈታው በመታመኑ</b> ነበር፡፡ ምልአተ ጉባኤው ስለ ውሳኔው ያወጣው መግለጫ ቃል የሚከተለውን ይላል፡-</p>
<p>በቅ/ሲኖዶስ የተቋቋመው ኮሚቴ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከትን ችግር ለመፍታት አጥንቶ ያቀረበውን ጥናታዊ ጽሑፍ የመረመረው የቅ/ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በጥናቱ መሠረት የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት በአራት አህጉረ ስብከት ቢከፈል ለአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ቅርበት ያለው አገልግሎት መስጠት የሚችል ከመኾኑም በላይ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አካባቢ የሚታየው የአስተዳደር ችግር በዘላቂነት እንደሚፈታው በመታመኑ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት በምሥራቅ፣ በምዕራብ፣ በሰሜን፣ በደቡብ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ጽ/ቤት እንዲደራጅ ወስኗል፡፡</p>
<p>የምልአተ ጉባኤውን ውሳኔ አስመልክቶ የቅ/ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል ከብዙኀን መገናኛ ለቀረበላቸው ጥያቄ በወቅቱ በሰጡት ምላሽ÷ <i>‹‹አቤት ባዩ በዛ፤ ጩኸት በዝቷልና ሁሉም በአካባቢው እንዲስተናገድ በሊቃውንትም በአባቶችም ተጠንቶ ቀጠሮ ተይዞበት የቆየ ነው፤››</i> ብለው ነበር፡፡</p>
<p>ቅዱስ ሲኖዶሱ ባሳለፈው ውሳኔ መሠረት አራቱን የአዲስ አበባ አህጉረ ስብከት የሚመሩ ሁለት ሊቃነ ጳጳሳት በምልአተ ጉባኤው፣ ሥራ አስኪያጆችና ጸሐፊዎች በቋሚ ሲኖዶሱና ቋሚ ሲኖዱሱን ለማጠናከር በተመረጡት ሰባት ብፁዓን አባቶች ተመድበው ነበር፡፡ ይኹንና ከኅዳር ወር መጀመሪያ አንሥቶ ተግባራዊ በኾነው <i>የአዲስ አበባ በአራት አህጉረ ስብከት መደራጀት</i> አድባራትና ገዳማት መልካም አስተዳደር አግኝተዋልን? የተንሰራፋው ሙስናና ብልሹ አሠራር ተወግዷልን?</p>
<p>ምላሹ ግልጽ ነው፤ ለውጡ የቅርጽ እንጂ የይዘትም ባለመኾኑ ተጠያቂነትና ግልጽነት የሰፈነበት መልካም አስተዳደር ላም አለኝ በሰማይ ኾኗል፤ የዘመድ አዝማድ አሠራሩና ጎጠኝነቱ አልተገታም፤ ሞያና ሞያተኛው አልተገናኘም፡፡</p>
<p>አሁንም ሹመት፣ ቅጥር፣ ዕድገትና ዝውውር እየተፈጸመ የሚገኘው በውድድርና በፍትሐዊነት ሳይኾን በ<i>ኔትወርኪንግ /በደላሎች እና አቀባባዮች/</i>ነው፤ ለደብር እልቅና በአነስተኛ ግምት እስከ ብር 80,000፣ ለጸሐፊነት እስከ ብር 30,000፣ ለስብከተ ወንጌል ክፍል ሓላፊነት ሳይቀር እንደ ደብሩ ገቢ ከብር 10,000 – 15,000 ይጠየቃል፡፡ መዝገብ በሚያውቀው ደመወዝ ከቶም የማይታሰበውን መሬት መያዝ፣ ሁለት ቤት መሥራት፣ የግልም የንግድም መኪኖችን መሸመት ብርቅ አይደለም፡፡</p>
<p>አዲስ አበባ የመንበረ ፓትርያሪኩ መቀመጫና የሁሉም አህጉረ ስብከት ማእከል በመኾኑ ያለውን ቅምጥ አቅም ያህል፣ ይቅርና<b> </b>በመልካም አስተዳደር (ቅጥር፣ ዕድገት፣ ዝውውር) በቅጽ አሟላልና በፐርሰንት አሰባሰብ እንኳ የአህጉረ ስብከቱ ሁሉ አርኣያ ሊኾን አልቻለም፡፡</p>
<p><b>ይህ አህጉረ ስብከት ቀድሞም</b>÷ ብር 64,000 እጅ መንሻ ሲቀበሉ <i>(አንዱን በደብር እልቅና ለማሾም፣ የደብሩን የሰበካ ጉባኤ ምርጫ ለማጸደቅ፣ የካህናቱንና ሠራተኞችን በጀት ለማጸደቅ)</i> <b>እጅ ከፍንጅ የተያዙት </b>የቀድሞው ምክትል ሥራ አስኪያጅ<b> </b><i>ርእሰ ደብር በሪሁ አርኣያ</i>በሙስና ወንጀል ከመጠየቅ ይልቅ ወደ ጠቅላይ ቤተ ክህነቱ <b>ትምህርትና ሥልጠና መምሪያ</b> በምክትል ሓላፊነት በማዘዋወር በጎጠኝነት ከተጠያቂነት የማራቅ ሥራ የተሠራበት ነው፡፡</p>
<p><b>ይህ አህጉረ ስብከት ቀድሞም</b>÷ በአድባራትና ገዳማት በልማት ስም ጉብኝት ሲያካሂዱ ከብር 30 – 50 ሺሕ እየተቀበሉ፣ በታወቁ የጥቅም አቀባባይ ደላሎቻቸው ቅጥር፣ ዕድገትና ዝውውር እየፈጸሙ የቆዩት፣ ከሁሉም በላይ በ2004 ዓ.ም የበጀት ዓመት በቀረበው ሪፖርት <b>ከብር ስድስት ሚልዮን በላይ ጉድለት</b> የተገኘባቸው የሀ/ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ <b>ንቡረ እድ ኤልያስ ኣብርሃ፣ </b>ለዓመታት ድኻውን እየበደሉ ፍርድ እያጓደሉ <i>ተቋማዊ ለውጥን የማምከን ሚናቸውን ሲጫወቱ ወደኖሩበት</i> ወደ ጠቅላይ ቤተ ክህነቱ <i>የመንፈሳዊ ዘርፍ ምክትል ሥራ አስኪያጅነት</i>ያለአንዳች ተጠያቂነት የተዘዋወሩበት ነው፡፡</p>
<p><b>በዚህ አህጉረ ስብከት</b>÷ ርእሰ ደብር በሪሁን በሰንዳፋ፣ ንቡረ እድ ኤልያስ በሰንዳፋና በሌሎች ከሁለት ባላነሱ የከተማ ቦታዎች በገንዘብም በዐይነትም እየዘረፉ ስለሠሯቸው የመኖሪያና የንግድ ቤቶች፣ ስለወሰዱት የቤተ ክርስቲያን መሬቶች የጠየቃቸው የለም፡፡</p>
<p><b>ዛሬም</b>÷ አዲስ አበባ ለአራት አህጉረ ስብከት ከተከፈለ በኋላ ሙስናው፣ ጎጠኝነቱና ብልሹ አሠራሩ በሰሜንና ምሥራቅ አዲስ አበባ አህጉረ ስብከት መጠነኛ መሻሻል ቢያሳይም በደቡብና ምዕራብ አዲስ አበባ አህጉረ ስብከት ግን ተባብሶ መቀጠሉ ነው የተዘገበው፡፡ በተለይም<b>በምዕራብ አዲስ አበባ ሀ/ስብከት ጽ/ቤት</b> በአስከፊ ደረጃ የተስፋፋው የጎጠኝነትና ሙስና ተግባር <i>በቀጥታ ከሊቀ ጳጳሱ ጋራ የተያያዘና በእርሳቸው ዙሪያ የሚያጠነጥን እንደኾነ </i>መገለጹ ሊቀ ጳጳሱን በሚበዛው ምስጉን አቋማቸው የሚያውቋቸውን ብዙዎች አሳዝኗል፡፡</p>
<p>በሀ/ስብከቱ ሥር የሚገኙ 33 ያህል አጥቢያ አብያተ ክርስቲያን አስተዳደሮች ግንቦት 12 ቀን 2005 ዓ.ም ለብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪኩ እንዳስገቡት የተዘገበው ባለአራት ገጽ አቤቱታ <b>እንደሚጠቁመው</b>÷ ከጠቅላላው የሀ/ስብከቱ 21 የክፍል ሓላፊዎችና ድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች መካከል 13 ያህሉ ከሊቀ ጳጳሱ ጋራ በአንድ ይኹን በሌላ መንገድ የቅርብ ዝምድና ያላቸው የአካባቢ ተወላጆች ናቸው፡፡ ፊት በአዲስ አበባ አድባራትና በትውልድ ቦታቸው ከብር 300 – 400 በማይበልጥ ደመወዝ ይሠሩ የነበሩ የሥጋ ዘመዶቻቸው በታላላቅ አድባራት <b>ከዐቃቢነት እስከ ዋና ጸሐፊነትና አስተዳዳሪነት</b> በከፍተኛ ደመወዝ ተቀጥረዋል፤ በደብር እልቅና የሚገኙ ቀራቢዎቻቸው (<i>ለምሳሌ</i>፡- በጠሮ ቅድስት ሥላሴ) ከደመወዛቸው ወጪ ከፍተኛ አበል (እስከ ብር 2600) እንዲከፈላቸው ተወስኖላቸዋል፤ በዚህም መንገድ በተዘረጋ የጎጠኝነትና ጥቅመኝነት ሰንሰለት በተለይ <i>ግራር ደብረ ዐባይ</i> በሚባለው አካባቢ የሚገኘው የቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን በየሳምንቱ ከ5 – 12,000 ብር በብፁዕነታቸው ስም ይባክናል፤ ሊቀ ጳጳሱም <b>‹‹የልማት አባት››</b> እያሉ ሸልመዋቸዋል፡፡ የጋዜጠኝነት ልምድ የሌለውን ዘመዳቸውን በቀድሞው የሀ/ስብከቱ ማኅተምና ፕሮቶኮል ደብዳቤ በሀ/ስብከቱ ልሳን <i>ኆኅተ ጥበብ</i> ጋዜጣ ላይ በምክትል አዘጋጅነት አስቀጥረዋል፡፡</p>
<p><b>‹‹ሁሉ ቤቱን ሠርቶ እኔ ብቻ ቀርቻለኹ›› </b>በማለት ማማረር ጀመረዋል የሚባሉት ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል ከዚህ ቀደም÷ <i>‹‹ለጳጳስ ቍሪት/ንብረት የለውም – ጎመን የሚዘራበት፣ ሽንኩርት የሚተክልበት፤ ንብረቶቹ ምእመናን ናቸው›› </i>በማለታቸው የተደሰቱባቸው ወገኖች<i> </i>በቡራዩና በሰሚት(?) በሚገኙ የከተማ ቦታዎች ቤት እየሠሩ የመኾናቸው ወሬ ሲሰሙ ‹‹ኧረ ምን ሊኾናቸው›› ብለው ማዘናቸው አልቀረም፡፡ ‹ሥራውን›ም የሀ/ስብከቱ ሓላፊዎች እንዲያስተባብሩላቸው ያዝዟቸዋል ተብሏል – ልክ እነንቡረ እድ ኤልያስ <b>‹‹አምስቱ ከለባት››</b>የሚባሉትን <i>የደብር አለቆች፣ ጸሐፊዎች፣ ሒሳብ ሹሞች፣ ቁጥጥሮችና ገንዘብ ያዦች</i> ቢያጆ አሸዋና ሲሚንቶ እያስገለበጡ እንዳሠሩት ማለት ነው፡፡</p>
<p>ሊቀ ጳጳሱ ለቤት ሥራው እንዲተባበሯቸው ከሚያገብሯቸው የሀ/ስብከቱ ሓላፊዎች አንዱ ሥራ አስኪያጁ መልአከ ጽዮን አባ ኅሩይ ወንድይፍራው ናቸው፡፡ በሀ/ስብከቱ የሰፈነውን የሙስናና የዘመድ አዝማድ አሠራር ወደ ዐደባባይ አውጥቶ አነጋጋሪ ያደረገው አጋጣሚ፣ ሊቀ ጳጳሱ የምዕራብ አዲስ አበባ ሀ/ስብከት ሥራ አስኪያጅ በመኾን በቋሚ ቅ/ሲኖዶስ ውሳኔ የተመደቡትን መልአከ ጽዮን አባ ኅሩይን ባለፈው ሳምንት፣ በቁጥር 765/4/05 በቀን 07/09/2005 ዓ.ም ከሓላፊነታቸው ከማገዳቸው ተያይዞ ተነሥቷል፡፡<a href="http://haratewahido.files.wordpress.com/2013/05/aba-hiruy-complaints1.jpg"><img alt="Aba Hiruy complaints" src="http://haratewahido.files.wordpress.com/2013/05/aba-hiruy-complaints1.jpg?w=261&amp;h=363" width="261" height="363" /></a></p>
<p>የእግዱ ምክንያት <i>‹‹ከሊቀ ጳጳሱ ዕውቅና የተሠሩ ሥራዎች ናቸው››</i> ቢባልም ከሊቀ ጳጳሱ ዕውቅና ውጭ አንዳችም ነገር አለመፈጸማቸውን ነው አባ ኅሩይ ሲናገሩ የሚደመጡት፡፡ ‹‹እርሳቸው ያልመሩትን ሥራ አልሠራኹም፤›› የሚሉት ሥራ አስኪያጁ፣ በሀ/ስብከቱ የተሰገሰጉና የጥቅም ሰንሰለት የዘረጉ ‹‹የሊቀ ጳጳሱ ቤተሰቦች›› በሊቀ ጳጳሱ ስም የሚፈጽሙትን ሕገ ወጥ ተግባር እንዲጠነቀቁበት ገልጠው መናገራቸው ከበደል እንደተቆጠረባቸው ያስረዳሉ፡፡</p>
<p>በሥራ አስኪያጅነት የተመደቡት በቋሚ ቅ/ሲኖዶሱ እንደኾነ ያስታወሱት መልአከ ጽዮን አባ ኅሩይ፣ ከሓላፊነት የታገዱበት ርምጃ በራሱ ‹‹አቡነ ሕዝቅኤል በሌላቸው ሥልጣንና ሓላፊነት›› የወሰዱት ነው፡፡ በመኾኑም<i>‹‹ይህ ዐይነቱ አሠራር ለቤተ ክርስቲያኗና ለእምነታችን አደጋ ኾኖ ከመገኘቱም ባሻገር በታማኝነትና በቅንነት ለማገልገል ለቆሙና ለሚቆሙ ሰዎች የሞራል ስሜት የሚያሳጣ ስለሆነ ያለሥልጣንና ያለሕግ የተጻፈብኝ ደብዳቤ ይነሣልኝ››</i> ሲሉ በሊቀ ጳጳሱ የተላለፈባቸውን እግድ በመቃወም ለብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪኩ የጻፉት ደብዳቤ ያመለክታል፡፡</p>
<p>በሌላ በኩል ሊቀ ጳጳሱ በሥራ አስኪያጁ ላይ ያስተላለፉትን እግድ ተቃውመዋል የተባሉት የሀ/ስብከቱ አድባራት አስተዳደሮች፣ ለብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪኩ በጽሑፍ ባስታወቁት ዝርዝር አቤቱታቸው÷ ሊቀ ጳጳሱ ሥራ አስኪያጁን መልአከ ጽዮን አባ ኅሩይንና የቀድሞውን ጸሐፊ መጋቤ ሥርዐት ደስታ ጌታሁንን ከሓላፊነት በማገድና በማንሣት የወሰዷቸው ርምጃዎች መንሥኤ <b>‹‹ጎጠኝነትና ሙሰኝነት ነው››</b> በሚል እንደማይቀበሉት አስታውቀዋል፡፡</p>
<p>በተቃውሞ አቤቱታው ላይ የተጠቀሰውና በሊቀ ጳጳሱና በሥራ አስኪያጁ መካከል ለተፈጠረው አለመግባባት ዋነኛ መነሻ የተባለው ግን፣ በስድስተኛው ፓትርያሪክ ምርጫ ጋራ ከሀ/ስብከቱ በመራጭነት እንዲሳተፉ የተለዩት ሰዎች <b>ትውልዳዊ ማንነት</b> መኾኑ በእጅጉ አሳዛኝ ነው፡፡ በአቤቱታው እንደተመለከተው፣ ከሀ/ስብከቱ ተወክለው በፓትርያሪክ ምርጫው እንዲሳተፉ ከተለዩት 13 ልኡካን 12ቱ(ሥራ አስኪያጁ ሲቀሩ)<i>የምርጫ ሕጉ ድንጋጌ እንደሚያዝዘው ሊቀ ጳጳሱ በሚመሩት የአስተዳደር ጉባኤ ሳይሆን በሊቀ ጳጳሱ ቀጥተኛ ውሳኔ የተመረጡ</i> ቀራቢዎቻቸውና ዘመዶቻቸው ናቸው፡፡</p>
<p><a href="http://haratewahido.files.wordpress.com/2013/05/south-and-west-a-a-diosces-manager.jpg"><img alt="South and West A.A Diosces manager" src="http://haratewahido.files.wordpress.com/2013/05/south-and-west-a-a-diosces-manager.jpg?w=210&amp;h=239" width="210" height="239" /></a></p>
<p>መልአከ ጽዮን አባ ኅሩይ ወንድይፍራው</p>
<p>12ቱ መራጭ ልኡካን ሀ/ስብከቱ ካሉት 33 ያህል አጥቢያዎች  መካከል ከስድስት አጥቢያ ብቻ የተመረጡ ነበሩ የሚሉት የዜናው ምንጮች፣ ሥራ አስኪያጁ እንደ ሊቀ ጳጳሱ ቃል በሊቀ ጳጳሱ ቀጥተኛ ውሳኔ የተመረጡትን ልኡካን በቃለ ጉባኤ አስደግፈው ለአስመራጭ ኮሚቴው እንዲልኩ የተላለፈላቸውን ትእዛዝ አለመቀበላቸው ግልጽ ግጭት ውስጥ እንደከተታቸው ያብራራሉ፡፡ በምትኩ የሀ/ስብከቱ አስተዳደር ጉባኤ ባካሄደው<b>‹‹የብሔር ተዋፅኦ የጠበቀ››</b> የመራጮች ልየታ በፓትርያሪክ ምርጫው የሊቀ ጳጳሱ ደጋፊዎች እንዲኾኑ የተዘጋጁት ልኡካን በቁጥር በማነሳቸው ለሥራ አስኪያጁ<b>‹‹ከምርጫው በኋላ እንገናኝ››</b> የሚል ዛቻ እንዳተረፈላቸው ምንጮቹ አልሸሸጉም፡፡</p>
<p>የአቤቱታው አቅራቢዎች እንደሚያምኑት፣ አሁን መልአከ ጽዮን አባ ኅሩይን ከሥራ አስኪያጅነት ሓላፊነት በማገድ የተገለጸው ርምጃ <i>‹‹የአቡነ ሕዝቅኤል የፓትርያሪክነት ሥልጣን ጥማት የወለደው በቀል››</i> ነው፤ ሊቀ ጳጳሱ ከምደባቸው ጀምሮ የጠሏቸውን አባ ኅሩይን ከሥራቸው ሊያሳግድ የሚያስችል በቂ ምክንያት ይነቀስ ቢባል ከስም ማጥፋት ያለፈ አንድም ነጥብ እንኳ ማቅረብ እንደማይቻልም ርግጠኞች ናቸው፡፡ ለብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪኩ ያቀረቡትን አቤቱታ ሲያጠቃልሉም <i>‹‹የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጠባቂዋና መሪዋ እንደመኾንዎ መጠን ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል እያራመዱ ያሉት ግፍና በደል ሙስናና ዘረኝነት ቆሞ ከዚህ ሁሉ የጸዳ ሥራ እየሠሩ ያሉት አባ ኅሩይ ከቅዱስነትዎ መመሪያ ወርዶ በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ እስኪዛወሩ ድረስ አቡነ ሕዝቅኤል በሰብል መሰብሰቢያ ወቅት የሰጧቸው እግድ ተነሥቶላቸው የዘሩትን ዘር ምርቱን እንዲሰበስቡ እንዲደረግ ቅዱስነትዎ ቆራጥ አመራርና ርምጃ ወስደው መመሪያ እንዲሰጡልን ከእግረ መስቀልዎ ዝቅ ብለን እናመለክታለን››</i> በማለት ጠይቀዋል፡፡</p>
<p>የሥራ አስኪያጁ ማመልከቻ የደረሳቸው ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪክ አቡነ ማትያስ÷ የመ/ፓ/ጠ/ቤ/ክ ጽ/ቤት ውዝግቡን እንዲያጣራ፣ የማጣራቱ ተግባር እስኪጠናቀቅ ድረስ በሊቀ ጳጳሱ የተላለፈው እግድ ተነሥቶ መልአከ ጽዮን አባ ኅሩይ ወደ ሓላፊነታቸው ተመልሰው ሥራቸውን እንዲቀጥሉ አባታዊ መመሪያ መስጠታቸው ተሰምቷል፡፡ ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ መመሪያው በብፁዕ ዋ/ሥራ አስኪያጁ ወይም በጽ/ቤታቸው ተፈጻሚ እንዳልኾነ የተገለጸ ሲሆን ይህም የቅ/ሲኖዶሱ ዋና ጸሐፊ በኾኑት ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤልና በብፁዕ ዋ/ሥራ አስኪያጁ አቡነ ፊልጶስ መካከል ባለው ተዘምዶ የመረዳዳት ኹኔታ ተደርጎ ተወስዷል፡፡</p>
<p>ለፓትርያሪኩ እንደ <i>ልዩ ሀ/ስብከት</i> በሚቆጠረው አራቱ የአዲስ አበባ አህጉረ ስብከት በአንዱ በተፈጠረው በዚህ አለመግባባት፣ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በሰጡት መመሪያ ቅር የተሰኙት አቡነ ሕዝቅኤል በበኩላቸው÷ ለእግድ ርምጃቸው ድጋፍ ለማሰባሰብ ይመስላል የምዕራብ አዲስ አበባ ሀ/ስብከት አጥቢያ አብያተ ክርስቲያን <i>አስተዳዳሪዎችን፣ ጸሐፊዎችን፣ ሒሳብ ሹሞችን፣ ቁጥጥሮችንና ገንዘብ ያዦችን </i><b>በነገው ዕለት</b> በጽ/ቤታቸው ለማነጋገር ስብሰባ መጥራታቸው ተዘግቧል፡፡</p>
<p align="center">*             *            *</p>
<p>በብፁዕነታቸው ጥንተ ሀ/ስብከት – <i>ከፋ ሸካ ቤንች ማጂ አህጉረ ስብከት</i> – ጎልተው የሚሰሙ መሰል የመልካም አስተዳደርና ሙስና ችግሮችን ለጊዜው እናቆያቸው፡፡ ብፁዕነታቸው በአዲስ አበባ ደርበው በያዟቸው ሁለት አህጉረ ስብከትና እንደ ቅ/ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሚስተዋልባቸው አስተዳደራዊ ውሳኔ÷ <i>በሐቀኝነት በሚወሰዱና በጥቅመኞች ተጽዕኖ በሚገለባበጡ</i> አቋሞቻቸው መካከል የሚዋልልና <i>ምልስ ቅልስ የበዛበት</i> እንደኾነ ተጨማሪ ማሳያዎች እየተነቀሱ የሚቀርቡባቸው ትችቶች ጥቂቶች አይደሉም፡፡</p>
<p><b>ትችት (፩)፤</b> አባ ዮናስ መልከ ጼዴቅ ይባላሉ፡፡ በምዕራብ አዲስ አበባ ሀ/ስብከት የቶታል ሰፈረ ገነት ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ ናቸው፡፡ ደብሩ ለሚያሠራው ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን የሚያስፈልገውን ሞያዊ አበርክቶ አቅሙና በጎ ፈቃዱ ባላቸው የቤተ ክርስቲያን ልጆች በማሟላት <b>ከ20 ሚልዮን ብር በላይ</b> ወጪ ለማዳን ከምእመናን የቀረበላቸውን ሐሳብ በተለያዩ ስልቶች ውድቅ በማድረግ፣ በጥቅም ለተሳሰሩት አካል ያለግልጽ ጨረታ ይሰጣሉ፡፡ ምእመናን አካሄዱን ተቃውመው አምስት ጊዜ ወደ ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል እየተመላለሱ አቤት ቢሉም የብፁዕነታቸው አቋምና ውሳኔ ከአስተዳዳሪው ጋራ ነበር፡፡</p>
<p>ይኹንና ምእመናኑ አቤቱታቸውን አጠንክረው ለበላይ አካል በማሰማታቸው ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪኩ ለመ/ፓ/ጠ/ቤ/ክ ምክትል ሥ/አስኪያጅ በሰጡት መመሪያ አላግባብ በጥቅም ትስስር የተሰጠው የሕንጻ ግንባታ ፕሮጀክት አፈጻጸም ውሳኔ ተሽሮ ቤተ ክርስቲያን በልጆቿ ሞያዊ በረከት እንድትገለገልና ከከፍተኛ ወጪ እንድትድን ተደርጓል፡፡</p>
<p>ብፁዕነታቸው ግን በውሳኔው ደስ አልተሰኙም፡፡ እንዲያውም እልክ በመጋባት ይመስላል <i>ከደብረ ሣህል ጻድቃኔ ቅድስት ማርያም እስከ መርካቶ ደ/ኀ/ቅ/ ራጉኤል</i> የቤተ ክርስቲያንን መሬትና ንብረት እየሸጡ የግል ጥቅማቸውን በማካበት፣ ከዚህም ጋራ በተያያዙ የፍ/ቤት ክሦችና ንጽሕ ከመጠበቅ አኳያ በሚቀርቡባቸው አቤቱታዎች የሚታወቁትን የደብሩን አስተዳዳሪ <b>በጅቡቲ ደ/ፀ/ቅ/ገብርኤል አስተዳዳሪነት ለማሾም</b>ጥረው አድርገው የነበረ ቢኾንም ይህም አልሠመረላቸውም – ከፓትርያሪኩ ልዩ ጽ/ቤትና የውጭ ግንኙነት የበላይ ሓላፊ ቢሮ የወጣው ትእዛዝ እንደሚያመለክተው ጥቅመኛው አባ ዮናስ ለጊዜውም ቢኾን ለዚህ ሓላፊነት የተገቡ ኾነው አልተገኙም፡፡</p>
<p><b>ትችት (፪)፤</b> ይኼኛው ትችት ብፁዕነታቸው በቅ/ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊነት ካለባቸው ሓላፊነት ጋራ የሚያያዝ ነው፡፡ ችግሩ በአጭሩ ሲገለጽ በድሬዳዋ ሳባ ደብረ ኀይል ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ሕንፃ ሥራ የተፈጸመውን ሙስናና ምዝበራ ይመለከታል፡፡ በውለታ ከተያዘው ጊዜ  በአምስት ዓመት በዘገየው የሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑ ግንባታ በአነስተኛ ግምት ከስድስት ሚልዮን ብር በላይ የምእመናን ገንዘብና የቤተ ክርስቲያን ንብረት ለተቋራጩና ለጥቅመኛ የሕንፃ አሠሪ ኮሚቴ አባላት ሲሳይ እንደተዳረገ ታምኗል፡፡</p>
<p>ይህም በቀደመው የጠቅላይ ቤተ ክህነቱ የቁጥጥር አገልግሎት ኦዲት ሪፖርትና ቅ/ሲኖዶስ ዳግመኛ በላከውና በም/ሥ/አስኪያጁ በተመራው አጣሪ ኮሚቴ ሪፖርት መረጋገጡ ተነግሯል፡፡ በተለይም ከመቶ በላይ በሚቆጠሩ ገጾች የተጠናቀረው የአጣሪ ኮሚቴው ሪፖርት ከአባሪ ማስረጃዎች ጋራ የቀረበላቸው የቅ/ሲኖዶሱ ዋና ጸሐፊ፣ ለሚመለከተው አካል በአጀንዳ አስይዘው እንዲያስወስኑ በተለያየ ጊዜ ከተደረጉት ጥረቶችና ማሳሰቢያዎች በተፃራሪ ሪፖርቱን <b>ለወራት አግተው</b> የመያዛቸው ምስጢር ለኮሚቴውና ለፍትሕ ፈላጊ የሀ/ስብከቱ ምእመናን ግርታን የሚፈጥር ኾኗል፡፡</p>
<p align="center">*             *            *</p>
<p>ብፁዕነታቸው በመልአከ ጽዮን አባ ኅሩይ ላይ ባስተላለፉት የእግድ ርምጃና እግዱ ተነሥቶ መንሥኤው እንዲጣራ ቅዱስነታቸው በሰጡት አባታዊ መመሪያ መካከል የታየው ልዩነት የመጀመሪያ እንዳልኾነ የሚናገሩት የመንበረ ፓትርያሪኩ ምንጮች፣ ኹኔታው በአንድ በኩል÷ <b>ብቁ አመራር ከመስጠት አንጻር</b> ብፁዕነታቸው በመሠረቱ ያለባቸውን ውስንነት ያሳያል ይላሉ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ይህን ውስንነት የሚበዘብዙ<b>ቀራቢና ዘመድ ነን ባይ ጥቅመኞች በብፁዕነታቸው ዙሪያ መበራከታቸውን</b> እና ብፁዕነታቸውም <i>በማወቅም ይኹን ባለማወቅ</i><b>በተጽዕኗቸው መጠለፋቸውን</b> እንደሚያረጋግጥ ያምናሉ፡፡</p>
<div><a href="http://haratewahido.files.wordpress.com/2012/12/ab-hizkiel.jpg"><img alt="Ab Hizkiel" src="http://haratewahido.files.wordpress.com/2012/12/ab-hizkiel.jpg?w=235&amp;h=284" width="235" height="284" /></a>ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል</div>
<p>አሁን በአባ ኅሩይ ላይ የተላለፈውን እግድ መጽናት የሚጠባበቁ ሁለት ግለሰቦች እንዳሉ ተጠቁሟል፡፡ አንዱ፣ <i>የፓትርያሪኩን ልዩ ጽ/ቤትና የውጭ ግንኙነት መምሪያ</i> በሓላፊነት የመቆጣጠር ተስፋቸው የጨለመባቸውና ለአራት የተከፈለውን የአዲስ አበባ አህጉረ ስብከት <i>በአንድነት ይዞ ጥቅምን የማስፋት</i> ሌላ ከንቱ ተስፋ መሰነቃቸው የሚነገርላቸው ንቡረ እድ ኤልያስ ኣብርሃ ናቸው፡፡ ሌላው÷ በቀድሞው የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት <i>ሒሳብና በጀት ክፍል</i> ሓላፊ የነበሩቱ ናቸው፡፡ ግለሰቡ የሀ/ስብከት ሓላፊነታቸውን እንደ ትርፍ ጊዜ ሥራ ይሠሩ የነበሩ፣ በሙሉ ጊዜያቸው ግን በአንድ የግል ባንክ ውስጥ <b>በአካውንቲንግ ሞያ በመደበኛ ሠራተኝነት የተቀጠሩ፣ በዓለ ሆቴል</b> መኾናቸው ተገልጧል፡፡</p>
<p>ሁለቱም በብፁዕነታቸው ዙሪያ በብፁዕነታቸው ስም ተጽዕኗቸውን ያጠናከሩ ግለሰቦችን በተላላኪነትና በሽምግልና እየተጠቀሙ መኾናቸው ተገልጧል፡፡ በዚህም እንደተባለው በወቅቱ የሀ/ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ላይ ያለማስረጃ ተላልፏል የተባለው እግድ ከጸና በቋሚ ሲኖዶስ ስብሰባ በብፁዕነታቸው ለሥራ አስኪያጅነት የመጠቆም ዕድል እንደሚያገኙ ተስፋ ያደርጋሉ¡¡</p>
<p>ይህና ይህን የመሳሰሉት የጥቅመኞች ተስፋዎች ግን÷ በመጪው የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ <i>ከመንበረ ፓትርያሪኩ ጀምሮ የጠቅላይ ቤተ ክህነቱን አስተዳደር በተዋረድ በዘመናዊ መልክ ለማዋቀርና ዘመኑን የዋጀ ቀልጣፋ አሠራር ለመዘርጋት በሚያስችል የባለሞያ ጥናት</i> ላይ ለመወያየት ከጥቅምት ምልአተ ጉባኤ ያደረ አጀንዳ ለያዘው ቅዱስ ሲኖዶስና የቅዱስነታቸው አስተዳደር አንዱ መፈተኛው ይኾናል፡፡</p>
<p>እኒህን የመሳሰሉ የጥቅመኞችን ተስፋዎች መሥመር ማስያዝ÷ <b>በፀረ ሙስናና በልማት እንዲሁም በሰላምና በመልካም አስተዳደር ዙሪያ</b>ከሚመለከታቸው አካላት ጋራ የተጠናከረ ሥራ ለመሥራት <b>ከምንጊዜውም በላይ የተዘጋጀች እንደኾነች</b> በጥቅምቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ውሳኔዎች መግለጫ ላይ ያስታወቀችው ቤተ ክርስቲያናችን ዝግጁነት የሚለካበት እንደኾነ ጥርጥር የለውም፡፡</p>
<p>ምዕራብ÷ ‹‹ዕርበተ ፀሓይ›› የሚፈጸምበት ዐቢይ ማእዘን የመኾኑን ተፈጥሯ ሥራት በምሳሌነት በመያዝ <i>በምዕራብ አዲስ አበባ ሀ/ስብከት</i><i>አስተዳደር </i>የተቀሰቀሰው ውዝግብ አፈታት÷</p>
<ul>
<li><b>የቤተ ክርስቲያናችን የፀረ ሙሰኝነትና ፀረ ጎጠኝነት አቋም ትርጉም ባለው ደረጃ የሚታይበት፣</b></li>
<li><b>አዲስ አበባ በአራት አህጉረ ስብከት የመደራጀቱ ፋይዳ በቅርጹም በይዘቱም የሚፈተሽበት፣</b></li>
<li><b>ከሁሉም በላይ ያዘቀዘቀችውና ድልህ የመሰለችው የሙሰኞችና ጎጠኞች ‹ጀንበር› ዳግመኛ ላትወጣ ግባቷ (መጥለቋ) የሚረጋገጥበት እንዲኾን እንመኛለን፡፡</b></li>
</ul>
<p><i>‹‹የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ለአራት መከፈል ሙስናውን ጨርሶ ባያስወግደውም ይቀንሰዋል ብለን ተስፋ እናደርጋለን፡፡››</i> /ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል፣ ጥቅምት 2005 ዓ.ም/፡፡</p>
<p>&nbsp;</p>
<p><b>በመልአከ ጽዮን አባ ኅሩይ ወንድይፍራው ላይ የተላለፈውን እግድ በመቃወም ለብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪኩ የቀረበው የጽሑፍ አቤቱታ<a href="http://haratewahido.files.wordpress.com/2013/05/petition-by-west-a-a-dioseces-001.jpg"><img alt="Petition by west A.A Dioseces 00" src="http://haratewahido.files.wordpress.com/2013/05/petition-by-west-a-a-dioseces-001.jpg?w=600" /></a><a href="http://haratewahido.files.wordpress.com/2013/05/petition-by-west-a-a-diseces-011.jpg"><img alt="Petition by West A.A Diseces 01" src="http://haratewahido.files.wordpress.com/2013/05/petition-by-west-a-a-diseces-011.jpg?w=600" /></a><a href="http://haratewahido.files.wordpress.com/2013/05/west-a-a-petition-031.jpg"><img alt="West A.A Petition 03" src="http://haratewahido.files.wordpress.com/2013/05/west-a-a-petition-031.jpg?w=600" /></a><a href="http://haratewahido.files.wordpress.com/2013/05/petition-by-west-a-a-dioseces-031.jpg"><img alt="Petition by West A.A Dioseces 03" src="http://haratewahido.files.wordpress.com/2013/05/petition-by-west-a-a-dioseces-031.jpg?w=600" /></a></b></p>
<p>&nbsp;</p>
<p>ምንጭ፡ ሐራ ተዋሕዶ</p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/732"     class="crp_title">(ሰበር ዜና )አቡነ ማትያስ የኢትዮጵያ</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/493"     class="crp_title">ስለ መንበረ ፕትርክናው ዕጩዎች&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/683"     class="crp_title">የ5ቱ እጩ ፓትርያርክ ማንነት በጥቂቱ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/241"     class="crp_title">ኮሚቴው የፓትርያሪክ ምርጫ ሕገ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3294"     class="crp_title">ጠ/ቤተ ክህነት የመምህር ግርማ&hellip;</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=83422</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>በጎንደር ህዝቡ ደፍሮ በአደባባይ ተቃውሞውን አሰማ (VIDEO)</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3501</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3501#comments</comments>
		<pubDate>Thu, 23 May 2013 01:55:58 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3501</guid>
		<description><![CDATA[
Related Posts:ጽናት &#8211; ሁሉም ሊያየው የሚገባ&#8230;‹‹313 ሚሊዮኑ ለልማት!›› በሚል መሪ&#8230;የኮሜዲያን አዜብ መስፍን አዲስ&#8230;ቦንድ ለመሸጥ ሳዑዲ የገባው ወ]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p><iframe width="500" height="360" src="http://www.youtube.com/embed/05zC8dBw01U" frameborder="0" allowfullscreen></iframe></p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2804"     class="crp_title">ጽናት &#8211; ሁሉም ሊያየው የሚገባ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2468"     class="crp_title">‹‹313 ሚሊዮኑ ለልማት!›› በሚል መሪ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1299"     class="crp_title">የኮሜዲያን አዜብ መስፍን አዲስ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/13"     class="crp_title">ቦንድ ለመሸጥ ሳዑዲ የገባው ወያኔ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2536"     class="crp_title">በኖርዌይ የሚኖሩ ጀግና&hellip;</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=83402</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>ወይ መላ ነሽ አሉ ወይ መላ አባ መላ!</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3495</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3495#comments</comments>
		<pubDate>Wed, 22 May 2013 21:12:39 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3495</guid>
		<description><![CDATA[ከሎሚ ተራተራ እነደምን ከርማችሁ ወዳጆች ? እኔ አምላክ ይክበር ይመሰገን ደህና ነኝ። ሰሞኑን ከወደ ትውልድ አገር የመጡን አዛውንት እንኳን ደህና መጡ፤ የሰሜን አሚሪካ አየርሰ እንዴት ተቀበሎት ለማለት ወደ ጎረቤት ቤት፤ ጎራ ብዪ ነበርና፤ አረፍ እንዳልኩ አንድ ቀደም ብሎ ባለሁበት ከተማ ለጥቂት ወራት በርቀት ዝቅ ብለው እጅ በመንሳት የሃገሬን ተናፋቂ ባህል የሚያሰታውሱኝና እጀግም የማከብራቸውን አባት ድምጥ [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3398">በላተኛው አባ-መላ</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3454">በላተኛው አባ-መላ  ከያሬድ አይቼህ</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/872">በደቡብ አፍሪካ በአቡነ ያዕቆብ ላይ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1037">“ልጄ በእሳት ተቃጥላ እንድትሞት&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/742">አወዛጋቢ የተባሉት ፓትሪያርክ አቡነ</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/aba-mela.jpg"><img class="alignleft size-medium wp-image-3399" alt="aba mela" src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/aba-mela-300x225.jpg" width="300" height="225" /></a></p>
<p><em>ከሎሚ ተራተራ</em></p>
<p>እነደምን ከርማችሁ ወዳጆች ? እኔ አምላክ ይክበር ይመሰገን ደህና ነኝ። ሰሞኑን ከወደ ትውልድ አገር የመጡን አዛውንት እንኳን ደህና መጡ፤ የሰሜን አሚሪካ አየርሰ እንዴት ተቀበሎት ለማለት ወደ ጎረቤት ቤት፤ ጎራ ብዪ ነበርና፤ አረፍ እንዳልኩ አንድ ቀደም ብሎ ባለሁበት ከተማ ለጥቂት ወራት በርቀት ዝቅ ብለው እጅ በመንሳት የሃገሬን ተናፋቂ ባህል የሚያሰታውሱኝና እጀግም የማከብራቸውን አባት ድምጥ ሰማሁ።</p>
<p>እንድምነ ዋላችሁ አሉ አቶ በልሁ፤ ድምጣቸውን ያለወትሮዎቸው ለዘብ አድረገው፤ ;;’’’’’ እግዚአብሒር ይመሰገን”’ እንደምን ዋልክ በልሁ ግባ፣ ምነው ? ምን አዲሰ ነገር ሰማህ ደግሞ ድምጥህ ያለወትሮው ለዘብ ብሏል አሉ አቶ ታከለ፤ የዛሪን አያረገወና ልጆቻቸውን ለማየት ወደ ሰሜን አሜሪካ ከመጡ ወዲህ ቀረ እንጂ ድሮማ ሰው ሁሉ የሚጠራቸው “ አልሞ ተኳሸ” እያለ ነበር አሉ።</p>
<p>አቶ በልሁና አቶ ታከለ ለረጅም ግዜ ወዳጆች ከመሆናቸውም ሌላ በወቅቱ የሀገራችን ጉዳይ ዙሪያ ዘወትር በቁጭት ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ካላቸው ሃገራዊ ፍቀር በመነሳት መደረግ ሰለሚገባው የሃገር ጉዳይ ፤ በተለይም እንዴት አንድነታቸንን መገንባት እንደሚገባን አበክረው ከሚናገሩት የአካባቢያቸን የሰሜን አሜሪካ አዛውንቷች ዋናዎቹ ናቸው።</p>
<p>ወዲያዉ እግራቸው እንደገባ ወንበርም ላይ ሳይቀመጡ አዬ…; ተወኝ እባክህ…..ሲሉ የሰሙትን ለማጫወት ጀመሩ።, እኔም ኖር;……. በዪ እጅ ከነሳሁ በሗላ ጆሮዪን ሰጥቼ ማዳመጥ ቀጠልኩ፣…… ይገርምሃል ሰሞኑን በዚህ በ “ቡል” ቶክ…ነው.. ”ፓል”ቶክ,,….የሚባል…. የመወያያ መደረክ….. አዪ……ለነገሩ እኔ ይሔንን የመወያያ መድረክ ሳይሆን….”የወሬ ቋት” ነው የምለው። አሉና… ቀጠሉ.. አንድ “አባ…መላ….የሚባል….የ..ወያኔዎቹ አፈቀላጤ.. ሚሰጥር አጋለጠ።……የወያኔን..የግፍ ሰራ መደበቅ (መሸፈን) ደከመኝ..ብሎ ተቃውሞ ሲያሰማ ዋለ። ብዙም ሚሰጥር የማወቀው አለ ብሏል..’…. እያለልሕ …..አዳሜ ተሰበሰቦ ….”ውይ መላ ነሸ አሉ ወይ መላ አባ መላ እያለልህ” ከበሮ፤ ይደልቃል።</p>
<p>ሲሉ ከልቤ ሳቅኩና፤ ፈጠን በዪ ማጋለጡ፣ መልካም አይደለምወይ ብዪ ? ጠየቀኳቸው? ሲመልሱ….እሱማ..መልካም..ነው። አሰገራሚዉ ነገር እኮ አራት ቀን ሙሉ..እንደውም አምሰተኛው ቀን ይኸው መጣ ተሰበሰቦ ማዳነቅ ምን ይሰራል? የተገኝወን መረጃ ሰበሰቦ ተግባራዊ ሰራ ላይ ማተኮር ነው የሚበጀው።</p>
<p>ብለው ሲሉ. በዚሁ ቃላቸው ተሰማምቼ እቸኩል ሰለነበር የሚጣፍጠውን ጫዋታ ገና በእፍታው፤ ትቼ በሉ ደህና ይዋሉ ብዪ ተሰናብቼ ወጣሁና፤ እቤቴ እሰክደርሰ” ወይ መላ ነሸ አሉ ወይ መላ አባ መላ” አሉ አቶ በልሁ፤ እያልኩ እያሰላሰልኩ እቤቴ ደርሰኩና ይቺን ለመጫጫር በቃሁ እላችኸላሁ።</p>
<p>ከላይ ለመመልከት እንደሞከርነው “ወይ መላ ነሸ አሉ፣ ወይ መላ አባ መላ” እያሉ ከበሮ መደልቅ; አባታችን አቶ በልሁ እንዳሉት አይጠቅመንምና መላው ዳይሰፖራውን ይታሰብበት እያለኩ፤ ከዚህ የሚከተለውን ይበጀናል ያልኩትን ብትጠቀምም ባትጠቅምም መፍትሄ ነው። ብዪ ሰለማምን ጀባ እላለሁ።</p>
<p>ዳይሰፖራው ማተኮር የሚገባው፦</p>
<p>1ኛ) በተገኝው ማንኛውም ይጠቅማል የተባሉትን ኢንፎረሜሸኖች በማሰባሰብና በማጠናከር ላልሰማውና ላልተረዳው፣ የህበረተሰብ ክፈል እነዲደርሰ ማደረግና ለውጤቱም ተግቶ መሰራት።</p>
<p>2ኛ) ከማንኛወም አይነት የጥላቻና የ መጎነታተል ወይም የመናናቅ የ ትግል ሰልት መራቅና ወቅታዊና አንገብጋቢው በሆነው የሃገራችን ቸግርላይ በማተኮር ሳንሰልችና ሳንታክት እያንዳንዳችን የድርሻችንን በቅንነትና በኢትዮጲያዊ ጨዋነት ማበርከት።</p>
<p>3ኛ) በወቅታዊው የሃገራቸን የፖሎቲካ፣ የ ኢኮኖሚም ሆነ የመሃበራዊ ችግሮቻችንን እና መፍትሄዎቻቸውንም ጭምር ባለሞያ ወንድሞቻችንንም ሆነ እህቷቻችንን በመጋበዝ ህብረተሰባችን ሰለወቀታዊው የሃገር ችግርና መፍትሄው ማወያየት።</p>
<p>4ኛ) የፖሎቲካ ድረጀቶችም የኔ የፖሎቲካ ፐሮገራም ነው ለወቀታዊው የሃገራችን ችግር ብቸኛ መፍትሄ የሚሆንው። ከሚል አሰተሳሰብ ወጥተን የጋራ የሆነወን የገጠመንን የሃገር ችግር በጋራ አፋጣኝ መፍትሄ ለማምጣት በመቻቻል፤ ተግቶ በጋራ በመሰራት አገር ወሰጥ ላሉት ለፖሎቲካ ድረጅቶች መልካም ኢትዮጲያዊ ሰሜትን በሁሉም መሰክ በመተግበር አጋርንትን በተገበር ማሳየት።</p>
<p>5ኛ) ከሁሉም በላይ ለምናልመውና ለማይቀረው የህዝብ የሃግር ባለቤትነት እያነዳንዱ ዜጋ ድርሻዪ ምንድነው ? በማለትና ለተግባራዊነቱም እውቀቱንም፤ ጉልበቱንም፤ ገንዘቡንም ህይወቱንም ሳይቅር ለመሰዋት የተዘጋጀ መሆን እንዳለበት ማረጋገጥ ነው።</p>
<p>ይህንን ካልተረዳና ለተግባራዊነቱም ካልተዘጋጀን በሰተቀር ቀደም ብዪ በመግቢያዪ ላይ እንደገለጥኩተ ትርፉ አቶ በልሁ እናዳሉት”…</p>
<p>ሆይ… መላ… ነሸ… አሉ… ሆይ,,.. መላ… አባ… መላ…</p>
<p>ነውና… እነዲህ አይነቱን… ባዶ… ከበሮ… ከመደለቅ… ያውጣን! አሜን!!!</p>
<p>በተመሳሳይ መጣጥፍ እሰክንገናኛ ደህና ሁኑ በቸር ይግጠመን! ችርም ያሰማን!</p>
<p>ከሎሚ ተራ ተራ</p>
<p>Wednesday, May-22-13</p>
<p>አሰተያየትዎን/ነቀፊታዎንም ቢሆን: mwl200825@yahoo.com</p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3398"     class="crp_title">በላተኛው አባ-መላ</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3454"     class="crp_title">በላተኛው አባ-መላ  ከያሬድ አይቼህ</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/872"     class="crp_title">በደቡብ አፍሪካ በአቡነ ያዕቆብ ላይ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1037"     class="crp_title">“ልጄ በእሳት ተቃጥላ እንድትሞት&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/742"     class="crp_title">አወዛጋቢ የተባሉት ፓትሪያርክ አቡነ</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=83400</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት የሚመራው ሕጋዊው ቅዱስ ሲኖዶስ የአዲስ አበባው ሕገ ወጥ ሲኖዶስ ለበተነው የሐሰት ጽሑፍ የተሰጠ መልስ</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3488</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3488#comments</comments>
		<pubDate>Wed, 22 May 2013 15:51:28 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3488</guid>
		<description><![CDATA[ቅዱስ ዳዊት እናንተ የሰው ልጆች እስከ መቼ ድረስ ልባችሁን ታከብዳላችሁ በማለት ለንስሐ ስፍራ ሳይኖራቸው ሐሰትን ፀንሰው አመፃን የወለዱትን ሰዎች የገሠጸበትን የቅዱስ መጽሐፍን ኃይለ ቃል መነሻችን ያደረግነው አለምክንያት አይደለም ። ለማንበብ እዚህ ይጫኑ &#160;<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1380">የኦሃዮ ደ. መድሃኒት መድሃኔዓለም&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/814">የኖርዝ ካሮላይና መካነ ብርሃን&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/892">የአ.አበባው ሲኖዶስ ታዛቢዎች&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1222">[ሰበር ዜና - Breaking News] የዳላሱ ቅዱስ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/649">በኒውዮርክና በአካባቢው ከምንገኝ&#8230;</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/Tewahdo.jpg"><img class="alignleft size-full wp-image-3490" alt="Tewahdo" src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/Tewahdo.jpg" width="243" height="228" /></a>ቅዱስ ዳዊት እናንተ የሰው ልጆች እስከ መቼ ድረስ ልባችሁን ታከብዳላችሁ በማለት ለንስሐ ስፍራ ሳይኖራቸው ሐሰትን ፀንሰው አመፃን የወለዱትን ሰዎች የገሠጸበትን የቅዱስ መጽሐፍን ኃይለ ቃል መነሻችን ያደረግነው አለምክንያት አይደለም ።</p>
<h2><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/Response_to_false_claim_from_Ethiopia.pdf" >ለማንበብ እዚህ ይጫኑ</a></h2>
<p>&nbsp;</p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1380"     class="crp_title">የኦሃዮ ደ. መድሃኒት መድሃኔዓለም&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/814"     class="crp_title">የኖርዝ ካሮላይና መካነ ብርሃን&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/892"     class="crp_title">የአ.አበባው ሲኖዶስ ታዛቢዎች&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1222"     class="crp_title">[ሰበር ዜና - Breaking News] የዳላሱ ቅዱስ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/649"     class="crp_title">በኒውዮርክና በአካባቢው ከምንገኝ&hellip;</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=83364</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>‹‹አድርባይነት›› የወያኔ/ኢህአዴግ መለያ ባህሪው ነው።‹‹አድርባይነት›› ምን ማለት ነው?</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3484</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3484#comments</comments>
		<pubDate>Wed, 22 May 2013 14:46:39 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3484</guid>
		<description><![CDATA[ከዘካሪያስ አሳዬ አንድ መልካም እድል ሲገኝ በዚያ ዕድል ቀዳሚ ተጠቃሚ ለመሆን የሚያንቀዠቅዥ ልክፍት አለ። የዚህ ልክፍት መጠሪያም ‹‹አድር ባይነት›› (Opportunism) ይባላል።መልካም አጋጣሚ ወይም ዕድል (Opportunity) ሲገኝ በዚያች ለመጠቀም ያለምንም ይሉኝታ መሽቀዳደም፤በስተኋላ ሊከሰት የሚችለውን ጎጂ ውጤት እያወቁም ቢሆን ‹‹እንደ አመጣጡ እመልሰዋለሁ›› በሚል ድፍረት መግባት፣ ከየት አመጣ? እንዴት አገኘ? በምን ዘዴእዚህ ደረሰ? የሚሉ የህዝቡ ምን ይላል ጥያቄዎችን [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1758">አንሰማም!  ከዘካሪያስ አሳዬ</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1837">ቁም ነገር ተናጋሪ የሌለበት&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/180">የኢሕአዴግ ከፍተኛ የመንግስት&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1473">መልከ ጥፉ ነኝ ብዬ ስለማስብ ወንዶች&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2908">ሁለቱን በጣምራ/በአንድነት ማስኬድ&#8230;</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p>ከዘካሪያስ አሳዬ</p>
<p><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/04/Zekarias.jpg"><img class="alignleft  wp-image-1452" alt="Zekarias" src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/04/Zekarias.jpg" width="132" height="167" /></a>አንድ መልካም እድል ሲገኝ በዚያ ዕድል ቀዳሚ ተጠቃሚ ለመሆን የሚያንቀዠቅዥ ልክፍት አለ። የዚህ ልክፍት መጠሪያም ‹‹አድር ባይነት›› (Opportunism) ይባላል።መልካም አጋጣሚ ወይም ዕድል (Opportunity) ሲገኝ በዚያች ለመጠቀም ያለምንም ይሉኝታ መሽቀዳደም፤በስተኋላ ሊከሰት የሚችለውን ጎጂ ውጤት እያወቁም ቢሆን ‹‹እንደ አመጣጡ እመልሰዋለሁ›› በሚል ድፍረት<br />
መግባት፣ ከየት አመጣ? እንዴት አገኘ? በምን ዘዴእዚህ ደረሰ? የሚሉ የህዝቡ ምን ይላል ጥያቄዎችን ወደ<br />
ጎን አሽቀንጥሮ ጥሎ ጥቅም ፍለጋ ሲል ብቻ ለመሰል አለቆቹ እየተሽቆጠቆጠና የእሱ ቢጤዎችን እያሰባሰበ<br />
የሚንቀሳቀስበት አሰራር አድርባይነት ነው። ሰውሸንኮራ አገዳ አይደለም፤ እየተመጠጠ አይታይም። ከላይ<br />
ስታየው የሚጣፍጥ የመሰለህ አገዳ ገዝተህ ስትቀምሰው ሊጎመዝዝህ ይችላል። የአድርባይም ጉዳይ እንዲሁ ነው።አድርባይነት የተገኘውን መልካም አጋጣሚ ሁሉየግል ጥቅምና አላማን ለማስቀደም የሚደረግ የፖለቲካ<br />
አቋምን ያመለክታል። ጥቅም የሚያስገኝ እስከሆነ ድረስ ማንኛውንም አቋም ለማራመድ (ለመደገፍ) ቆርጦ<br />
መነሳትን፣ ለግምገማም ሆነ ለህጋዊ ተጠያቂነት ንቀት ማሳየትን፣ የህዝብን ውክልናና ስልጣን አሳንሶ ማየትን፣<br />
አይንን በጨው አጥቦ ለጥቅም ሲሉ ብቻ የድርጅቱን ራዕይመመሪያና ደንቦችን የህዝብን ትዝብትና ሃይማኖትንጭምር ጨፈላልቆ ለመሄድ ያለንን ውስጣዊ የጠባይ(የባህርይ) ዝግጁነት የሚያሳይ ክፉ አመለካከት ነው።አድርባይ ሰው በድርጅቱ የፖለቲካ አቋምአያምንም። ያመነ የሚመስለውና ከእሱ በላይ ተቆርቋሪ የሌለ እስኪመስል ድረስ ያዙኝ ልቀቁኝ እያለ ለመሪዎቹ(አለቆቹ) ፍቅር ያለው ይመስል የሚሽቆጠቆጠው ያቺን ያሰባትን ጥቅም በእጁ እስኪያስገባና ተጨማሪ ጥቅምለማግኘት የሚያስችል እድል (አጋጣሚ) Opportunity እስካለ ድረስ ብቻ ነው። ‹‹የራስ ጥቅምን መፈለግና ለዚህም ተግቶ መንቀሳቀስ ምን ችግር አለው?›› የሚልጥያቄ ሊነሳ ይችላል። ሁላችንም የምንሰራው ለመጠቀም<br />
ነው። ራሳችንንና ቤተሰባችንን ለማስተዳደር ሰው የደረሰበት ደረጃ ላይ ለመድረስ ነው። መሬት፣ መኪና፣<br />
ቤት፣ ኢንቨስትመንት፣ አካውንት፣ ደህና ዕቁብ ጥሩዕድር ቢኖረንና የጣፈጠ በልተን ያማረ ለብሰን ብንኖር<br />
አንጠላም። ይህ ደግሞ ኃላፊነት በሚሰማውና በእውቀትና በጉልበት ተሳትፎ ተሰርቶ የሚገኝ ሲሆን ደስ ይላል።እንደ ምርጫና ወዘተ&#8230; በመሳሰሉት አጋጣሚዎች በተገኘእድል ከህዝብ በተሰጠ አደራ የራስን ጥቅም ለማስቀደም የሚደረግ የፖለቲካ እሽቅድድም ግን አያዋጣም።አድርባይነት በፓርቲና በመንግስት ተቋማት ኃላፊዎችና ሠራተኞች አማካይነት ሲፈፀም ከፍተኛ ችግር ያስከትላል።ታማኝነት (Loyalty)&#8230; ግልፅነት (transparency)&#8230;ምስጢር ጠባቂነት (Confidentiality)&#8230; ሀቀኝነት(Honesty) ተጠያቂነት (Accountability) አለማዳላት(Impartiality)&#8230;ምላሽ ሰጪነት (Responsiveness)አርአያ መሆን (Exemplary) የህዝብ ጥቅም (Public<br />
Interest) ወዘተ&#8230; የሚባሉት መሰረታዊና ስትራቴጂክ የዕድገት እሴቶቻችን በሙሉ ጥንጣን እንደበላው የበረሃዛፍ ውስጥ ውስጡን እየተቦረቦሩ ያልቁና ራዕያችንን ገንድሰው ይጥሉብናል። ከዚያ ኋላማ ‹‹የማን ቤት ጠፍቶየማን ሊበጅ&#8230; የአውሬ መፈንጫ ይሆናል እንጂ›› እያልን እርስ በርስ ከመጨካከንና ከመተራረድ በቀር የሚተርፈን ነገር የለም።ይህ ማለት ደግሞ ሰዎችን ስንጠረጥራቸውእንኑር፣ ወይም በየጆሯቸው ስር መረጃ እናቁምባቸው፣ስህተታቸውን የሚያሳብቅ ቃጭል እናንጠልጥልላቸው ማለት አይደለም። ወደንና ፈቅደን እንደሰው መጠን አገናዝበን የመረጥናቸው ወኪሎቻችንና አገልጋዮቻችን ስለሆኑ አዲሶቹ በአድርባይነት በሽታ እንዳይለከፉና የተለከፉትም ከዚህ የአድርባይነት አስተሳሰብ እንዲወጡ በተቻለን አቅም እንርዳቸው፣ እናግዛቸው ማለት ብቻነው። አድርባይነት የስብዕና (Personality) ምስክርነው። የአመለካከት ችግር ነው። የሰዎች ስብዕናና አመለካከት የሚቀረፀው ደግሞ አንደወጡበት ቤተሰብና እንደ አደጉበት ማህበረሰብ ነው። ሌብነትን ከሚፀየፍ ቤተሰብና ማህበረሰብ የተገኘ ልጅ ሌብነት ውስጥ ሊገባ አይችልም። ወይም የመግባት እድሉ በጣም ጠባብ ነው።ስለዚህ የሰውዬውን ቤተሰብና ያደገበትን ማህበረሰብ ዳራ ማወቅ ይጠቅማል። አድርባይነትን ከሚያስፋፉ ባህርያት አንዱ ስኬታማ የመሆን ጥማት ነው።ከሌሎች ሰዎች ተሽሎ የመገኘት፣ የማሸነፍ፣ በውጤት፣በዝና በሀብት በልጦ የመገኘት (‹‹ወንዳታ›› የመባል)ውስጣዊ ፍላጎት ነው። ይህን ፍላጎት ለማርካት (ከግብለማድረስ) ሰውዬው ስልጣኑንና የተገኘውን መልካም አጋጣሚ ሁሉ በመጠቀም እስከየትኛውም ጫፍ ድረስ ይጓዛል። ከድርጅቱ (ከፓርቲው) እና ከሚሰራበት ተቋም መርሆዎች ጋር ፈጽሞና ፈጽሞ የማይጣጣሙ ዘዴዎችን(አሰራሮችን) እየተጠቀመና ጉሮሮ ለጉሮሮ እየተናነቀ<br />
ይሟሟታል። ይህ ደግሞ ለአድርባይነት ይዳርገዋል።ለአድርባይነት ከሚዳርጉ ምክንያቶች ሌላኛው የሰው ልጅያለው የስጋት (ስጋታምነት) ተፈጥሮ ነው። ለትንሹም ለትልቁም መስጋት ይወዳል። በሰላም አገር ‹‹ይገመግሙኝይሆን? ከደረጃ ዝቅ ያደርጉኝ ይሆን?&#8230; ይጠረጥሩኝይሆን?&#8230; ከቤተሰቤ ወደራቀ ቦታ ያዛውሩኝ ይሆን?ያባርሩኝ ይሆን?&#8230; ዕድገት ይከለክሉኝ ይሆን? እያለይጨናነቃል። ከዚያች ከያዛት ቦታ ቢለቅ ወይም ከዚያመስሪያ ቤት ቢወጣ ሰማይ የሚደፋበት ይመስለዋል።በራስ መተማመኑ ብን ብሎ ይጠፋበታል። ስለዚህ ህዝብ የጣለበትን አደራና ተቋሙ የሰጠውን ኃላፊነት እርግፍ አድርጎ ትቶ የጥቅመኛ አለቃው ሽቁጥቁጥ አሽከር(ባሪያ) ሆኖ ያርፈዋል። ‹‹ቢጭኑት አጋሰስ፤ ቢጋልቡት ፈረስ›› ይሆንና ሀሳብ አመንጭነትና ተነሳሽነት የጎደለው አስመሳይ ተራማጅ ሆኖ ይቀራል። ለድርጅቱም (ለተቋሙ)<br />
ሳይጠቅም ህዝቡ የጣለበትን አደራ ሳይፈጽም የትውልድ መዛበቻና የዘመን መሳለቂያ ሆኖ ያርፈዋል። ሌላው ጉዳይ ደግሞ አድርባይነት የሚያስገኘውን ጥቅም (pay off) ከፍአድርጎ የማሰብ አመለካከት ነው። ድርጅቱ ቢያባርረኝ፣ህዝቡ ቢታዘበኝ፣ ህግ ያለውን ቢለኝ አድርባይ ሆኜ አንድ ዝግ ከዘጋሁ ይካካስልኛል። የተቀጣሁትን ሁሉ ያህል ብቀጣ በአድርባይነቴ ባገኘሁት ጥቅም አጥበዋለሁ።ጉድ አንድ ሰሞን ነው። የኛ ሰው እንደሁ ማውራት ልማዱ ነው፤ ስለዚህ ያለውን ይበል&#8230; በዚህ ላይ ደግሞ የሚኮንነኝ ሰው የመኖሩን ያህል የሚደግፈኝ ሰውም አለ። ያሉትን ቢሉ ምን ያመጣሉ&#8230; ለዚያውስ ለየትኛው ህግ ነው? አንድ ሚሊዮን ዘግተህ ሁለት ዓመት ታስረህ ለምትወጣው ምን ችግር አለ። ሁለት ዓመት እንደሁነገ ናት.. እያሉ የሚያበረታቱ ሞልተዋል። ሌላው ጉዳይ አድርባይነት ‹‹ለራስ ሲቆርሱ አያሳንሱ›› በሚለው መርህ<br />
መሰረት የሚመራ በመሆኑ ጥሩ ውጤት የተገኘ ጊዜ ነጥቡን ለራስ እየወሰዱ መጥፎ ውጤት በተመዘገበና<br />
ጉዳት በደረሰ ጊዜ ኪሳራውን በሌሎች ላይ ማላከክ(Shifting the costs, blame and disadvantages toothers) የሚቻልበት አሰራር በመኖሩና ይህም በሰዎች አመለካከት ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ የሚያሳድር መሆኑ ነው። ሌላውን ተጠያቂ ማድረግ ጣትን በሌላው ላይመቀሰር ሁል ጊዜም ቀላል ስራ ነው። ለችግሮች ውጫዊ ምክንያት መስጠት ቀላል ነው። የአድርባይነትን ጠባይ ከሚያበረታቱ ነገሮች መካከል መነሳት ያለበት የሰውዬው ወይም የዚያ ቡድን የስልጣን መጠን ነው። ስልጣን ሲባል<br />
ሁሌም ለሙስና ይጋብዛል። ፍፁማዊ ስልጣን ደግሞ ለፍፁማዊ ሙስና አይን ላወጣ አድርባይነት ይዳርጋል።<br />
(All power corrupts, and absolute power corruptsabsolutely) ሰውዬው ከፍ ያለ ስልጣን ያለው ከሆነ ተቆጣጣሪ ስለሌለበት ያገኘውን መልካም አጋጣሚ ሁሉ ለግል ጥቅሙ የሚያውልበት ሰፊ እድል አለው። ስለዚህ አድርባይ ይሆናል። ለአድርባይነት መኖር በር የሚከፍተው<br />
ሌላኛው አመለካከት ደግሞ ‹‹እኔ ባላደርገው ሌላው ያደርገዋል&#8230; ስለዚህ ለምን እኔ አላደርገውም›› የሚለው አመለካከት ነው። ሌላው መጥቶ አጋጣሚውን ለራሱ ጥቅም የሚያውለው ከሆነ እኔስ እጄ ባለው አጋጣሚ ብጠቀም ሃጢአቴ እምኑላይ ነው ብሎ ያስባል።የበላይ አለቆቹንም ያያል። ሁሉም በአድርባይነት<br />
በሽታ የተለከፉ ይሆኑበታል። ያላቸውን ቤት፣ መሬት፣መኪና፣ ኢንቨስትመንት&#8230; የአኗኗር ሁኔታ ሲመለከት<br />
እኔስ ከማን አንሳለሁ ይላል።እነሱ ምን ተደረጉ ይላል። ለእነሱ ያልሰራ ህግ ለእሱም እንደማይሰራ ያምናል። ይገባበታል፤ በመጨረሻም ከእነሱ ጋር ተለቃቅሞ ይገባታል። እስከዚያው ድረስ ግን ጥቅም ነውና ይሟሟትበታል። አድርባዩ በበዛበት ድርጅት ውስጥ ሆኖ አድርባይ አልሆንም ማለት ይከብዳል።ሁሉም አብዶ ጨርቁን በጣለበት ሀገር ልብስ ለብሶ የሚሄድ ሰው ከተገኘ ዋናው እብድ የሚባለው እሱ<br />
ይሆናል። የአባትህ ቤት ሲዘረፍ አብረህ ዝረፍ የሚለውም የአድርባዮች መገለጫ ነው። ሰዎችን አድርባይ እንዲሆኑ የሚያደርጋቸው ሌላው ምክንያት የመረጃ፣ የእውቀት፣የግንዛቤ እጥረት ነው። ሰዎቹ በአድርባይ ጠባያቸው የተነሳ በፓርቲውና በመንግስት ስራ ላይ፣ በህዝብ ላይ፣ በሀገርላይ በመጨረሻም በራሳቸውና በቤተሰባቸው ህይወት ላይ የሚያደርሰውን ጉዳት ካልተረዱ አድርባይ መሆናቸው ሳይታለም የተፈታ ነው። አንዳንዶች በዚህ ረገድ ማግኘት ያለባቸውን መረጃና ግንዛቤ እንዳያገኙ ወይም የተዛባመረጃ ሆን ተብሎ እንዲያገኙ deliberate disinformation የሚደረጉበት ሁኔታ አለ። ሌሎች ደግሞ አድርባይነት<br />
በሚያስከትለው መዘዝ ላይ መረጃውና ግንዛቤው እያላቸው ሆን ብለው ራሳቸውን የሚያታልሉና በአጉል ድፍረት በልቼ (ተጠቅሜ) የመጣው ይምጣ ብለው የሚገቡ ፈጣጦች አሉ። ሲሾሙ ካልበሉ ሲሻሩ እንዳይቆጫቸው።ከዚህ በላይ ያነሳናቸው በአድርባዩ ሰውዬ በራሱ አማካይነት ተኮትኩተው ስለሚፋፉ የአድርባይነት ባህርያት ነው። ለእነዚህ ተከታታይ ስልጠና ያስፈልጋል።የአመለካከት ለውጥ፣ የግንዛቤ ዕድገት እንዲያመጡ ማድረግ ያስፈልጋል። ካደጉበት የ‹‹እንብላው›› ብሂል የሚወጡበትን እድል ጥልቅ በሆነ ስነአዕምሯዊ ስልጠናና ክትትል ከውስጣቸው ለመንቀል መስራት ያስፈልጋል። ማስተማር<br />
ያስፈልጋል። በሌላ በኩል ደግሞ ተቋማት ራሳቸው ሰዎችን ወደ አድርባይነት ለመገፋፋት የሚያመቻቹበት<br />
ሁኔታ አለ። አንዳንድ ድርጅቶች የአድርባይነት ጠባይ የማያስተናግድ በግልፅ የተቀመጠ ውልፍጥ የማያደርግ<br />
ህግና ደንብ አላቸው። ሰውዬው ምን ቢያደርግ ምን እንደሚደርስበት በግልጽ ተቀምጧል። ይህ ይነገረዋል።<br />
በጽሑፍም ይሰጠዋል። አድርባይ ሆነው የተገኙ ሰዎችንም የሚቆጠቁጥ ቅጣት ይጥሉባቸዋል። በስልጣን ላይ ሳሉባገኙት አጋጣሚ ያከማቹትን ሀብት እንዲያጡ፣ ለበርካታ ዓመታት በእስር እንዲቀጡ፣ ባዶ እጃቸውን እንደመጡባዶ እጃቸውን እንዲወጡ የሚያደርግ የፍትህ አሰራርም አላቸው። ሌሎች ድርጅቶች እንዲህ አይነት በግልፅ የተቀመጠ ህግ ስለሌላቸው የሚደርስባቸው ቅጣትም ከበሉት ገንዘብና ከተቀራመቱት ጥቅም አንፃር ሲታይ በእጅጉ አናሳ በመሆኑ ጓዶችን ሲያዩ እየተሽቆጠቆጡ፣ ዞርሲሉ ምላሳቸውን እያወጡ፣ በህዝብ ላይ እያላገጡ፣ ሰለሄመለሄ እየዋጡና ሙቅ ተበሪድ አማርጠው እየጨለጡ እንዲኖሩ እድል ይሰጣቸዋል። ከተቋማት አንፃር ሲታይ በርካታ ለአድርባይነት የሚገፋፉ አመቺ ሁኔታዎች አሉ።ሁሉንም ዘርዝረን አንችልም። አንድ ቦታ ላይ ማቆም አለብን። የሙስና የኪራይ ሰብሳቢነት የብልሹ አስተደደር<br />
እናቱም አባቱም አድርባይነት (Opportunism) ነው።ልንዋጋውና ልንታገለው ይገባል። ‹‹አድርባይነት››የተባለውን ጽንሰ ሀሳብ በግልጽና በጥልቀት በተለያዩ አደረጃጀቶቻችን አማካይነት ልንገነዘበው ይገባል። በእከክልኝ ልከክልህ በአባልነት ስም እየተሳሳቡ ጥሩ ጥሩውን ውጤት<br />
ወደራሳቸው እየሳቡና ጥፋት ሲገኝ በሌላው ላይ እያሳበቡ፣ምንም ሳይሰሩ እየደለቡ እንዲኖሩ መፍቀድ የለብንም።ይህን መታገል ደግሞ የኢትዮጵያ ህዝብ  ኃላፊነትብቻ ነው።ምክንያቱም ወያኔ‹‹አድርባይነት›› ሙያው ስለሆነ እንዲያውም በዋናነት የህብረተሰቡ የራሱ ኃላፊነት ነው። ከየት አመጣችሁ ብሎ መጠየቅ<br />
አለበት፤ ድምፁን መንፈግና በምርጫ ካረዱ መቅጣት አለበት ከደሃ ትከሻው ልናስፈነጥረውና አሽንቀጥሮ መጣል አለበት።ታዲያ ይኽሁላ የምናየው የገዥው መንግስት ባህሪያት አይደሉምን?ለማንኛውም መልካሙን ሁላ ለህዝባችን ይስጥልን!!</p>
<p>ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!!!</p>
<p>ከዘካሪያስ አሳዬ</p>
<p>&nbsp;</p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1758"     class="crp_title">አንሰማም!  ከዘካሪያስ አሳዬ</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1837"     class="crp_title">ቁም ነገር ተናጋሪ የሌለበት&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/180"     class="crp_title">የኢሕአዴግ ከፍተኛ የመንግስት&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1473"     class="crp_title">መልከ ጥፉ ነኝ ብዬ ስለማስብ ወንዶች&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2908"     class="crp_title">ሁለቱን በጣምራ/በአንድነት ማስኬድ&hellip;</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=83363</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>በጥቁር ገበያ የዶላር ዋጋ በሰላሳ ሳንቲም መቀነሱ አነጋጋሪ እየሆነ ነው</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3481</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3481#comments</comments>
		<pubDate>Wed, 22 May 2013 14:05:18 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3481</guid>
		<description><![CDATA[በሰንደቅ ጋዜጣ ሪፖርተር በአዲስ አበባ የሚገኙ የጥቁር ገበያ ባለድርሻዎች በከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት እና ታዋቂ ነጋዴዎች ከሙስና ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው በመታሰራቸው በተፈጠረ መደናገጥ መነሻ ከፍተኛ የሆነ ኪሳራ እያጋጠማቸው መሆኑን ገልፀው፣ የዶላር ምንዛሪ በታሪኩ የሰላሳ ሳንቲም ቅናሽ አሳይቷል። የከፍተኛ ባለስልጣናቱ በወንጀል የመጠርጠር ዜና ከመሰማቱ በፊት ሃያ ብር ከአርባ ሳንቲም የነበረው የዶላር ምንዛሪ ወደ ሃያ ብር ከአስር ሳንቲም [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/180">የኢሕአዴግ ከፍተኛ የመንግስት&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3472">የአያት አክሲዮን ማህበርና የስራ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3070">ወያኔ ባለስልጣናቱን አቶ መላኩ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1916">የለገደንቢ ወርቅ ሽያጭ ድራማ!!&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/709">ኃ/ማርያምን ጨምሮ ከፍተኛ&#8230;</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/dollar.jpg"><img src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/dollar-225x300.jpg" alt="dollar" width="225" height="300" class="alignleft size-medium wp-image-3482" /></a>በሰንደቅ ጋዜጣ ሪፖርተር</p>
<p>በአዲስ አበባ የሚገኙ የጥቁር ገበያ ባለድርሻዎች በከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት እና ታዋቂ ነጋዴዎች ከሙስና ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው በመታሰራቸው በተፈጠረ መደናገጥ መነሻ ከፍተኛ የሆነ ኪሳራ እያጋጠማቸው መሆኑን ገልፀው፣ የዶላር ምንዛሪ በታሪኩ የሰላሳ ሳንቲም ቅናሽ አሳይቷል።<br />
የከፍተኛ ባለስልጣናቱ በወንጀል የመጠርጠር ዜና ከመሰማቱ በፊት ሃያ ብር ከአርባ ሳንቲም የነበረው የዶላር ምንዛሪ ወደ ሃያ ብር ከአስር ሳንቲም በሳምንት ውስጥ ቀንሷል። በዚህ ቅናሽ ውስጥ አስደንጋጭ የሆነው ክስተት በማንኛውም አይነት ምንዛሪ መጠን ዶላር ወደላይ ሲጨምር ሆነ ሲቀንስ በሰላሳ ሳንቲም የልዩነት ምንዛሪ ውስጥ ወድቆ አለማወቁ መሆኑን ከስፍራው ያገኘነው መረጃዎች ያሳያሉ። በሙስና ከተጠረጠሩ ባለስልጣናት እና ነጋዴዎች ጋር በተያያዘ ይህ ልዩነት መፈጠሩ አብዛኛው የጥቁር ገበያ የዶላር ምንዛሪ ባለድርሻ አካላትን ማስደንገጡን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ወገኖች ጠቁመዋል።<br />
ባለፉት አራት ወራት ውስጥ ከፍተኛ የዶላር እጥረት በሀገሪቷ ሲከሰት የጥቁር ገበያ ባለድርሻ አካላት ከፍተኛ ተጠቃሚ መሆናቸውን ቢገለጽም፣ ከመንግስት እና ከግል ባንኮች ሰራተኞች የገጠማቸው ችግር ግን እጅግ ፈታኝ እንደነበር አስረድተዋል። ይህም ሲባል፣ ለአንድ የአሜሪካን ዶላር ከአንድ ብር እስከ አንድ ብር ከሃምሳ ሳንቲም የባንኩ ደንበኞች ክፍያ እየፈጸሙ ከፍተኛ መጠን ያለው የዶላር ምንዛሪ ከባንኮቹ ማግኘትን በአማራጭነት በመውሰዳቸው  ወደ እኛ ከመምጣት ባንኮንችን ተመራጭ ያደርጉ ነበር። ሆኖም ከፍተኛ መጠን ዶላር የማይፈልጉ ደንበኞች በወቅቱ ስለነበሯቸው ከፍተኛ ተጠቃሚ መሆናቸውንም አልሸሸጉም።<br />
በአሁን ሰዓት ከመንግስት ኪራይ ሰብሳቢ የተለያዩ ባለስልጣናት እና ነጋዴዎች ወደ እነሱ ይፈስ የነበረው የኢትዮጵያ ብር ለዶላር ምንዛሪ ከፍተኛ ጠቀሜታ የነበረው ከመሆኑ አንፃር አሁን የተፈጠረው ድንጋጤ በከፍተኛ ሁኔታ የጥቁር ገበያውን የዶላር ምንዛሪ ይጐዳዋል። የተፈጠረው ድንጋጤ ግለሰቦችን ሳይቀሩ ማሸማቀቁን ያነጋገርናቸው ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ወገኖች አረጋግጠዋል። በስፍራው የተገኙት መረጃዎችም የሚያሳዩት ከመንግስት ከፍተኛ ኪራይ ሰብሳቢ ባለስልጣናት ሰንሰለት ይፈስ የነበረው የኢትዮጵያ ብር ለጊዜ ተቀዛቅዟል። ሁኔታዎች በዚህ ከቀጠሉ የጥቁር ገበያው አደጋ ውስጥ መውደቁ አይቀርም የሚል ስጋት እንዳላቸው ገልፀዋል።<br />
ለምን የኢትዮጵያ ብር ወደ ጥቁር ገበያ ይላካል?<br />
በሙስና ውስጥ የተዘፈቁ የመንግስት ባለስልጣናት እና ተባባሪ የንግዱ ማሕበረሰብ አባላት ከሕግ አግባብ ውጪ የሚያገኙትን የኢትዮጵያ ብር በአዲስ አበባ ጥቁር ገበያ ውስጥ በዘረጉት ሰንሰለት ወደ አሜሪካ ዶላር ለውጠው ወደ ውጭ ሀገር እንዲወጣ በማድረግ ተጠቃሚ በመሆናቸው መሆኑን ያገኘነው መረጃ ያሳያል።<br />
በተለይ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት በዚህ መልኩ የሰበሰቡትን የአሜሪካ ዶላር በተሰጣቸው ያለመፈተሸ መብት በመጠቀም እና በገቢዎችና ጉምሩክ በዘረጉት የኪራይ ሰብሳቢ ሰንሰለቶች አማካይ ወደ ውጭ ይዘውት የሚወጡበት አሰራር ሊኖር እንደሚችል ግምታቸውን አስቀምጠዋል። የሰበሰቡትን የአሜሪካ ዶላር በሳምሶናዊት ቦርሳቸው ውስጥ በመጨመር እና ቦርሳውን ላይ ያለመፈተሽ መብት የሚያጎናጽፋቸውን ልጣፍ በመለጠፍ በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ በቀጥታ ዶላሩን ይዘው የሚወጡበት ዕድል ከፍተኛ በመሆኑ ሊጠቀሙበት ይችላሉ ሲሉ ግምታቸውን ተናግረዋል።<br />
በአስረጅነት ግምታቸውን ሲያስቀምጡ የገቢዎችና ጉምሩክ ምክትል ዋና ዳሬክተር የነበሩት አቶ ገብረዋህድ ወ/ጊዮርጊስ መኖሪያ ቤት የተገኘው 26ሺ የአሜሪካ ዶላር እና 19ሺ ዩሮ የአውሮፓ ሕብረት የመገበያያ ገንዘብ በዚህ መልኩ የተሰበሰቡ ሊሆን እንደሚችል ያላቸውን ግምት ገልፀዋል። አያይዘውም አንድ ግለሰብ ከ200 የአሜሪካ ዶለር ምንዛሪ ውጪ ይዞ መገኘት እንደማይችል በኢትዮጵያ ሕግ መስፈሩንም አስታውሰዋል። እንዲሁም በአቶ አስመላሽ ወ/ማሪያም መኖሪያ ቤት የተገኘውም አንድ ሚሊዮን የኢትዮጵያ ብር ወደ ዶላር ለመቀየር የተቀመጠ ገንዘብ ሊሆን እንደሚችል ከጥቁር ገበያ ያገኘነው ግምታዊ መረጃ ያሳያል።<br />
ይህን መሰል ተግባር መፈጸም ትርጉሙ ብዙ ሊሆን ይችላል። በተለይ አንድ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣን በሀገር ውስጥ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ እጥረት መኖሩ እያወቀ የኢትዮጵያን ብር በዶላር እየመነዘረ ወደ ውጭ ሀገር በማስወጣት ተግባር ላይ ከተሰማራ እንደሀገር ትልቅ በደል መሆኑን መገንዘብ ሮኬት ሳይንስ አይሆንም። በዚህ መልኩ የተሰማሩ የመንግስት ባለስልጣናት በወፍ በረር ሲታይ፣ ዶላር ማሸሽ ቢመስልም በተግባር ግን ሲመነዘር የኢትዮጵያ መንግስትን እና ሥርዓቱን ቀስ በቀስ እየሸራረፉ ሊጨርሱት መዘጋጀታቸውን የሚያሳይ ነው። የፓርቲ ሹመኞቹን የመንግስትን ስርዓት ለዘረጋው ገዥ ፓርቲ ቢተውም፣ ተግባራቸው ግን ሕገ መንግስቱን በጠራራ ፀሐይ እየበጣጠሱት ስለመሆኑ አስረጂ አያስፈልገውም።<br />
<strong>የገንዘብ ምንጩ ስትራቴጂ</strong><br />
እ.ኤ.አ. የሴፕቴምበር 11 ቀን 2001 የአሜሪካኑን የሽብር ጥቃት ተከትሎ ትንሹ ቡሽ ሴፕቴምበር 20 ቀን 2001 “WAR ON TERROR” በሚል መጠሪያ ዓለም ውስጥ የሚገኙ አሸባሪዎችን ለመደምሰስ ያስችላል በሚል አዲስ ስትራቴጂ ይዘው ብቅ አሉ። ቡሽ ቀጠል አድርገው በአሸባሪዎች ላይ የምንከፍተው ዘመቻ ‘የመስቀል ጦርነት’ ነው በማለት ለዓለም ሕዝብ በይፋ ተናገሩ።<br />
ቡሽ ብዙም ሩቅ ሳይጓዙ በአደባባይ “የመስቀል ጦርነት” የሚለውን ቃል ተገቢ አይደለም፤ ከእስልምና እምነት ተከታዮች ጋር አወዛጋቢ ፍቺ ያመጣል በማለት በይፋ ይቅርታ ጠይቀዋል። ጦርነቱን የምንጀምረው በአልቃይዳ እና በእሱ የሽብር መረብ ከተያያዙ አሸባሪዎች ጋር ነው ሲሉ አቋማቸውን በግልፅ አስቀመጡ። ዓለም ከአሜሪካ ጎን ቆመ። ቡሽም፣ ‘ወይ ከእኛ ወይም ከእነሱ’ ጋር መሆንን ምረጡ ብለው ለዓለም ዓቀፉ ሕብረተሰብ ጥሪ አቀረቡ። ዓለምም በወቅቱ በጐ ምላሽ ሰጣቸው። ጦርነቱ እንደቀጠለ ነው። ኦሳማ ቢላደን ግን ከአስር ዓመት በኋላ ተገድሏል።<br />
እዚህ ላይ ልብ ማለት ያለብን ቁምነገር፤ እንደቡሽ የመጀመሪያ አቀራረብ ቢሆን የተቀደሰውን የእስልምና እምነት ከሽብር ተግባር ጋር ጨፍልቆ ለማየት ያለመ ነበር። ሆኖም ቡሽ ፈጥነው አባባላቸው ስህተት መሆኑን አርመው በይፋ ይቅርታ ጠየቁ። ስለዚህም ነገሮች ለያይቶ ማየት እንጂ በአንድ ቅርጫት ውስጥ ወርውሮ አንድ መለያ መስጠት ተገቢ አለመሆኑ ከዚህ መረዳት ይቻላል።<br />
በተነፃፃሪነት ሲታይ ደግሞ ገቢዎችና ጉምሩክ በቀድሞ ከፍተኛ አመራሮቹ በኩል የኢትዮጵያ ነጋዴዎችን በተለይ እዚህ አዲስ አበባ ውስጥ የሚገኙትን ነጋዴዎች በግብር ስም ሁሉም ነጋዴ ግብር አጭበርባሪ ኪራይ ሰብሳቢ በማድረግ ሽብር “TERROR ON TAX” በነጋዴው ላይ ረጩ። ነጋዴውም ግብር መክፈሉን ሳይሆን ለኪራይ ሰብሳቢ ወይም ለግብር አጭበርባሪ ታፔላን ላለመጋለጥ በሚል ብቻ የገቢዎችና ጉምሩክ ከፍተኛ ሃላፊዎች ተገዢ መሆኑ አረጋገጠ። በመጨረሻም በተፈበረከው የሽበር ማዕቀፍ ውስጥ ነጋዴው ወደቀ። ፍርሃት፣ ስጋት መለያው ሆነ።<br />
ከዚህ በኋላ ከገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን የቀድሞ ከፍተኛ አመራሮቹ ጋር ተባብሮ መስራት የኪራይ ሰብሳቢዎች የህግ የበላይነትን ማረጋገጫ አድርጎ ተቀበለው። ለዚህ ማሳያ የሚሆነው መንግስት ከፍተኛውን የሙስና ወንጀል በራሱ መንገድ ደረሰበት እንጂ በአደባባይ በመውጣጥ ለማጋለጥ የደፈረ ታዋቂ ባለሃብት አንድም አልነበረም። በሕግ የማይነኩ በሚመስሉ የገቢዎችና የጉምሩክ ባለስልጣናት ጋር ሲራኮቱ የነበሩ ታዋቂ የከተማችን ባለሃብቶች ሕግ በራቸው ደጃፍ ሲመጣ ሌላ የፖለቲካ ዓላማ ያለው ተግባር እንጂ ሙስና አይመስለንም ሲሉ በአደባባይ በዘረጉት የኪራይ ሰብሳቢዎች የሙስና ሰንሰለት በመጠቀም ከተማውን እያሟሟቁ ይገኛሉ። እውነቱ ግን ሌላ ሆኖ ነው እየታየ ያለው።<br />
ከዚህ ጋር በተያያዘ በባሕርዳር በተደረገ የኢሕአዴግ 9ኛው ጉባኤ ላይ ከተጋበዙ ባለሃብቶች መካከል አንዱ የከተማችን ባለሃብት ለጉባኤው ያቀረበው ጥያቄ አጠቃላይ መንፈሱ ሲታይ “የኪራይ ሰብሳቢ” መሰረታዊ ይዘት በመቀየር ወደ ‘ሽብር’ መለወጡን አመላካች ነው። ባለሃብቱ ጉባኤውን የጠየቀው እንዲህ ሲል ነበር፣ “የኪራይ ሰብሳቢ ፍቺው በጣም የተለጠጠ ነው። በትክክልም ምን እንደሆነ እንኳን ለመረዳት አዳጋች ነው። በጅምላ ሁሉም ነጋዴ በገባበት ቢሮ ውስጥ ኪራይ ሰብሳቢ እየተባለ ይሸማቀቃል። እኔ እራሴ አሁን ኪራይ ሰብሳቢ በሚባለው ፍቺ ኪራይ ሰብሳቢ ልሁን፣ አልሁን ማረጋገጥ እንኳን አልችልም” ሲል በነጋዴው ላይ የተለቀቀውን ሽብር ለጉባኤው አስረድቷል።<br />
ቡሽም በጅምላ የሚካሄደው ጦርነት የመስቀል ጦርነት ነበር ያሉት። እሳቸው ግን በይፋ ይቅርታ ጠይቀዋል። የኢትዮጵያ መንግስትም ከንግዱ ማሕበረሰብ ጋር የበለጠ በመቀራረብ ለኪራይ ሰብሳቢዎች የተጋለጠውን የንግዱን ሕብረተሰብ ከሌላው ጤነኛ የንግዱ ሕብረተሰብ መለየት አለበት። ሁሉም ነጋዴ የኪራይ ሰብሳቢዎች መጠቀሚያም ተባባሪም ሊሆን ስለማይችል ነው። ንግድም ዓለምን የለወጠ የተከበረ ተግባር ከመሆኑ አንፃር መንግስት ከዚህ በፊትም ሲያደርገው እንደነበረው አሁንም አጋርነቱን ማሳየት ይጠበቅበታል። ስለዚህም መሰረታዊ የመንግስትን የገቢዎችና ጉምሩክ ፖሊሲን “በሽብር”፣ “በፍርሃት” ቆፈን ቀይረው ለራሳቸው ጥቅም ያደሩ የመንግስት ባለስልጣናት በፈጠሩት የተሳሳተ የኪራይ ሰብሳቢ ፍቺም በተቻለ ፍጥነት ለንግዱ ማሕበረሰብ መሰረታዊ ዕሳቤውን ማቅረብ ያስፈልጋል። በአንድ ቅርጫት ውስጥ የተቀመጠው የንግዱ ማሕበረሰብ ስምም ተገቢውን ስፍራ ሊያገኝ ይገባል። በመንግስትም በበኩሉ ኪራይ ሰብሳቢዎችን መያዙ ምርጫው ሳይሆን ግዴታው መሆኑን ግንዛቤ መውሰዱም ይጠቅማል። በተረፈ መንግስትና ጤናማው የንግዱ ማሕበረሰብ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጸች መሆናቸው የአደባባይ ሚስጥር በመሆኑ ብዙ ማለት   አይቻልም።¾(ሰንደቅ ጋዜጣ 8ኛ ዓመት ቁጥር 402 ረቡዕ ግንቦት 14/2005)</p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/180"     class="crp_title">የኢሕአዴግ ከፍተኛ የመንግስት&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3472"     class="crp_title">የአያት አክሲዮን ማህበርና የስራ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3070"     class="crp_title">ወያኔ ባለስልጣናቱን አቶ መላኩ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1916"     class="crp_title">የለገደንቢ ወርቅ ሽያጭ ድራማ!!&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/709"     class="crp_title">ኃ/ማርያምን ጨምሮ ከፍተኛ&hellip;</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=83359</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>(IMF) የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እድገት ወደ 5 ነጥብ 5 እንደሚወርድ ተነበየ</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3478</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3478#comments</comments>
		<pubDate>Wed, 22 May 2013 13:58:37 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3478</guid>
		<description><![CDATA[በፀጋው መላኩ አለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ሰሞኑን የየሀገራቱን የኢኮኖሚ አጠቃላይ ሁኔታ አስመልክቶ ባወጣው ሪፖርት እ.ኤ.አ በ2014 የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት ወደ 5 ነጥብ 5 የሚወርድ መሆኑን አስታወቀ። የገንዘብ ድርጅቱ በሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት ትንበያም ሆነ አፈፃጸም ከመንግስት ጋር የሚለያይ ሲሆን የኢትዮጵያን መንግስት የባለሁለት አሀዝ እድገትን ባለአንድ አሀዝ እድገት መሆኑን ሲገልፅ ቆይቷል። እ.ኤ.አ በ2011/12 የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ባለሁለት [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1274">“ዘጠኝ ቦላሌ…” ከይኸነው&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3137">ኢትዮጵያ በፍጥነት ወደኋላ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3164">የኢትዮጵያ ወጣቶች ብሄራዊ ንቅናቄ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2968">የኢትዮጵያ ብሔራዊ የሽግግር ም/ቤት&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/502">በወያኔ ኢትዮጵያ: ቆርጦ ቀጥል&#8230;</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/IMF-LOGO-KNN.gif"><img src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/IMF-LOGO-KNN-300x296.gif" alt="IMF LOGO KNN" width="300" height="296" class="alignleft size-medium wp-image-3479" /></a>በፀጋው መላኩ</p>
<p>አለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ሰሞኑን የየሀገራቱን የኢኮኖሚ አጠቃላይ ሁኔታ አስመልክቶ ባወጣው ሪፖርት እ.ኤ.አ በ2014 የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት ወደ 5 ነጥብ 5 የሚወርድ መሆኑን አስታወቀ።<br />
የገንዘብ ድርጅቱ በሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት ትንበያም ሆነ አፈፃጸም ከመንግስት ጋር የሚለያይ ሲሆን የኢትዮጵያን መንግስት የባለሁለት አሀዝ እድገትን ባለአንድ አሀዝ እድገት መሆኑን ሲገልፅ ቆይቷል። እ.ኤ.አ በ2011/12 የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ባለሁለት አሀዝ እድገትን የሚያስመዘግብ መሆኑን በገለፀበት ወቅት የገንዘብ ድርጅቱ በበኩሉ እድገቱ ሰባት በመቶ እንደሚሆን በትንበያው ያስቀመጠበት ሁኔታ ነበር።<br />
የገንዘብና የኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ባለፈው የካቲት ወር በለቀቀው መረጃ የኢኮኖሚ እድገቱን ቀመር ለመስራት ቀደም ሲል ሲጠቀምበት የነበረውን ብሄራዊ የአካውንቲግ ሲስተም በተሻሻለ የሂሳብ ስሌት እንዲቀየር መደረጉን በመግለፅ ብሔራዊውን የኢኮኖሚ እድገት መጠን ወደ 8 ነጥብ 5 በመቶ ያወረደበት ሁኔታ ነበር። በዚህም ወቅት የአለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት የ6 ነጥብ 5 በመቶ እድገትና የኢትዮጵያ መንግስት የእድገት ቀመር ቢቀራረብም ሰሞኑን የወጣው የገንዘብ ድርጅቱ የኢኮኖሚ እድገት ትንበያ ደግሞ የቀጣዩን ዓመት እድገት ወደ 5 ነጥብ 5 በመቶ አውርዶታል። የኢትዮጵያ መንግስት ለተከታታይ ዓመታት የባለሁለት አሀዝ የኢኮኖሚ እድገት ሲያስመዘገብ መቆየቱን ሲገልፅ የቆየ ሲሆን ከዚሁ ጋር በተያያዘም የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ነዳጅ አምራች ካልሆኑ ሀገራት መካከል ከፍተኛ እድገት እያስመዘገበ ነው ተብሎ ሲጠቀስ ቆይቷል።n</p>
<p><em>ምንጭ ሰንደቅ ጋዜጣ የሜይ 22 ዕትም</em></p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1274"     class="crp_title">“ዘጠኝ ቦላሌ…” ከይኸነው&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3137"     class="crp_title">ኢትዮጵያ በፍጥነት ወደኋላ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3164"     class="crp_title">የኢትዮጵያ ወጣቶች ብሄራዊ ንቅናቄ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2968"     class="crp_title">የኢትዮጵያ ብሔራዊ የሽግግር ም/ቤት&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/502"     class="crp_title">በወያኔ ኢትዮጵያ: ቆርጦ ቀጥል&hellip;</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=83360</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>የኢሕአዴግ የአ.አ ወጣቶች ማህበር 15 አመራሩን አገደ</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3476</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3476#comments</comments>
		<pubDate>Wed, 22 May 2013 13:56:26 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3476</guid>
		<description><![CDATA[የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር በጉባኤው ዋዜማ ላይ እየተወዛገበ ነው ‘‘የማህበሩ አመራር በኪራይ ሰብሳቢነት ተዘፍቋል’’ ከማህበሩ የታገዱ የም/ቤት አባላት ‘‘በኪራይ ሰብሳቢነት የተዘፈቁት የታገዱት አመራሮች ናቸው’’ የማህበሩ አመራር በዘሪሁን ሙሉጌታ የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ከግንቦት 25 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ ጠቅላላ ጉባኤውን በማካሄድ የአመራር ምርጫ ያካሂዳል። ማህበሩ ጉባኤ ከማካሄዱ በፊት ወደ 15 የማህበሩ ም/ቤት አመራር አባላትን ማገዱን [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/358">ባለራዕይ ወጣቶች ማህበር በመንግስት</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/16">ሰበር ዜና -የባለራዕይ ወጣቶች&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2790">የሠራተኛ ማህበሩ ሊቀመንበርና&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1034">በአዲስ አበባ አምስቱም መውጫዎች&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2425">የሰንደቅ ጋዜጣ ገጽ ሶስት፣ የአዲስ&#8230;</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<h2 style="text-align: center;"><span style="color: #000000;">የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር በጉባኤው</span><br />
<span style="color: #000000;"> ዋዜማ ላይ እየተወዛገበ ነው</span></h2>
<h2 style="text-align: center;">‘‘የማህበሩ አመራር በኪራይ ሰብሳቢነት ተዘፍቋል’’<br />
ከማህበሩ የታገዱ የም/ቤት አባላት<br />
‘‘በኪራይ ሰብሳቢነት የተዘፈቁት የታገዱት አመራሮች ናቸው’’<br />
የማህበሩ አመራር</h2>
<p>በዘሪሁን ሙሉጌታ</p>
<p><div id="attachment_1035" class="wp-caption alignleft" style="width: 310px"><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/03/Addis-Ababa.jpg"><img src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/03/Addis-Ababa-300x200.jpg" alt="የአዲስ አበባ ከተማ ገጽታ" width="300" height="200" class="size-medium wp-image-1035" /></a><p class="wp-caption-text">የአዲስ አበባ ከተማ ገጽታ</p></div>የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ከግንቦት 25 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ ጠቅላላ ጉባኤውን በማካሄድ የአመራር ምርጫ ያካሂዳል። ማህበሩ ጉባኤ ከማካሄዱ በፊት ወደ 15 የማህበሩ ም/ቤት አመራር አባላትን ማገዱን ተከትሎ ከታገዱት አባላት ጋር ውዝግብ ውስጥ ገብቷል።<br />
70 አባላት ካሉት የማህበሩ ም/ቤት መካከል ወደ 23 የሚሆኑ አባላት አለአግባብ ‘‘ተባረናል’’ ሲሉ ለሰንደቅ ጋዜጣ ገልፀዋል። በአሁኑ ወቅት ማህበሩን እየመራ ያለው የአመራር አካል በኪራይ ሰብሳቢነት መዘፈቁንም አመልክተዋል። በቅርቡ ለሚካሄደው ጠቅላላ ጉባኤም 1 ነጥብ 3 ሚሊዮን የተጋነነ ገንዘብ መመደቡንም ገልፀዋል። የተመደበውም ገንዘብ በአብዛኛው ‘‘ለተሃድሶ’’ ወይም ለመዝናናት የሚውል ከመሆኑም በላይ የገንዘብ አሰባሰብ ሂደቱም ግልፅነት የጎደለው እንደሆነም ተናግረዋል።<br />
ማህበሩ ጉባኤውን ለማካሄድ የጠየቀውን 1 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር ከአዲስ አበባ አስሩም ክፍለ ከተሞች፣ ከአዲስ አበባ ገቢዎችና መንገዶች ባለስልጣን እና ከሌሎች መንግስታዊ ተቋማት የሚሰበሰብ እንደሆነም አመልክተዋል።<br />
በማህበሩ አመራር አለአግባብ ታግደናል የሚሉት እነዚሁ ወጣት አመራሮች በተጨማሪ እንደገለፁት የጉባኤው መሪ ቃል (ሞቶ) ‘‘የወጣቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የመለስን ራዕይ እናሳካለን’’ የሚል መሆኑ ማህበሩ ነፃነት የሌለውና በኢህአዴግ ካድሬዎች የሚሽከረከር መሆኑን ማረጋገጫ ነው ብለዋል።<br />
‘‘አለአግባብ ተባረናል’’ የሚሉት ወጣት አመራሮች የተባረሩበት ምክንያት በማህበሩ አካባቢ ኪራይ ሰብሳቢነት መስፈኑን በማጋለጣቸው፣ አንዳንዶቹ ደግሞ በሕገ-መንግስታዊ መብታቸው መሠረት በሌላ ነፃ ማህበር ውስጥ አባል በመሆናቸው ምክንያት መሆኑን ገልፀዋል።<br />
ማህበሩ ለስሙ 80 ሺህ አባላት እንዳሉት ቢነገርም በትክክል የማህበሩን ስራ የሚያከናውኑ ከሁለት ሺህ እንደማይበልጡ ነው ቅሬታ አቅራቢዎቹ የገለፁት። የማህበሩ ፕሬዝዳንት ወጣት ዮሐንስ ጣሰው ማህበሩን ውጤታማ ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት ቢያደርግም በኢህአዴግ ካድሬዎች ተፅዕኖ እንደሚደረግበትም ቅሬታ አቅራቢዎቹ አያይዘው ገልፀዋል።<br />
በማህበሩ አመራር ላይ በተነሱ ቅሬታዎች ላይ የማህበሩ ፕሬዝዳንት ወጣት ዮሃንስን ለማነጋገር ተደጋጋሚ ሙከራ ያደረግን ቢሆንም ከስራ መብዛት ጋር በተያያዘ ልናገኘው አልቻልንም። ሆኖም የማህበሩ ምክትል ፕሬዝዳንት ወጣት መድሃኔ መለሰ ለሰንደቅ ጋዜጣ እንደገለፀው ከአንድ ሳምንት በፊት ስብሰባ ተካሂዶ እንደነበር እና 15 የማህበሩ የም/ቤት አባላት ለጊዜው መታገዳቸውን አምኗል። በማህበሩ ሕገ-ደንብ መሠረት የአመራር አባላት የሚባረሩት በጠቅላላ ጉባኤው መሠረት እንደሆነ አስታውቋል። 15ቱ የአመራር አባላት የታገዱት ከክፍለ ከተማ በመጣ ግምገማ መሠረት እየሰሩ አለመሆኑ በተጨባጭ ማስረጃ በመረጋገጡ ከክፍለ ከተሞች ለአስፈፃሚው በመጣ የግምገማ ሪፖርት መሆኑን አመልክቷል። ሦስቱ የአመራር አባላት ደግሞ በገዛ ፈቃዳቸው ከምክር ቤቱ እራሳቸውን በማግለል ሲሆን፤ የቀሩት አምስቱ ደግሞ ከሀገር በመውጣታቸው እንደሆነም ገልጿል።<br />
ለጉባኤው የወጣው የገንዘብ መጠን በተመለከተ ወጣት መድሃኔ ተጠይቆ ትክክለኛው የገንዘብ መጠን 1 ሚሊዮን ሦስት መቶ ሺህ ሳይሆን አንድ ሚሊዮን ሦስት መቶ ብር መሆኑን፤ ከዝግጅት ጋር በተያያዘም ጠቅላላ ጉባኤው መካሄድ ከነበረበት ጊዜ መዘግየቱን በመጪው ግንቦት 25 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ የወረዳ ም/ቤት ጉባኤዎች ከተካሄዱ በኋላ በሳምንቱ ደግሞ በከተማ ደረጃ የማህበሩ ጠቅላላ ጉባኤ እንደሚካሄም አመልክቷል።<br />
ለጉባኤው ወጪ የተደረገው የገንዘብ መጠን በ116 ወረዳዎች ውስጥ ለሚካሄድ ጉባኤ በመሆኑ ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቅ መሆኑን የጠቀሰው ወጣት መድሃኔ በ116 ወረዳዎች ጠቅላላ ጉባኤ ለማካሄድ የተጠቀሰው ገንዘብ ቢያንስ እንጂ አይበዛም ብሏል።<br />
ማህበሩ በመተዳደሪያ ደንቡ የገንዘብ ምንጩ በመንግስትና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የሚደገፉ በመሆኑ ከመንግስታዊ አካላት በአይነት መደገፉ ወይም ስፖንሰር መደረጉ ችግር የለውም፤ የሚለው ወጣት መድሃኔ ገንዘቡ ለተሃድሶ (ለመዝናናት) ይውላል መባሉ በተጨባጭ እቅድ ላይ የሌለ ነገር ነው ሲል አስተባብሏል። ከመንግስት አካላት በገንዘብ ከሚሰጠው ድጋፍ በበለጠ በቲሸርት፣ በኮፍያና በአዳራሽ መልክ የሚደረጉ ድጋፎች እንጂ በካሽ አለመሆኑን አያይዞ ገልጿል።<br />
የማህበሩ የአባላት ብዛት በተመለከተ ቀደም ሲል 80 ሺህ አባላት አሉት ይባል እንደነበር የጠቀሰው ወጣት መድሃኔ፤ ነገር ግን በተደረገው የማጥራት ስራ በአሁኑ ወቅት በማህበሩ እንቅስቃሴ ውስጥ በንቃት የሚሳተፉ የአባላት ቁጥር 32ሺህ መሆኑንም አስረድቷል።<br />
የጉባኤው መሪ ቃል በተመለከተ ‘‘በመለስ ሌጋሲ የወጣቱን ተጠቃሚነት እናረጋግጣለን’’ መባሉ ከማህበሩ ነፃነት አንፃር ስላለው ፋይዳም ተጠይቆ፤ በቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ አስተዳደር ወቅት ወጣቶችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ፓኬጆች በመቀረፃቸው፣ በህገ-መንግስቱ ወጣቱ በነፃ በመደራጀቱና ወጣቱ በአነስተኛና ጥቃቅን ተደራጅተው ተጠቃሚ መሆናቸውን መነሻ በማድረግ የተወሰነ ነው ሲል መልሷል።<br />
በማህበሩ ስም ከሚከራዩ ተቋማት ገቢ ጋር በተያያዘ ምዝበራ ስለመኖሩም ወጣት መድሃኔ ተጠይቆ ከአመራሩ ይልቅ በም/ቤቱ ከታገዱ ወጣቶች ላይ ይሄ ችግር መኖሩን ከታገዱበት ሦስት ምክንያቶች መካከል የኪራይ ሰብሳቢነት ችግር አንዱ እንደሆነ በመግለፅ በአንፃሩ ማህበሩ አመራሩን የሚቆጣጠርበት ስርዓት መቀየሱን፤ በአሁኑ ሰዓት ሦስት የአመራር አባላት ከኪራይ ሰብሳቢነት ችግር ጋር በተያያዘ በፍርድ ቤት ተከሰው ጉዳያቸው በሕግ መያዙን በመጥቀስ አመራሩ ኪራይ ሰብሳቢነት እየተዋጋ መሆኑን አመልክቷል።<br />
የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር በ1990 ዓ.ም የተቋቋመ ማህበር መሆኑ ይታወቃል።n</p>
<p>(ምንጭ ሰንደቅ ጋዜጣ የዛሬ ሜይ 22 ዕትም)</p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/358"     class="crp_title">ባለራዕይ ወጣቶች ማህበር በመንግስት</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/16"     class="crp_title">ሰበር ዜና -የባለራዕይ ወጣቶች&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2790"     class="crp_title">የሠራተኛ ማህበሩ ሊቀመንበርና&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1034"     class="crp_title">በአዲስ አበባ አምስቱም መውጫዎች&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2425"     class="crp_title">የሰንደቅ ጋዜጣ ገጽ ሶስት፣ የአዲስ&hellip;</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=83361</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>የአያት አክሲዮን ማህበርና የስራ አመራሮቹ ላይ በእስርና ከፍተኛ በገንዘብ ተቀጡ</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3472</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3472#comments</comments>
		<pubDate>Wed, 22 May 2013 13:50:05 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3472</guid>
		<description><![CDATA[(ፍኖተ ነፃነት) የአያት አክሲዮን ማህበር፣ በስራአስኪያጁ አቶ አያሌው ተሰማና በሌሎች ማህበሩ አመራሮች ላይ ላይ በገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን በተመሠረቱባቸው  ክሶች ጥፋተኛ በመባላቸው ዛሬ በልደታ ፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 8ኛ ወንጀል ችሎት በእስርና ከፍተኛ በገንዘብ እንደተቀጡ የፍኖተ ነፃነት የፍርድ ቤት አስታወቀ፡፡ የፍኖተ ነፃነትየፍርድ ቤት ዘጋቢ እንዳስታወቀው የልደታ ፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 8ኛ ወንጀል ችሎት ባስተላለፈው ውሳኔ መሰረት [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/16">ሰበር ዜና -የባለራዕይ ወጣቶች&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3087">የታሰሩት ባለስልጣናት እና ነጋዴዎች</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2790">የሠራተኛ ማህበሩ ሊቀመንበርና&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3481">በጥቁር ገበያ የዶላር ዋጋ በሰላሳ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1942">ባርሴሎናና ሪያል ማድሪድ&#8230;</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/ayat-real-estate.jpg"><img src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/ayat-real-estate.jpg" alt="ayat real estate" width="300" height="300" class="alignleft size-full wp-image-3473" /></a>(ፍኖተ ነፃነት) የአያት አክሲዮን ማህበር፣ በስራአስኪያጁ አቶ አያሌው ተሰማና በሌሎች ማህበሩ አመራሮች ላይ ላይ በገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን በተመሠረቱባቸው  ክሶች ጥፋተኛ በመባላቸው ዛሬ በልደታ ፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 8ኛ ወንጀል ችሎት በእስርና ከፍተኛ በገንዘብ እንደተቀጡ የፍኖተ ነፃነት የፍርድ ቤት አስታወቀ፡፡</p>
<p>የፍኖተ ነፃነትየፍርድ ቤት ዘጋቢ እንዳስታወቀው የልደታ ፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 8ኛ ወንጀል ችሎት ባስተላለፈው ውሳኔ መሰረት አያት አክሲዮን ማኅበር 90 ሚሊዮን ብር፣ የአያት አክሲዮን የማኅበሩ መስራችና ከፍተኛ ባለድርሻ እንዲሁም ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ አያሌው ተሰማ 12 ዓመት እስራት እና 3.2 ሚሊዮን ብር ቅጣት፣ ዶ/ር መሐሪ መኮንን 12 ዓመት ፅኑ እስራት እና 436,646 ብር ቅጣት፣ አቶ ጌታቸው አጎናፍር 10 ዓመት ፅኑ እስራት እና 411,969.60 ብር ቅጣት ተወስኖባቸዋል፡፡  የአያት አክሲዮን የማኅበሩ መስራችና ከፍተኛ ባለድርሻ እንዲሁም ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ አያሌው ተሰማ እና ሌሎች ታዋቂ ነጋዴዎች ላይ ክስ በማቀናበርና በየሚዲያው ማብራሪያ ሲሰጡ የነበሩት የገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ምክትል ዳይሬክተር አቶገብረዋህድ ገ/ጊዮርጊስ በሙስና ተጠርጥረው በቅርቡ መታሰራቸው ያስታውቃል፡፡</p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/16"     class="crp_title">ሰበር ዜና -የባለራዕይ ወጣቶች&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3087"     class="crp_title">የታሰሩት ባለስልጣናት እና ነጋዴዎች</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2790"     class="crp_title">የሠራተኛ ማህበሩ ሊቀመንበርና&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3481"     class="crp_title">በጥቁር ገበያ የዶላር ዋጋ በሰላሳ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1942"     class="crp_title">ባርሴሎናና ሪያል ማድሪድ&hellip;</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=83362</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>ባህርዳር ከተማ የጅንአድ እየተቃጠለ ነው</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3461</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3461#comments</comments>
		<pubDate>Tue, 21 May 2013 19:10:48 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3461</guid>
		<description><![CDATA[የቪድዮ ምስል ከፋይል

Related Posts:ቦንድ ለመሸጥ ሳዑዲ የገባው ወያኔ&#8230;‹‹313 ሚሊዮኑ ለልማት!›› በሚል መሪ&#8230;የኮሜዲያን አዜብ መስፍን አዲስ&#8230;&#8220;ታ]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p>የቪድዮ ምስል ከፋይል<br />
<iframe width="500" height="380" src="http://www.youtube.com/embed/bdBY_11otbY" frameborder="0" allowfullscreen></iframe></p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/13"     class="crp_title">ቦንድ ለመሸጥ ሳዑዲ የገባው ወያኔ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2468"     class="crp_title">‹‹313 ሚሊዮኑ ለልማት!›› በሚል መሪ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1299"     class="crp_title">የኮሜዲያን አዜብ መስፍን አዲስ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/393"     class="crp_title">&#8220;ታምሜ ተኝቼ&#8221; &#8211; ታምራት&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2804"     class="crp_title">ጽናት &#8211; ሁሉም ሊያየው የሚገባ&hellip;</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=83315</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>በላተኛው አባ-መላ  ከያሬድ አይቼህ</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3454</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3454#comments</comments>
		<pubDate>Tue, 21 May 2013 16:21:30 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3454</guid>
		<description><![CDATA[ከያሬድ አይቼህ ፤ ሜይ 20፥2013 የፓልቷኩ አባ-መላ ሰሞኑን ገኗል። መግነኑ አልከፋኝም … ይግነን … ለሁሉም ጊዜ አለውና። ግን አባ-መላን ብዙ ጊዜ አዳምጨዋለሁና የአባ-መላን ነገር መዳሰስ ፈለኩ። ሰሞኑን አባ-መላ ገዢውን ፓርቲ መተቸት ጀምሯል። ይህንን የሰሙ የተቃዋሚ ፓርቲ ደጋፊዎች በጣም ፈንጥዘዋል ፡ እኔ አልፈነጠዝኩም። ለምን? አባ-መላ የሚናገረውን ነገር በየሳምንቱ ፡ አንዳንዴ አልፎ አልፎም ቢሆን ፡ አዳምጨዋለሁ። አባ-መላ [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3398">በላተኛው አባ-መላ</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1159">በኢህአዴግ መተካካት በነመራ ዲንሣ</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/541">ህወሃት ሊወድቅ ነው (ለነጻነታችን&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2468">‹‹313 ሚሊዮኑ ለልማት!›› በሚል መሪ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1299">የኮሜዲያን አዜብ መስፍን አዲስ&#8230;</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p style="text-align: left;" align="center">ከያሬድ አይቼህ ፤ ሜይ 20፥2013</p>
<div id="attachment_3455" class="wp-caption alignleft" style="width: 310px"><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/Aba-Mela.jpg"><img class="size-medium wp-image-3455" alt="Aba Mela" src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/Aba-Mela-300x240.jpg" width="300" height="240" /></a><p class="wp-caption-text">Ato Birhanu Damte (Aba mela)</p></div>
<p>የፓልቷኩ አባ-መላ ሰሞኑን ገኗል። መግነኑ አልከፋኝም … ይግነን … ለሁሉም ጊዜ አለውና። ግን አባ-መላን ብዙ ጊዜ አዳምጨዋለሁና የአባ-መላን ነገር መዳሰስ ፈለኩ። ሰሞኑን አባ-መላ ገዢውን ፓርቲ መተቸት ጀምሯል። ይህንን የሰሙ የተቃዋሚ ፓርቲ ደጋፊዎች በጣም ፈንጥዘዋል ፡ እኔ አልፈነጠዝኩም። ለምን?</p>
<p>አባ-መላ የሚናገረውን ነገር በየሳምንቱ ፡ አንዳንዴ አልፎ አልፎም ቢሆን ፡ አዳምጨዋለሁ። አባ-መላ የሚያረገውን የሚያረግው ለአንድ አበይት ምክንያት ብቻ ነው፦ የግል ጥቅም። አባ-መላ ሌላ ንዑስ ምክንያት የለውም። የሚያደርገው ፡ የሚናገረው ፡ የሚተነፍሰው ፡ የሚስቀው ፡ የሚያለቅሰው … ወዘተ … ለግል ጥቅሙ ነው (ለግል ጥቅሙ መቆሙ መጥፎ ነው ማለቴ አይደለም ፡ ያ ምርጫው ነው)።</p>
<p>በ2008 እ.አ.አ. አባ-መላ ክፍል ውስጥ አስተዳዳሪ የነበረ ሰው (“addis_ababa_1”? በሚል መጠሪያ ስም ሚሳተፍ) ክፍሉ ውስጥ በተነሳ ቅራኔ ምክንያት የክፍሉን ሚስጥር በተቃዋሚ ክፍሎች ውስጥ ገብቶ ሲናገር ሰምቻለው። ከተናገረው ሚስጥር አንዱ ፡ ቃል በቃል ባላስታውስም ፡ አባ-መላ ከሚድሯክ ወይም ከሼህ መሃመድ አልሙዲ በአመት $50,000 ዶላር እንደሚከፈለው ነው። ይሄ ነገር የአባ-መላን ባህሪ እና የፓለቲካ ፕሮፓጋንዳ ትኩሳት ለመረዳት ወሳኝ መረጃ ሆኖ አገኝቼዋለሁ።</p>
<p>አባ-መላ የሚያደርገው ነገር ሁሉ ከሚድሯክ ጥቅም ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያለው ነው ብዬ አምናለሁ። የሚድሯክ ጥቅም ሲከበር ፡ አባ-መላ ለኢህአዴግ እስክስታ ይወርዳል። የድርጅቱ ጥቅም ስጋት ላይ የወደቀ ሲመስል ፡ አባ-መላ ደረቱን ይመታል።</p>
<p>አባ-መላ የኢህአዴግ ደጋፊ ሆኖ አያቅም። አባ-መላ የሚድሯክን ገጽታ የሚያሽሞነሙን ፡ የደርግ ስርዓት ያፈራው ፡ አንደበተ ምላጭ ፡ የሚያደርገውን የሚያቅ ፡ ፕሮፓጋንዲስት ነው።</p>
<p>ታዲያ ምነው ሰሞኑን የፓልቷክ ተቃዋሚ ክፍሎች ባዶ ሆነው የሲቪሊቲ ክፍል ሞልቶ የፈሰሰው? ተቃዋሚ ባካችሁን በአባ-መላ አትበሉ። አባ-መላ ሚያደረገው ሁሉ ለአገራዊ ጥቅም ብሎ ሳይሆን ለግል ጥቅሙና ለሚያገለግለው ድርጅት ጥቅም ብቻ ብሎ መሆኑን እንገንዘብ።</p>
<p>ሚድሯክ ለብዙ ኢትዮጵያውያን የስራ እድል የከፈተና ፡ አያሌ ካፒታል ያፈሰሰ ድርጅት በመሆኑ ድርጅታዊ ገጽታውንና ጥቅሙን መንከባከቡ ተገቢና የሚጠበቅ ነው። ሆኖም ግን የገዢው ፓርቲ ተቃዋሚዎች በሚድሯክ እና በኢህአዴግ መካከል ሆነን ልንፈጭ ነውና ፡ በአባ-መላ የፓለቲካ ስልት እንዳንበላ ጠንቀቅ እንበል።</p>
<p>አባ-መላንም ሆነ ሌሎች ገዢው ፓርቲን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የሚደግፉ ሰዎችን ተስገብግበን ወደ ተቃዋሚው ጎራ መጨመር የለብንም። በጊዜ ውስጥ ሊፈተኑ ፡ አመኔታችንን ቀስበቀስ ሊያገኙ ይገባል እንጂ ተንሰፍስፈን መርዝ ይሁን መድሃኒት እንደያዙ ሳናቅ አንቀበላቸው።</p>
<p>ወቅቱ የህወሃት/ኢህአዴግ መጨረሻ ወቅት ነውና የሚደናበሩትን የገዢውን ፓርቲ በላተኞች ለጥቅማችን እንጠቀምባቸው እንጂ እነሱ አይጠቀሙበን።</p>
<p>_ _ _ _ _ _</p>
<p>ጸሃፊውን ለማበረታታት ፡ ለመውቀስና ለማስፈራራት በዚህ ይጻፉ፦ yared_to_the_point@yahoo.com</p>
<p><iframe width="560" height="315" src="http://www.youtube.com/embed/rKCWlu-BeWM" frameborder="0" allowfullscreen></iframe></p>
<p>&nbsp;</p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3398"     class="crp_title">በላተኛው አባ-መላ</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1159"     class="crp_title">በኢህአዴግ መተካካት በነመራ ዲንሣ</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/541"     class="crp_title">ህወሃት ሊወድቅ ነው (ለነጻነታችን&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2468"     class="crp_title">‹‹313 ሚሊዮኑ ለልማት!›› በሚል መሪ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1299"     class="crp_title">የኮሜዲያን አዜብ መስፍን አዲስ&hellip;</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=83277</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>ሰውየው (የመጨረሻ ክፍል) ከይገርማል ታሪኩ</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3440</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3440#comments</comments>
		<pubDate>Tue, 21 May 2013 15:18:16 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3440</guid>
		<description><![CDATA[ከይገርማል ታሪኩ  (የመጨረሻ ክፍል)  የአባጃሌው ልጅ ሀይሌ ከፊታቸው ጥንቃቄ የሚጠይቅ ስራ ይጠብቃቸዋል:: መዐሕድ ድርጅቴ ነው: ቤቴ ነው ብሎ የተቀበለውን አባል አሳምኖ ወደመኢአድ ማሰባሰብ ቀላል ነገር አይሆንም:: ወያኔ መራሹ መንግስት የትጥቅ ትግል ለማካሄድ ሲንቀሳቀሱ ይዣቸዋለሁ ያላቸው በርካታ ሰዎች ከፕሮፌሰር አስራት ወ/የስ ጋር በእስር ላይ ናቸው:: የእስረኞች ቤተሰቦች: ዘመድ አዝማዶች እንዲሁም መላው አባላት መስዋእትነት የተከፈለበት ድርጅት ሲፈርስ [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3281">ሰውየው (ክፍልሁለት) ከይገርማል&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3229">በምርጫ 97 የትዝታ ማህደር ውስጥ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2627">ዶ/ር መረራ ጉዲና እና አቶ ገብሩ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2923">&#8220;&#8216;አማራ ኬላ&#8217; የሚባሉ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/998"> &#8211; በልጅግ ዓሊ</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p style="text-align: left;" align="center">
<p>ከይገርማል ታሪኩ</p>
<p style="text-align: left;" align="center"><span style="text-decoration: underline;"> (የመጨረሻ ክፍል)</span><span style="text-decoration: underline;"> </span></p>
<p><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/03/Pen-4.jpg"><img class="alignleft size-thumbnail wp-image-1278" alt="Pen-4" src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/03/Pen-4-150x150.jpg" width="150" height="150" /></a>የአባጃሌው ልጅ ሀይሌ ከፊታቸው ጥንቃቄ የሚጠይቅ ስራ ይጠብቃቸዋል:: መዐሕድ ድርጅቴ ነው: ቤቴ ነው ብሎ የተቀበለውን አባል አሳምኖ ወደመኢአድ ማሰባሰብ ቀላል ነገር አይሆንም:: ወያኔ መራሹ መንግስት የትጥቅ ትግል ለማካሄድ ሲንቀሳቀሱ ይዣቸዋለሁ ያላቸው በርካታ ሰዎች ከፕሮፌሰር አስራት ወ/የስ ጋር በእስር ላይ ናቸው:: የእስረኞች ቤተሰቦች: ዘመድ አዝማዶች እንዲሁም መላው አባላት መስዋእትነት የተከፈለበት ድርጅት ሲፈርስ ምላሻቸው ምን ሊሆን እንደሚችል አይታወቅም:: ጊዜ ወርቅ ነው:: ማንኛውም ነገር በትክክለኛው ወቅት ያለእንከን መፈጸም ይኖርበታል:: የወያኔና አንጋቾቹ የፈጠራ ወሬ የየዋሆችን ልብ ሊፈትን ይችላል:: የፖለቲካ ፓርቲወችም ቢሆኑ እንዳሸን ነው የሚፈሉት:: ጊዜ ከተሰጠ አይደለም የተራው አባል የየወረዳ አስተባባሪወችንም በነበሩበት ማግኘት ይከብዳል:: ጥቃትን ለመመከት ሁሉም የየመሰለውን አማራጭ ሊከተል ይችላል:: መፍጠን ይኖርባቸዋል::</p>
<p>ጠ/ ሚኒስትሩ &#8220;ለስልጣን የበቃነው ጀርባችንን በእሳት አስገርፈን ነው&#8221; ብለው ያሉት ሀሰትነት የለውም:: ደርግ ከስልጣን የወደቀው እንዲህ በቀላሉ አልነበረም:: የትግራይ ወጣቶችን ጨምሮ መላው ኢትዮጵያዊ ደርግን ለመጣል እልህ አስጨራሽ ፍልሚያ አድርጓል:: በትግሉ ወቅት ይህ ነው የማይባል ንብረት ወድሟል:: ከሁሉም በላይ የበርካታ ሰዎች ህይወት ጠፍቷል:: ነገር ግን ደርግን ለመጣል በተደረገው ትንቅንቅ መስዋእት የሆኑት ኢትዮጵያውያን ለትግል የተነሱት ወያኔ የሚያዝ የሚናዝዝበትን አምባገነን ስርአት ለመመስረት አልነበረም- የአምባገነኑን ስርአት አፍርሰው ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶችን በሚያስከብር ስርአት ለመተካት እንጅ:: ወያኔ ግን የህዝብ ልጆች በመስዋእትነታቸው ያስገኙትን ድል ለራሱ በሚመች መልኩ አዘጋጀው:: ለተሰውት የህዝብ ልጆች ካሳ የሚገባኝ እኔ ነኝ ብሎ ድርቅ አለ:: በርግጥ ወያኔ ደረቅ ብቻም አይደለም- ብልጥም ነው::</p>
<p>የተቃዋሚ ፓርቲዎች እንዲሞቱም ሆነ እንዲጠነክሩ አይፈለግም:: ተቀናቃኝ ፓርቲወች አሉ መባሉ የገዥውን ፓርቲ መልካም ገጽታ በአንድ ደረጃ ከፍ ያደርገዋል:: የዴሞክራሲ ስርአት አንዱ መገለጫ ከገዥው ፓርቲ ሌላ የተደራጁ ተፎካካሪ ፓርቲወች መኖር ነው:: ታማኝ የሆኑ ፓርቲዎች ከመንግስት ልዩ ድጋፍ ሊደረግላቸው ይችላል:: ታማኝ ፓርቲዎች ታማኝ ተቃዋሚ ያላቸው ናቸው:: ታማኝ ተቃዋሚ በሆነ ባልሆነው መንግስትን አይጐንጥም: የሰጡትን በጸጋ ይቀበላል:: ሕዝብንና መንግስትን ለመነጠል አይሞክርም:: በዚህ ስሌት መሰረት መኢአድም ሆነ ሌላ ፓርቲ ቢመሰረት ችግር የለውም:: ችግር የሚሆነው ፓርቲዎች ገንነው መውጣት ከጀመሩ ነው:: ሕዝብ የሚደግፋቸው ፓርቲዎች ቀይ መስመርን የተሻገሩ ናቸው:: ቀይ መስመር ማለት ኢሕአዴግ ለተቃዋሚዎች ያስቀመጠው የመንቀሳቀሻ ዳራ ነው:: ቀይ መስመሩን አይደለም ማለፍ መንካት ቀይ ካርድ ያሰጣል:: ቀይ ካርድ ያየ ግለሰብ ወይም ድርጅት ከጨዋታ ውጭ ይሆናል:: በጥፋትም ይቀጣበታል:: ኢህአዴግ በወረቀት ላይ ያሰፈራቸው የፖለቲካ: የኢኰኖሚና የማህበራዊ ጉዳይ ፖሊሲዎች በትክክል በስራ ላይ ቢውሉ ህልውናው ሊያከትም እንደሚችል ያውቀዋል::  የነጻና የገለልተኛ ማህበራዊና ዴሞክራሲያዊ ተቋሞች መኖር ለህልውናው ጸር ናቸው:: ትክክለኛ ምርጫ ቢካሄድ እንደማይመረጥ ይረዳል:: መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ እንደማይደግፈው እንዲያውም እንደሚጠላው ያውቃል:: ስልጣኑን ከለቀቀ ደግሞ በስልጣን ላይ በነበረበት ጊዜ ለሰራቸው ወንጀሎች ሁሉ መጠየቅ ይመጣል:: ባለስልጣናቱ ያላግባብ ያከማቹት ንብረት ሊወረስ ይችላል:: ስልጣን ከሌለ አይደለም ሀብት ንብረትን ህልውናንስ እንዴት ማስጠበቅ ይቻላል? ተተኪው መንግስት ያለፈውን ሁሉ ይቅር ብሎ የያዙትን ይዘው ከስልጣን ብቻ ገለል እንዲሉ ስለመፍቀዱ ምን ማረጋገጫ ይኖራል? ስለዚህ ወረቀት ላይ ያለው ለተመልካች ፍጆታ የሚውል ነው:: በስራ ላይ የሚውለው በስውር የሚተላለፈው የውስጥ መመሪያ ነው:: ወረቀት ላይ የሰፈረውንና በተግባር እየታየ ያለውን አለመጣጣም የተመለከተ &#8220;እንዴት እንዲህ ሊሆን ይችላል?&#8221; ብሎ ቢጠይቅ መልሱ ቀላል ነው:: &#8220;ፖሊሲወቻችን እንከን የላቸውም:: ዴሞክራት ናቸው የሚባሉ ሀገሮችን በጎ ተሞክሮወች ሁሉ ያካተቱ ናቸው:: ችግሩ የአፈጻጸም ነው:: አፈጻጸምን ለማሻሻል አቅምን ማሳደግ የግድ ይላል:: እና ለአቅም ግንባታ ፕሮጀክት ማስፈጸሚያ እጃችሁን ዘርጉ&#8221; የሚል መልስ ይሰጥና ሌላ የገቢ ማሰባሰብ ስራ ይሰራል:: የመናገር: የመሰብሰብ: ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ: የመምረጥ: ወዘተ መብቶች በወረቀት ላይ ያሉ እንጅ በተግባር የሚተረጎሙ አይደሉም:: እኒህን በወረቀት ላይ የተጻፉ መብቶች ለመጠቀም የሞከረ ማንኛውም አካል ቀይ መስመሩን የተሻገረ ነው::</p>
<p>መኢአድ ዳዴ ማለት እስኪጀምር ድረስ ከመንግስት ምንም አይነት ጥቃት ሊሰነዘርበት እንደማይችል የተረዱት ሀይሌ ካለምንም ስጋት እንደበፊቱ ሁሉ ጎንደርንና ጎጃምን ከዳር ዳር አዳረሷቸው:: በመኪና የሚኬደውን በመኪና: ለፈረስ የተመቸውን በፈረስ ካልሆነም በእግር:: &#8220;ግዴላችሁም እኔ ያጠፋኋችሁ ልሁን&#8221; ይላሉ ሻለቃ ያገነገኑ ሰዎች ሲያጋጥሟቸው:: ባርኔጣቸውን ከጭንቅላታቸው ላይ አንስተው ፍጹም ትህትና በተመላበት አኳኋን &#8220;ጤና ይስጥልኝ ጌታየ&#8221; ብለው ሲቀርቡ አይሆንም ብሎ ገፍቷቸው ሊሄድ የሚችል ሰው አይገኝም:: ቀልቡን ሰብሰብ አድርጎ ያዳምጣቸዋል:: በዚህ መልክ ቀደም ሲል የመዐሕድ አባል የነበሩትን ሁሉ ወደመኢአድ አስገቧቸው:: የየወረዳ ኮሚቴዎችንም አጠናከሩ::</p>
<p>’የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲወች ግንባር’ ለመፍጠር የተደረጉት ብዙ ሙከራወች ገንዘብ: ጉልበትና ጊዜ በልተው ሳይሳኩ ቀርተዋል:: በሀገር ውስጥ ከኦብኮና ከደቡብ ሕዝቦች ጋር ተመስርቶ የነበረው ህብረት ብዙ መሄድ ሳይችል ቀርቶ ፈርሷል:: በውጭ ሀገር የሚገኙ የፖለቲካ ድርጅቶችን ያካተተው የተቃዋሚ ሀይሎች ህብረትም ቢሆን አባል ፓርቲዎችን ሰብስቦ ይዞ መቀጠል አልቻለም:: ኢዴፓና መኢአድ ተከታትለው ከህብረት ጋር ተፋተናል ሲሉ አውጀው የየራሳቸውን መንገድ ተከተሉ:: በመሰባሰባቸው ተስፋ አሳድሮ የነበረው ሕዝብ ተስፋው ጫጨ:: ሻለቃ ከህዝብ ጋር ተመሳስለው ኗሪ በመሆናቸው የህዝቡን ስሜት ይከታተላሉ:: ይህ የፓርቲወች ህብረት መፍረስ መሰራት እርሳቸውንም አበሳጭቷቸዋል:: &#8220;እንዲያው ምን ይሻላል? የልጅ ጨዋታ አደረጉትኮ&#8221; ይላሉ ከመሰሎቻቸው ጋር ሲያወጉ:: እንዲህ እንዲህ ሲል ቆይቶ በአራት ፓርቲዎች (መኢአድ: ኢዴፓ: ቀስተደመና: ኢዴሊ) ጥምረት ቅንጅት ተመሰረተ::</p>
<p>የቅንጅት መመስረት በየአካባቢው ይደረጉ የነበሩትን የፓርቲዎች የጎንዮሽ ሽኩቻ አስታገሰ:: ባህርዳር ጽ/ቤት የከፈቱት መኢአድና ኢዴፓ መድህን መጠላለፋቸውን ትተው በአንድነት ቆመዋል:: ቀደም ባሉት ጊዚያት አንዱ የሌላውን ጽ/ቤት ረግጦ አያውቅም ነበር:: አሁን ሁኔታው ተለውጧል:: ሁለቱም ጽ/ቤቶች የጋራ አገልግሎት እየሰጡ ነው:: ኢዴፓዎች ድንቅ ድንቅ ሰዎች አሏቸው:: ጥሩ ሀሳብ ማመንጨት: በሳል አመራር መስጠት የሚችሉ ሰዎችን ያካተተ ስብስብ ነው ኢዴፓ:: መኢአድ በአደረጃጀት ከኢዴፓ በእጅጉ ይበልጣል:: በሻለቃ ሀይለየሱስ ሀላፊነት ስር የሆነው ባህርዳር ልዩ ዞንና ምእራብ ጐጃም ዞን እስከቀበሌ ድረስ ተደራጅቷል:: በየአንዳንዱ የገጠር ቀበሌ አምስት አምስት አባላት ያሏቸው አመራር ሰጪ ኰሚቴዎች ተቋቁመዋል:: የባህር ዳር የመኢአድ ወኒያምና ቆራጥ አባላት ኢዴፓዎችን ወደዋቸዋል:: በመሀል የነበረው የመፈራራትና የመጠራጠር ስሜት አሁን የለም:: አንድ ላይ ተሰብስበው ይመክራሉ: መክረውም በጋራ ይወስናሉ::</p>
<p>የቅንጅት አመራር ከገዥው ፓርቲ ጋር የሚያደርጋቸው ክርክሮች የሁሉንም ቀልብ ስቧል:: አርሶ አደሩ ሳይቀር ክርክሩን ለመከታተል ሬዲዮ ገዝቶ ጆሮው ላይ ለጥፎ ይውላል:: የሰላ አንደበትና የበሰለ ትችት የኢሐዴግን ተከራካሪዎች ያንተፋትፍ ይዟል:: ፖለቲካው ነፍስ እየዘራ ነው:: ባሕር ዳሮች የበለጠ ተነቃቅተዋል:: አሁንም ባሕርዳሮች እንደማእከል እያገለገሉ ነው:: ከየዞኖች በሚመጡ ችግሮች ዙሪያ መግለጫ ይሰጣል:: የቅንጅት ኮሚቴው ለችግሮች መፍትሄ ፍለጋ ከፖሊስና ከአስተዳደር ጋር ውይይት ያደርጋል:: መፍትሄ ግን የለም:: ያም ሆነ ይህ ቅንጅት በያንዳንዱ ልብ ውስጥ ቦታ ይዟል:: ትልቅ ስኬት! የቅንጅት የምርጫ ምልክት የሆነው ሁለት ጣት የሰላምታ መለዋወጫ ሆኗል:: መቸም ፌስታ ነው:: እስካሁን ስር የሰደደ ችግር አይታይም::</p>
<p>የኢትዮጵያ አርሶ አደር የመላው ኢትዮጵያን ሕዝብ ከ80%-85% ያህል ይሆናል:: ኢሕአዴግ የትግል አጋሬ ነው የሚለው አርሶ አደሩን ነው:: አርሶ አደሩ የሚኖረው በገጠር ነው::  ስለዚህ ቢያንስ 80% የፓርላማ ወንበር እንደሚያሸንፍ እርግጠኛ ሆኗል:: ቢሆንም እኒህ መአተኛ ቅንጅቶች ወደገበሬው መጠጋት የለባቸውም:: መርዛቸው እንዲህ በቀላሉ የሚነቀል አይሆንም:: ስለዚህ ባህርዳሮች ወደገጠር ተጉዘው አርሶ አደሩን እንዳያሰባስቡ ሆደ ሰፊው ብአዴን መንገዶችን ሁሉ ጥርቅም አድርጐ ዘጋ::</p>
<p>አርሶ አደሩ ተሰባስቦ የሚገኝበት የእረፍት ጊዜ የደብሩ ታቦት የሚከበርበት ቀን ነው:: ለምሳሌ አዴት ታቦቱ መድሀኔአለም ከሆነ አዴቶች የወሩን 27ኛ ቀን ስራ ፈትተው ያከብሩታል:: በእለቱ ቤተክርስቲያን ሄዶ ማስቀደስ: የታመመን መጠየቅ: የተጣላን ማስታረቅ: ዘመድ ወዳጅን መጐብኘት ነው ዋናው ስራ:: ሌላውም ቢሆን እንዲሁ የየራሱን የበአል ቀን በተመሳሳይ ሁኔታ ነው የሚያሳልፈው:: ይህች ቀን አርሶደሩ ቤተክርስቲያን ተሰባስቦ የሚገኝባት ናት:: ቅንጅቶች ይህችን ቀን እንደሚጠብቁ ግልጽ ነው:: የየደብሩ ታቦት ከሚውልበት ቀን የተሻለ አይገኝምና ወደዚያው ይገሰግሳሉ:: ታዲያ ይህን የሚያውቁት ብአዴኖች እለቷን በተለያየ ፕሮግራም (ጤና: ጸጥታ: ልማት ወዘተ) ወጥረው ይይዛሉ:: ባሕር ዳሮች አርሶ አደሩን አሰባስበው የፖለቲካ ፕሮግራማቸውን ለማስተዋወቅ አልተቻላቸውም:: ከወር አንዲት የበአል ቀን ጠብቀው ተጉዘው ሲደርሱ ፖሊሶች ቀድመው ቦታው ላይ ተገኝተው ’ቤተክርስቲያን ውስጥ የፖለቲካ ስራ መስራት አይቻልም’ በማለት ይከለክሏቸዋል:: ከቤተ ክርስቲያን መልስ ገበሬው ምሳውን እንኳ መብላት አልፈቀድለት ብሎ እስከ ምሽት ድረስ በስብሰባ ይጠረነፋል:: ይህ ቀደም ሲል ያልነበረ ልምድ የተፈጠረው ቅንጅቶች ገበሬውን እንዳያገኙትና እንዳይበክሉት በሚል ነው:: &#8220;ቀደም ብለን የያዝነው ፕሮግራም ስለሆነ በእኛ ፕሮግራም ማንም የፖለቲካ ስራ እንዲሰራ አንፈቅድም:: ከፈለጋችሁ በሌላ ቀን ልትጠሩ ትችላላችሁ&#8221; እየተባሉ ቅንጅቶች ድካም ብቻ አትርፈው መመለስ ጀመሩ:: ይህንን የተገነዘቡት ሻለቃ አንድ ብልሀት ዘየዱ:: ሀይሌ የማንንም ሀሳብ አይንቁም:: &#8220;ከአንድ ራስ ሁለት ይበልጣል: ለእኔ ያልታየኝ ለአንተ ሊታይህ ይችላል&#8221; የሚሉት ሀይሌ የሁሉንም ሀሳብ ካዳመጡ በኋላ &#8220;ሁሉም የነርሱ ነው:: በየቦታው  ሄደን አቤት ብንልም መፍትሄ ልናገኝ አልቻልንም:: በየገጠሩ ለፍተን ሰውን እንዳናገኝ ስለተከለከልን ካለምንም ውጤት ደክመን እየተመለስን ነው:: አርሶ አደሩ እንዳይከዳቸው በጣም ሰግተዋል:: ፈርተውናል:: እንግዲህ አንድ የሚታየኝ አማራጭ አለ: የቤት ለቤት ቅስቀሳ&#8221; ሲሉ ተናገሩ:: ይህ ሀሳብ መተኪያ የሌለው ነው ተብሎ በመታመኑ የቤት ለቤት ቅስቀሳ እንዲካሄድ ተወሰነ:: የየቀበሌው ኮሚቴ አባላት የዚህን ስራ ሀላፊነት ወሰዱ:: በዚህ መሰረት የቤት ለቤት ቅስቀሳው ተጀመረ:: የየቀበሌው ኮሚቴ አባላት ከቤት ቤት እየዞሩ ግንዛቤ ማስጨበጥ ቀጠሉ:: &#8220;እናንተ ቅንጅትን እንድትመርጡ የምንፈልገው በምርጫው ቀን በምርጫ ወረቀቱ ላይ ብቻ ነው:: ከዚያ ውጭ እነርሱ የሚሏችሁን ሁሉ እሽ በሏቸው:: ተሰብሰቡ ሲሏችሁ እሽ: ማንን ነው የምትመርጡ ሲሏችሁ እናንተን በሏቸው:: ማን ማንን እንደመረጠ የሚያሳይ መሳሪያ ተክለናል የሚሉት ውሸታቸውን ነው:: እንዲህ አይነት መሳሪያ የለም&#8221; እያሉ አስጠኗቸው::</p>
<p>&nbsp;</p>
<p>በከተሞች አካባቢ የሚደረገው ህዝባዊ ስብሰባ በአንጻራዊነት በእጅጉ የተሻለ ነው:: ቅንጅቶች የምርጫ ምልክታቸውን የያዘ ቲሸርት አሰርተው ለብሰዋል:: ትግሉ ኢሕአዴግን በሰላማዊ መንገድ ከስልጣን ለማስወገድ ነው:: አለበለዚያ መብቶች የሚከበሩባት: ፍትህና እኩልነት የሰፈነባት ኢትዮጵያን ለመመስረት አይቻልም:: ኢሕአዴግን ከመንበረ ስልጣኑ ለማንሳት አብዛኛውን የፓርላማ መቀመጫ ማሸነፍ የግድ ይላል:: ስለዚህ የእኔ የእኔ ብሎ ነገር የለም:: ቅስቀሳው መካሄድ ያለበት በጋራ ነው:: በጋራ ወጪ መኪና መከራየት: የቅስቀሳ ወረቀቶችን ማባዛት: ሁሉንም- በጋራ መከወን:: ሕዝቡ ሁለንተናዊ ድጋፍ በማድረግ ከቅንጅቶች ጐን መቆሙን በግብር እያሳየ ነው::  ጽ/ቤቶች  በሰው ተጣበቡ:: ማን ማን እንደሆነ አይታወቅም:: ሁሉም ይወጣል ይገባል: ይሰራል:: አንዳንዶች ስጋት ገብቷቸዋል:: ይህንን እድል ተጠቅሞ ብአዴን ብዙ ነገር ሊያበላሽ ይችላል:: ሻለቃ እንዳባት ይገስጻሉ: ይመክራሉ:: &#8220;ቢመጡ እኛ ምን ቸገረን:: በድብቅ የምንሰራው ስራ የለን! ሚስጥር ባይኖርባቸውም ጥንቃቄ የሚጠይቁ አንዳንድ ሰነዶቻችንን ከእይታ አርቀናቸዋል:: እዚህ ያለው ጽ/ቤቱና መገልገያ እቃወች ብቻ ናቸው:: የሚያስፈራን ምንም ነገር የለም:: እንዲያውም እንግዶችን መቀበል ያለብን በትህትና ነው:: አያችሁ በአንድ ሰው ብልጫ አንድ ወንበር ይገኛል: በአንድ ወንበር ብልጫ ደግሞ ገዢ ፓርቲነት:: ያላወቅነው ሰው ሁሉ ጠላታችን ነው ብለን ፊት የምንነሳው ከሆነ ምናልባት ያ ሰው በእውነት ሊያግዘን የመጣ ሰው ቢሆን ሊሸሸን ማለትም አንድ ድምጽ ሊያሳጣን ይችላል&#8221; በማለት የአባላትን የጎፈነነ ስሜት ገፈፉ:: ጥድፊያ ነው:: ሁሉም ይሰራል:: ቅንጅቶች ሰርግ የሚደግሱ መሰሉ:: ከሁሉ ከሁሉ ባህር ዳር የተጠራው ሕዝባዊ ስብሰባ አስገራሚ ነበር:: የባሕርዳር ኗሪ ለስብሰባው ንቅል ብሎ ወጥቷል:: የፖሊና የፔዳ ተማሪወች ቀድመው ስቴዲዮም ደርሰዋል:: የባሕርዳር ስታዲዮም የቅንጅትን እድምተኛ ሰብስቦ መያዝ ባለመቻሉ አካባቢው ሳይቀር በሕዝብ ተጨናንቋል:: እለቱ የጥምቀት በአል የሚከበርበት እንጅ ስብሰባ የሚደረግበት አይመስልም:: ከአዲስ አበባ የቅንጅት አመራር ተወካዮች ተገኝተዋል:: የመድረክ መሪው ሰላማዊ መፈክሮችን ያሰማል:: በዚህ ወቅት አንድ ለየት ያለ ነገር ተከሰተ:: &#8220;አንድ በኢትዮጵያ ባንዲራ ያጌጠች መኪና ክላክስ እያሰማችና ከሰው ጋር እየተጋፋች በቀስታ ወደስታዲዮሙ ዘለቀች:: በመኪናዋ ላይ ያሉት ሰዎች የኢትዮጵያን ባንዲራ ይዘው ድምጻቸውን ከፍ አድርገው መፈክር ያሰማሉ:: የመድረክ መሪው ጩኸት በተቀላቀለበት መንፈስ ደስታውን ገለጸ:: &#8220;በጭብጨባ ተቀበሏቸው&#8221; አለ:: ስታዲዮሙ በጩኸትና በፉጨት ድብልቅልቁ ወጣ:: በዚያች መኪና የመጡት ሰዎች የሙገር አግሮ ኢንዱስትሪ ሰራተኞች ነበሩ:: ስብሰባው ከታሰበው በላይ በደመቀ ሁኔታ በስኬት ተጠናቀቀ:: በበነጋታው ጠዋት የሙገር አግሮ ኢንዱስትሪ ባለቤት የሬዲዮ ቃለመጠይቅ እየተደረገላቸው ነበር:: &#8220;ቅንጅት መኪናችንን አስገድዶ በመውሰድ ለቅስቀሳ ተጠቀመባት&#8221; ብለው እርፍ አሉ:: ምን ያድርጉ? ተይዘዋል ማለት ነው:: የእውነት ዴሞክራሲ አለ መስሏቸው መብታቸውን ተጠቅመው ድጋፋቸውን የሰጡት አግሮ ኢንዱስትሪዎች በወያኔ ተስፈኞች ጥርስ ውስጥ ገቡ::</p>
<p>&nbsp;</p>
<p>የአውሮፓ ህብረት ታዛቢዎች በየጽ/ቤቶች እየተገኙ እየተደረገ ያለውን አጠቃላይ እንቅስቃሴ ይከታተላሉ: አስተባባሪወችን ይጠይቃሉ:: በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር የነበሩት ኦሪያል ብራዚል በጣና ሆቴል የቅንጅትና የህብረት ተወካዮችን አግኝተው አነጋግረዋል:: ሁለቱ ድርጅቶች እያከናወኗቸው ያሉትን ተግባራት: በገዥው ፓርቲ እየደረሱብን ነው ያሏቸውን ችግሮች ገልጸው እኛን ለማፈን ከበላይ አካል ተዘጋጅቶ በተዋረድ እስከቀበሌ ድረስ እንዲሰራበት የተላለፈ የውስጥ መመሪያ ነው በማለት ሰነድ አስረክበዋል:: አሜሪካም ሆነች ሌሎች የአውሮፓ ሀገሮች ግንባራቸውን ኮስተር አድርገው ወያኔን &#8220;ዋ!&#8221; ብለው ከእኩይ ተግባሩ እንዲታቀብላቸው ሊያስፈራሩላቸው አሻፈረኝ ካለም አርጩሜ ቆርጠው ሾጥ ሾጥ አድርገው ሊያስተካክሉላቸው እንደማይችሉ ያውቃሉ:: ግን ተግባሩ መገለጽ ስላለበትና ለፎርማሊቲም ያህል መሆን ስለሚገባው ተደረገ:: በወያኔ እኩይ ተግባር አንጀቱ ያረረ ሁሉም ነው: የራሱ አባላት ጭምር:: ስለዚህ የወያኔን ብልሹ አሰራር የሚያጋልጡ ሰነዶችን ማግኘት ከባድ አልነበረም::</p>
<p>&nbsp;</p>
<p>አይደርስ የለምና የምርጫው እለት ግንቦት 7 1997 ደረሰ:: ሁሉም በጠዋት ተነስቶ ስፍራ ስፍራውን ይዟል:: የቅንጅት ጽ/ቤት በጣም በጠዋት እንዲከፈት በተወሰነው መሰረት ጽ/ቤቱ ውስጥ እንዲሰሩ የተመደቡት ሰዎች በጠዋት ተገኝተው ስራቸውን ማከናወን ጀምረዋል:: ሪፖርት ይቀበላሉ: ሪፖርት ያደርጋሉ:: በምርጫ ጣቢያወች በታዛቢነት የተመደቡት የቅንጅት ሰዎች ጥብቅ መመሪያ ተሰጥቷቸው ተሸኝተዋል:: &#8220;ድምጽ መስጠት ከመጀመሩ በፊት የምርጫ ኮሮጆው ባዶ መሆኑን አረጋግጡ: ብአዴኖች ሊያበራግጓችሁ ስለሚሞክሩ በምንም መልኩ ሳትደናገጡ በትእግስት ማጠናቀቅ አለባችሁ:: መራጩ ህዝብ ላይ የሚደረገውን ወከባ ተጋፈጡ:: የሚስጥር ድምጽ መስጫው አካባቢ የኢሕአዴግ ሰዎችን እንቅስቃሴ ተከታተሉ: የድምጽ ቆጠራው እንደተጠናቀቀ የምርጫ ጣቢያው ማህተም ያረፈበት ውጤት ተቀብላችሁ በፍጥነት ወደጽ/ቤት እንድትመለሱ &#8212;&#8221; ተብለው ተመክረው ነው ቀድመው በየምድብ ቦታቸው እንዲገኙ የተደረጉት:: በሌላ በኩል ከኗሪው ጋር ተመሳስለው በምርጫ ጣቢያወች አካባቢ የሚደረጉ ሁኔታወችን እየተከታተሉ በስልክ ጽ/ቤት ላሉት ሰዎች እንዲያስተላልፉ የተመደቡት ሰዎች በንቃትና በጥንቃቄ ግዳጃቸውን እየተወጡ ነው:: ሁሉም ነገር አሪፍ ነው::  ኢሕአዴግ በምእራብ ጐጃሞች ላይ ተደጋጋሚ የፍተሻ ተኩስ አካሂዶ ችግር የለም ብሎ ደምድሟል:: በወታደራዊ ሳይንስ ትምህርት የፍተሻ ተኩስ ማለት አንድ ጠላት ሊኖርበት ይችላል ተብሎ የተጠረጠረ አካባቢ ላይ የሚደረግ የሩምታ ተኩስና አሰሳ ነው:: ተኩስ በተደረገበት አካባቢ ጠላት ካለ የአጸፋ ተኩስ ይከፍታል:: ምእራብ ጐጃሞች ይህን የፍተሻ ተኩስ አልፈውታል:: በየስብሰባው ላይ እየተገኙ የገዥው ፓርቲ አጋርነታቸውን አረጋግጠዋል:: ደረሱብን ብለው ያሏቸውን ችግሮች አሰምተው በሚቀጥሉት አምስት የስልጣን ዘመናቸው ችግሮቻቸው እንደሚቀረፉላቸው በብአዴኖች ቃል ተገብቶላቸዋል:: የየተሰበሰቡበት የውሎ አበል ተከፍሏቸው ተቀብለዋል:: በየስብሰባው ማብቂያ ላይ የቀረበውን ድግስ በደስታ ተጋብዘው ተመራርቀዋል:: ቅንጅት ጸረ ልማት ድርጅት እንደሆነ ተነግሯቸው ልክ ነው ብለው ቅንጅትን አውግዘው ፈክረዋል:: ስለዚህ ብአዴኖች በምእራብ ጐጃም ላይ ስጋት የለባቸውም:: ሙሉ ሀይላቸውን እነርሱን በሚነቅፉና አስተማማኝነታቸው በሚያጠራጥር ዞኖች ላይ ብቻ ማሳረፍ እንዳለባቸው አምነዋል:: እና ለምእራብ ጎጃም የየምርጫ ጣቢያ አስመራጮች የተለየ መመሪያ አልተላለፈም::</p>
<p>&nbsp;</p>
<p>የምርጫው እለት ማታ መላው የባሕርዳር ህዝብ እንቅልፍ በአይኑ አልዞረም:: በንቃት ይጠብቃል:: መብራት አሁንም አሁንም ይቋረጣል:: &#8220;ሌባ ሌባ&#8221; ሲል ሕዝቡ ይጮሀል:: ብአዴኖች ወያኔ የሚሆነውን የሚሆኑ: አድርጉ የሚባሉትን የሚያደርጉ ሮቦቶች ናቸው ብሎ ስለሚያምን ሁሌም ይጠራጠራቸዋል:: መብራት የሚያጠፉ ቀድመው ባዘጋጁት የተሞላ የምርጫ ኮሮጆ ሕዝብ ድምጽ የሰጠበትን ኮረጆ ለመቀየር ነው ብሎ ይጠረጥራል:: እና መብራት ሲጠፋ &#8220;ሌባ ሌባ&#8221; እያለ ግር ብሎ ወደየምርጫ ጣቢያዎች ይተማል::  አንዳንድ ባለመኪኖች የመኪናዎቻቸውን የፊት መብራቶች ወደምርጫው ቦታ ቦገግ አድርገው በማብራት ሌብነቱን ለመከላከል ይጥራሉ:: በጥበቃ ብዛት ሕዝቡ ተሰላችቶ ወደየቤቱ እንዲመለስ ይመስላል ጊዜን በአግባቡ አለመጠቀም ይታያል:: እሁድ በጠዋት ወረፋ ይዞ ቀድሞ መርጦ ወደጉዳዩ ለመሰማራት ያሰበው ሕዝብ ወረፋው አልደርስ ብሎ እስከእኩለ ሌሊት ድረስ ተጉላላ:: ቢሆንም ሁሉም በእልህ: በጽናትና በትእግስት የፍላጎቱን አሳካ- መረጠ::</p>
<p>&nbsp;</p>
<p>ሻለቃ ልጃቸውን እንደሚድሩ አባት በደስታ ብዛት የሚይዙትን የሚጨብጡትን አሳጥቷቸዋል:: ይህን ይዘው ያን ይጥላሉ:: ወዲያ ሄድው ወዲህ ይመለሳሉ:: ሳያስቡት ብድግ ይሉና ተመልሰው ቁጭ ይላሉ:: እርሳቸው የሚወዳደሩበት የምርጫ ክልል መራጭ ወገኖቻቸው አይዞህ ብለዋቸዋል:: ደራወች ጥለው አይጥሏቸውም:: ምእራብ ጐጃም በርሳቸው የተደራጀ በመሆኑ በአሸናፊነት እንደሚወጡ ሙሉ እምነት አላቸው::</p>
<p>&nbsp;</p>
<p>ሰኞ እለት ከጠዋት ጀምሮ የቅንጅት የምርጫ ታዛቢወች እየተንጠባጠቡ ወደቅንጅት ጽ/ቤቶች መምጣት ጀመሩ:: የየምርጫ ጣቢያው ማህተም ያለበት የድምጽ ውጤት በእጃቸው ይዘዋል:: የቅንጅት አስተባባሪወች የየምርጫ ክልሎችን አሸናፊ ለማወቅ ከየምርጫ ጣቢያወች የመጡትን ውጤቶች መደመር ቀጠሉ:: ለማመን ይከብዳል:: ምእራብ ጐጃም ላይ መቶ በመቶ (100%) ቅንጅት አሸንፏል:: ቅንጅቶች ብዙ አይነት ስሜት እየተሰማቸው ነው:: ደስታ: ስጋት: ፍርሀት:: ደስታቸው:- የትግላቸው ፍሬ መልካም ከመሆኑ የመጣ ነው:: ስጋታቸው:- ምእራብ ጐጃም ላይ የተገኘው ውጤት በሌሎች ዞኖችና ክልሎች ያልተገኘ እንደሆነ ከሚል የመነጨ ነው:: ፍርሀታቸው:- ሕዝብ በድምጹ የጣለው መንግስት ምላሹ ምን ሊሆን እንደሚችል ካለማወቃቸው የተነሳ ነው:: ምናልባት ምክንያት ፈጥረው በድርጅቱና በአባላቱ ላይ የጥፋት ስራ ቢሰሩስ? ሕዝቡንስ ይበቀሉት ይሆን? ወይስ ምን?</p>
<p>&nbsp;</p>
<p>ሻለቃ ወታደር በመሆናቸው ጠርጣራ ናቸው:: በተለይ ወያኔ ከቶውንም ሊታመን የማይችል ድርጅት ነው:: ብአዴኖች ደግሞ የራሳቸው ህሊና የላቸውም:: አስፈራራ ሲባሉ የሚያስፈራሩ: ደብድቡ ሲባሉ ሙልጭ አድርገው የሚገርፉ: እሰሩ ሲሏቸው የሚያስሩ: ግደሉ ሲባሉ የሚገድሉ ናቸው:: ለእነርሱ ሕዝብ: ሞራል: ምናምን ቦታ የላቸውም:: ስለዚህ ወያኔ ሱርፍ ብሎበት &#8216;ለየታዛቢወች የሰጣችኋቸውን የውጤት መግለጫ ሰነዶች በአስቸኳይ ቀሙ&#8217; ካላቸው እሳት ጐርሰው እሳት ለብሰው እንደሚመጡባቸው ያውቃሉ:: አሁንም ፍጥነት ያስፈልጋል:: የውጤት መግለጫ ሰነዶችን ሰብስቦ ማራቅ::</p>
<p>&nbsp;</p>
<p>የምእራብ ጐጃም አርሶ አደር ታሪክ ሰራ:: እንዲህ ያለ ውጤት በየትኛውም የሀገሪቱ የየክልል ዞኖች አልታየም:: ሻለቃ በምእራብ ጎጃም ኮርተዋል:: ቃሉን የማያጥፍ: ለእውነት የቆመ: የቁርጥ ቀን የኢትዮጵያ ልጆች ስብስብ ሲሉ ያሞካሻሉ:: ወያኔ ደግሞ &#8216;ጐጃም በከፋ ሁኔታ አጠቃን:: ጉድ ሰራን:: ጐጃምና ተልባ እያደረ ሸርተት ነው የሚባለው ተረት ሀሰት መስሎን ነበር&#8217; ሳይል አይቀርም:: ጐጃም በፍርሀትና በጥቅም ቃሉን አይለውጥም:: በነጻነት ለመወሰን እድሉን ሲያገኝ ሁሌም ከእውነት ጐን የሚሰለፍ ባለማተብ ሕዝብ ነው:: ’ውሻ በበላበት ይጮሀል’ የጎጃሞች መለያ አይደለም::</p>
<p>&nbsp;</p>
<p>ቅንጅት በበርካታ የምርጫ ክልሎች ተጭበርብረናል ባለበት ወቅት አያልቅበት ወያኔም &#8220;ካላችሁስ ኧረ እኔም ተጭበርብሬአለሁ&#8221; ብሎ ቀረበ:: ይሉኝታና ሀፍረት አልፈጠረበትም:: ለነገሩ ይሉኝታና ሀፍረት የፋራ ነው: ወያኔ ደግሞ አራዳ:: ቅንጅት ቅሬታ ካቀረበባቸው የምርጫ ክልሎች በዳግም ምርጫው አንድም ሳያገኝ ቀረ:: ወያኔዎች ተጭበርብረናል ብለው ቅሬታ ያቀረቡባቸውን ቦታወች አስመለሱ:: እንዲህ ናቸው ወያኔዎች:- ታግለው የሚጥሉ: አባረው የሚይዙ: ሮጠው የሚያመልጡ: ተናግረው የሚያሳምኑ: ተከራክረው የሚረቱ:: እና ሁሉም ሆነ:: በዳግም ምርጫው ምእራብ ጐጃም በድምጹ አስከብሮት የነበረውን አንድ ወንበር አጣ:: ም/አፈ ጉባኤ ሽታየ ምናለ በዳግም ምርጫው በክንዳሙ ወያኔ እገዛ አንድ የፓርላማ ወንበር ከህዝብ ነጠቁ::</p>
<p>&nbsp;</p>
<p>-ጐጃም በመጀመሪያወች የወያኔ የግዛት አመታት በተጭበረበረ ገንዘብ ምርቱን ተነጥቋል::</p>
<p>-በ1989 ዓ.ም አካባቢ የጐጃም ሕዝብ &#8216;የደበቅኸው መሳሪያ አለ&#8217; ተብሎ ታስሯል: ተገርፏል: ተገድሏል::</p>
<p>-ከምርጫው በኋላ ኢሕአዴግ የአማራ ክልልን እንደተሸነፈ አምኖ ሊለቅ ነው የሚል ወሬ ባ/ዳሮች ዘንድ ደረሰ:: ቀጥሎ &#8220;እስከቀበሌ ድረስ የሚዘልቅ የክልሉን መንግስት መዋቅር ሰርታችሁ በቶሎ አቅርቡ:: ከዘገየን ቅንጅት ሊያስተዳድር አልቻለም ብለው ተመልሰው ሊወስዱብን ይችላሉ&#8221; የሚል መልእክት ከቅንጅት ላእላይ ምክር ቤት መጣ በመባሉ: ኮሚቴ ተቋቁሞ ኰሚቴው የክልሉን መንግስት አስተዳደራዊ መዋቅር ሰርቶ ሰነዱ ፋክስ ተደርጐ ነበር:: ፋክስ የተደረገው ጊዮን ሆቴል በሚገኘው የፋክስ ሜሽን ነበር:: ፋክሱ ለቅንጅት ላእላይ ምክር ቤት መድረስ አለመድረሱ አልተረጋገጠም:: ብአዴኖች ግን እንዴት እንዳገኙት ሳይታወቅ ኮፒው ደርሷቸዋል:: እና በሰነዱ ላይ ፊርማቸውን ያስቀመጡትን ሁሉ ሰብስበው አሰሩ:: እስረኞች ሌሊት ሌሊት በሽፍን መኪና ወደመሸንቲ መንገድ እየተወሰዱ ጫካ ውስጥ ተገረፉ::</p>
<p>-በጥቅምት 1998 የባሕርዳር ኗሪዎች በጥይት ተደበደቡ::</p>
<p>-በሚኒሊክ ጊዜ በደል ተፈጽሞብናል በሚል በአሁኑ ዘመን ያለውን አማራ ለመበቀል ያላፈረው ወያኔ የትናንቱን የምእራብ ጐጃም ጥቃት እንዴት ሊረሳው ይችላል? እና ጐጃሞች ዛሬም በሰበብ አስባቡ እየተሳደዱ ነው::</p>
<p>&nbsp;</p>
<p>ሻለቃ ሀይለየሱስ እጅጉ በሀላፊነታቸው ስር የተቀመጡትን ባ/ዳር ልዩ ዞንና ምእራብ ጎጃም ዞንን እድሜና ተሞክሮ ባጐናጸፋቸው ዘዴ ተጠቅመው ከሁሉም አባላት ጋር አሸንፈዋል:: የድሉ ባለቤትና የትግሉ አራማጅ የነበሩትን መላው የቅንጅት ቤተሰቦች: መላው የባህርዳርና የምእራብ ጎጃም እንዲሁም የራሳቸውን መራጭ የደራ ህዝብ ከልባቸው የክብር መዝገብ ላይ አስፍረዋል:: የቅንጅት አባላትም ሻለቃን በክብር ያስቧቸዋል::</p>
<p>አማሮች ዛሬም ሁነኛ ሰው ያስፈልጋቸዋል::</p>
<p>ረጅም እድሜ ለሻለቃ (ሻቃ) ሀይለየሱስ እጅጉ!</p>
<p>&nbsp;</p>
<p>&nbsp;</p>
<p>&nbsp;</p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3281"     class="crp_title">ሰውየው (ክፍልሁለት) ከይገርማል&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3229"     class="crp_title">በምርጫ 97 የትዝታ ማህደር ውስጥ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2627"     class="crp_title">ዶ/ር መረራ ጉዲና እና አቶ ገብሩ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2923"     class="crp_title">&#8220;&#8216;አማራ ኬላ&#8217; የሚባሉ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/998"     class="crp_title"> &#8211; በልጅግ ዓሊ</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=83273</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>የሙስናው አስር ምስጢር! (ማረ በላዎቹ ርስ-በርስ ተበላሉ!)</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3432</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3432#comments</comments>
		<pubDate>Tue, 21 May 2013 14:47:29 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3432</guid>
		<description><![CDATA[በሰሎሞን ተሰማ ጂ. semnaworeq.blogspot.com Email: solomontessemag@gmail.com ለብዙዎች “ሙስና” የሚለው ቃል በ1989 ዓ.ም ወዲህ የተፈጠረ ሃይለ-ቃል ይመስላቸዋል፡፡ ነገር ግን አይደለም፡፡ ቃሉ ግዕዝ ነው፡፡ ትርጉሙም፣“ጥፋት” ማለት ነው፡፡ በአማረኛም የኖረ ሕዝባዊ ግጥም/አባባል አለ፤ እንዲህ የሚል ነው፡፡     “የከንሯ ለዛ፣ የጉንጯ ሙስና፤          “ዐርብ ሮብ ያስክዳል፣ እንኳን ዐሙስንና፡፡” ይላል - አዝማሪም፡፡ በዚህ አገባብም መሠረት “ሙስና” የሚለው ቃል ትርጉም “ፈራሹ፣ ረጋፊው-መልኳ፣ ውበቷ እንዳጠፋ [...]<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3329">የአዲስ ጉዳይ መጽሔት ርዕሠ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3201">በሙስና ተጠርጥረው የታሰሩት&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/420">ታስሮ የነበረው ኤርሚያስ አመልጋ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/705">የጁኔይዲ ሳዶን ወደ ኬኒያ መሰደድ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3148">የናዝሬት ጉምሩክ የህግ ማስከበር&#8230;</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<div>በሰሎሞን ተሰማ ጂ. semnaworeq.blogspot.com</div>
<div>Email: <a href="mailto:solomontessemag@gmail.com">solomontessemag@gmail.com</a></div>
<div></div>
<div><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/Addis-Guday.jpg"><img class="alignleft size-medium wp-image-3434" alt="Addis Guday" src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/Addis-Guday-220x300.jpg" width="220" height="300" /></a>ለብዙዎች “ሙስና” የሚለው ቃል በ1989 ዓ.ም ወዲህ የተፈጠረ ሃይለ-ቃል ይመስላቸዋል፡፡ ነገር ግን አይደለም፡፡ ቃሉ ግዕዝ ነው፡፡ ትርጉሙም፣“ጥፋት” ማለት ነው፡፡ በአማረኛም የኖረ ሕዝባዊ ግጥም/አባባል አለ፤ እንዲህ የሚል ነው፡፡     “የከንሯ ለዛ፣ የጉንጯ ሙስና፤</div>
<div>         “ዐርብ ሮብ ያስክዳል፣ እንኳን ዐሙስንና፡፡” ይላል -</div>
<div>አዝማሪም፡፡ በዚህ አገባብም መሠረት “ሙስና” የሚለው ቃል ትርጉም “ፈራሹ፣ ረጋፊው-መልኳ፣ ውበቷ እንዳጠፋ ገፋፋኝ” ለማለትና ለማሳበብ ነው የፈለገው (ደስታ ተክለ ወልድ፣ <b><i>ዐዲስ ያማርኛ መዝገበ ቃላት</i></b>፣ 1962 ዓ.ም፣ ገጽ-822)፡፡</div>
<div></div>
<div>በቅርቡ የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ሃላፊዎችን ሰብስበው በ2006 ዓ.ም የበጀት ዓመት፣ አንድ መቶ ሁለት ቢሊዮን ብር በላይ እንሰበስባለን” እያሉ ይዝቱ የነበሩት አቶ መላኩ ፈንታና አቶ ገብረ ዋህድ ወልደ ጊዮርጊስ፣ በዚህ የብር ጮማና የንዋይ ብርንዶ ውስጥ ተቀምጠው የተጣለባቸውን ኃላፊነትና ታማኝነት ቢዘነጉት ምን ያስደንቃል? ኧረ! ጨርሶ በኢትዮጵያ ብር አንገበያይም ብለው፣ በአሜሪካን ዶላርና በእንግሊዝ ፓውንድ ወይም በስዊዝ ፍራንክ ብቻ እንጠቀም ቢሉ ምን ያስገርማል? (ጥፋቱን ሙሉ ለሙሉ እነርሱ ላይ ማላከኩ ተገቢም፤ ትክክልም አይደለም፡፡ እና የማነው? በወቅቱ የእርምት ርምጃ ያልወሰደባቸው አካል ነዋ!፡፡)</div>
<div></div>
<div>በርእሴ ላይ ንዑስ-ርእስ አድርጌ የተጠቀምኩበት ሌላው ነጥብ “ማረ በላዎች” የሚለው ሃረግ ነው፡፡ ሆን ብዬ ነው፡፡ “ሙሰኞች” የሚለውን ቃል ለመጠቀምም ሆነ ለማለት ቀፈፌሽን ስለያዘኝ ነው፡፡ የዘመኑ አላዋቂ ባለስልጣኖችና የእነርሱን ቃል እንደገደል ማሚቶ የሚደግሙት ሎሌዎቻቸው እንደፈለጋቸው ይበሉት እንጂ፣ “ሙሰኞች” የሚል የግዕዝም ሆነ የዐማረኛ አገባብ የለም፡፡ “ሙሰኞች” ማለት ራሱ “ሙሰኝነት” ነው፡፡ ስለሆነም፣ በአማረኛዬ እንዳልሞስን በማሰብ “ማረ በላዎች” የሚለውን የራሴን ሃረግ መርጫለሁ፡፡ ቃሉ፣ የደስታ ተክለ ወልድ መዝገበ ቃላት (በገጽ-804 ላይ) እንደሚፈታው ከሆነ የሚከተለውን ትርጉም አለው፤ “ማረ በላ” ማለት ይላሉ፣ <b><i>“ጠጉራም፣ ጥፍራም፣ ነጭና ጥቁር፣ ዐጪር ቁመት ያለው አውሬ ነው፣ ማር የሚበላ አውሬ”</i></b> ማለት ነው ሲሉም ይገልፁታል፡፡ “ቀይ ማር የሚበላ የቆላ ጉንዳንም” ማለት ነው ሲሉ ይገልጹታል፡፡ “ጉንዳን”ም ተባለ “ዐጪር ቁመት ያለው አውሬ” ለምንነጋገርበት ረእሰ-ጉዳይ ገላጭና ተስማሚ ሆኖ አግኝቸዋለሁ፡፡ ስለሆነም፣ ተጠቅሜበታለሁ፡፡ ያልደከሙበትን የሚወስዱና የሚዘርፉ ሁሉ፣ “ገፊ-ማረ በላዎች” ናቸው፡፡</div>
<div></div>
<div>ሙስናና ማረ በላነት በኢትዮጵያ የኖረ ተግባር ነው፡፡ ስሙን እየቀያየረ “ሙስና” የሚለው የዐማረኛ ቃል ከመሆኑ በፊት የተለያየ ስያሜ ነበረው፡፡ በነገሥታቱ ዘመን “እጅ-መንሻ” ወይም “መተያያ” እየተባለ ይታወቅ ነበር፡፡ በዘመነ ደርግ ደግሞ “ብዝበዛና ምዝበራ” የሚል ትርጉም ተሰጥቶት ሲንከባለል ከቆየ በኋላ፣ በ1975 ዓ.ም ገደማ “ጉቦ” የሚል ታርጋ ተለጥፎበት በ1976 ዓ.ም “የሠርቶ አደሩ ቁጥጥር ኮሚቴ” የሚባል የአሁኑ “የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን” የመንፈስ አባት በዐዋጅ ተቋቋመ፡፡ ወያኔ/ኢህአዲግ አዲስ አበባን እንደተቆጣጠረ ሰሞንም የዛሬው “ሙስና” ደርግ ያወጣለትን “ጉቦ” የሚል ስሙን እንደያዘ ነበር፡፡ በነሐሴ 2/1983 ዓ.ም አቶ አሰፋ ደስታ የተባሉት የከፍተኛ 13፣ ቀበሌ 10 “የሰላምና መረጋጋት ኮሚቴ ሊቀመንበር” አንዲት አደጋ ካደረሰች ተሸከርካሪ ሹፌር ላይ ሃምሳ (50.00) የኢትዮጵያ ብር “ጉቦ” የተቀበሉትን የቀበሌው ሰላምና መረጋጋት አባላት አሳፍሰው፣ አሳስረዋቸው እንደነበር አዲስ ዘመን ዘገባ ያወሳል (ገጽ-1)፡፡</div>
<div></div>
<div>የወያኔ/ኢህአዲግ ታጋዮችና ተጋዳላዮች በ1984 እና በ1985 ዓ.ም በየመንግሥት መሥሪያ ቤቱም እየሄዱ “የደርግ/ኢሠፓ አባላት” ናቸው ብለው የጠረጠሯቸውን ሰዎች ከሥራ ለማባረር ይጠቀሙበት የነበረው የስም ማጥፊያና ከሥራ ማስወገጃ አጀንዳቸው፣ “ያላግባብ የሕዝብ ሃብት የዘረፉ” የሚለው ነበር፡፡ (ያኔ፣ የሕዝብ ሀብት ዘረፉ ይባሉ የነበሩትና በወያኔ/ኢሕአዲግ አባላት ይባረሩ የነበሩት “ደርግ/ኢሠፓዎች ቢበዛ ሠላሳ ሺህ ብር ቪላ ቤት የሠሩ፣ ወይም ደግሞ ባለሦስት ክፍል ዛኒጋባ የቀለሱት “ሚስኪኖች” ነበሩ፡፡) ዛሬ ታሪኩ ተቀይሯል፡፡ ከባለአምስት ፎቅ ሕንፃ በታች ያለው ሹም ካለ “ፋራና ፈዛዛ” ብቻ ነው፡፡</div>
<div></div>
<div>በጥቅምት 14 ቀን 1989 ዓ.ም “አቶ ታምራት ላይኔ ከመከላከያ ሚኒስትርነቱና ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርነቱም ሲወገድ፣” የጠቅላይ ሚኒስትር መለሰ ዜናዊ ጽ/ቤት የሰጠው መግለጫ እንደሚለው ከሆነ፣ “አቶ ታምራት በምግባረ-ብልሹነት ተወወግዷል” ነው፡፡ “ጥይት ያላንበረከከውን ታጋይ፣ ስኳር አንበረከከውም!” ተብሎ ነበር (አዲስ ዘመን፣ ጥቅምት 15/1989 ዓ.ም፣ ገጽ-1)፡፡ ከወራት በኋላ፣ አቶ ታምራትና ወይዘሮ ሻዲያ ሀሰን ከነግብረ-አበሮቻቸው ተከሰው ፍርድ ቤት ሲቀርቡም፣ የተከሰሱበት ወንጀል “ያላግባብ ሃብት በማጋበስ” የሚል ነበር፡፡ በዚሁ ወንጀልም መሠረት፣ አቶ ታምራት ላይኔ በ14 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ የከፍተኛው ፍርድ ቤት ወሰነበት ተባለ፡፡ (“ተባለ” የምለው ሆን ብዬ ነው፡፡) አቶ ታምራት እስሩን ሳይጨርስ በ2000 ዓ.ም (በቅንጅት ታሳሪዎች ግርግርና በነፕሮፌሰር ኤፍሬም ይስሃቅ ተለማማጭነት ተፈታ፡፡ በቅርቡ ደግሞ ሪፖርተር ጋዜጣ እንደዘገበው ከሆነ፣ በስዊዝ ባንክ አስቀምጦት የነበረው ከ5 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገንዘብ ለኢትዮጵያ መንግሥት ተመልሷል፡፡</div>
<div></div>
<div>ከላይ እንደገለጽኩት፣ በታኅሣሥ ወር 1989 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ አቶ መለሰ ዜናዊና የገመናኛ ብዙኃኖቻቸው “ሙስና” የሚለውን ቃል ለፖለቲካ ፍጆታ መጠቀም ጀመሩ፡፡ “ሙስና” እና “የፀረ-ሙስና ኮሚሽን” የሚባሉት ቃላት ሕግ ተረቆላቸው፣ ጽሕፈት ቤት ከፍተው፣ “ኮሚሽነርም” የሚባል ሹም ታውቆላቸው መቀፍደድና ማስቀፍደድ ተከተለ፡፡ “ሙስና ሰበብ በቁጥጥር ስር” መዋል የተጀመረው በግንቦት 16/1993 ዓ.ም ነው፡፡ ለማቋቋም የሚያስችለው ውይይት በግንቦት 10/1993 ዓ.ም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተካሂዶ፣ ሳምንት ሳይሞላው በግንቦት 16/1993 ዓ.ም ሕግ ሆኖ ፀደቀ፡፡ ወቅቱ በጥድፊያ የተሞላና “የሕወሀት/ወያኔ ስንጠቃ በመቐሌና በሂልት አዲስ አበባ በይፋ የታወቀበት ጊዜ ነበር፡፡ ወያኔ ለሁለት መከፈሉም አርግጥ ነበር፡፡ ይሄንን ሕግ ከሚያረቁትም ሰዎች መካከል የዛሬው የገቢዎችና ጉምሩክ አቃቤ ሕግ አቶ እሸቱ ወልደ ሰንበት ነበረበት፡፡ መቀሌና ባህር ዳር ላይ ምቹ ሆቴሎችን ይዘው “የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና” ሕጉን ማርቀቅ ጀመሩ፡፡(አቶ እሸቱ በ1999 ዓ.ም እንደነገረኝ ከሆነ፣ ሕጉ ባስቸኳይ የተረቀቀው በአቶ ወረደወልድ ወልዴ ትዕዛዝ ሲሆን፣ በአቶ መለሰ ዜናዊ ቀጭን መመሪያም እንደተከወነ ነግሮኛል፡፡ በዚህም መሠረት፣ ሕጉ በጥቂት ሳምንታት ውስጥ ተረቀቀና ወዲያው ጸደቀ፡፡ በግንቦት 19/1993 ዓ.ም የፍትሕ ሚኒስትሩና የፀረ-ሙስና ኮሚሽነሯ ወይዘሮ እንወይ ገብረ መድህን፣ “ሕዝቡ የሙስና ወንጀልን ያለፍርሃት እንዲያጋልጥ” ጥሪ ካቀረቡ በኋላ፣ “የፀረ-ሙስና ሕጉ በቂ ጥበቃ” የሚያደርግለትም መሆኑን መግለጽ ጀመሩ፡፡ ከሁለት ቀናትም በኋላ የሙስናው ቲያትር (ገቢር አንድ) መጋረጃው ተገልጦ መታየት ጀመረ፡፡</div>
<div></div>
<div>በዕለተ ዐርብ ግንቦት 21/1993 ዓ.ም፣ የፀረ-ሙስና ኮሚሽን፣ “ከፍተኛ የሙስና ሴራ ውስጥ እንደሚገኙ በተጠረጠሩት ባለሥልጣነትና ነጋዴዎች ላይ ርምጃ ወሰድኩ” ሲል ለፈፈ፡፡ የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ መምሪያም በበኩሉ፣ በሙስና ወንጀል ተጠርጣሪ የሆኑትን የመንግሥታዊ ተቋማት ኃላፊዎችና ነጋዴዎችን በቁጥጥር ሥር ማዋሉን ገለጸ፡፡ በዚህም መሠረት፣ አቶ ስየ አብርሃ (ባለስልጣን)፣ አቶ አሰፋ አብርሃ (ባለሥልጣን)፣ አቶ ምህረትአብ አብርሃ (ነጋዴ)፣ አቶ ፍስሃ አብርሃ-ነጋዴ(አራቱን ወንድማማቾች) እና አቶ ቢተው በለይን፣ አቶ ኃይሉ ለገሠን፣ አቶ ሙሉጌታ ገብረ መድህንን፣ አቶ በለጠ አለማየሁን፣ አቶ ብርሃነ ጂጆን፣ አቶ ሶፊያ ኢብራሂምን (እነዚህ ሁሉ በአንድ ወቅት ስንቱን የሚያንጰረጵሩ የወያኔ ሹማምንት ነበሩ) በቁጥጥር ሥር ዋሉ፡፡</div>
<div></div>
<div>ከነጋዴዎቹም መካከል አቶ ምንውዬለት አጥናፉና አቶ አበባው ደስታ (የስታር ቢዝነስ ግሩፕ ባለቤቶች)፣ አቶ ወርቁ መግራ፣ አቶ አበባው ገላዬ፣ አቶ አስናቀ ጀምበሬ፣ ወ/ሮ አጀብነሽ ሳምሶን፣ ወ/ሮ የሺሃረግ ዘውዴ፣ ሚ/ር ገራርድ ማይክል ሞላይን እና ሌሎችም ነበሩ፡፡ አርብ ማታ በዜና ማሰራጫዎች ተነግሮ፣ ቅዳሜና እሑድን ተራው ሕዝብ እንዲሰልቀው አደረጉት፡፡ ሰኞ፣ ግንቦት 24/1993 ዓ.ም ደግሞ ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡ ማክሰኞ ግንቦት 25/1993 ዓ.ም ደግሞ ኮሚሽነሯ ወ/ሮ እነወይ ገብረ መድህን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ድረስ ሄደው “የፀረ-ሙስና ምንጠራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል” ተናገሩ (አዲስ ዘመን፣ ግንቦት 17፣ 18፣ 22፣ 25፣ አና 27 ቀን 1993 ዓ.ም፣ ገጽ-1 ላይ ማግኘት ይቻላል)፡፡ የአሁኑም ክስተት፣ ትዕይነተ-ቲያትር ወሙስና (ገቢር ሁለት) እንደማለት ይመስላል፡፡</div>
<div></div>
<div>በሰኔ 1/1993 ዓ.ም በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት 1ኛ ወንጀል ችሎት ክስ የተመሰረተባቸው አቶ ስየ አብርሃ፣ በመሃል ዳኛዋ ወ/ት ብርቱካን ሚዴቅሳ ውሳኔ መሠረት በዋስ እንዲለቀቁ ተደረገ፡፡ በዚያው ዕለትም፣ የፌዴራል ፖሊስ የምርመራ ማስተባበሪያ ዋና ክፍል የፍርድ ቤቱን ትዕዛዝ ጥሶ ተከሳሹን አቶ ስየ አብርሃን በድጋሚ አሠራቸው (አዲስ ዘመን፣ ሰኔ 2/1993 ዓ.ም፣ ገጽ-1 እና 5)፡፡ ይህንኑ የአቶ ስየ አብርሃንና የፌዴራል ፖሊስን ግብግብ ተከትሎ በተፈጠረው ውዝግብ የተነሳ፣ በወቅቱ የፍትሕ ሚኒስትር የነበሩት አቶ ወረደወልድ ወልዴ ተከሰው በሁለት ዓመታት “የፈተና ጊዜ ገደብ” ፍርድ ተጣለባቸው፡፡ ጉዳዩ ከከፍተኛው ፍርድ ቤት አልፎም ወደ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በይግባኝ ተወስዶ ነበር፡፡ ጠቅላይ ፍርድ ቤቱም ከፍተኛ ውዝግብ ውስጥ ከብቶ ነበር፡፡ በሰኔ 16/1993 ዓ.ም ኮሚሽነሯ ወ/ሮ እንይ በመገናኛ ብዙኃን ቀርበው (አይናቸውን በጨው አጥበው) እንዲህ አሉ፤ “መንግሥት ባለፉት ሰባት ዓመታት ውሰጥ ሙስናን መዋጋት ሁኔታዎችን ሲያመቻች መቆየቱን” ገልጸው ሲያበቁ፣ “በሙስና ወንጀል የተጠረጠረና የተያዘ ሰው፣ የዋስትና መብት የለውም፤” አሉ፡፡ “ምክንያቱም፣” አሉ ኮሚሽነሯ፣ “ምክንያቱም፣ ተጠርጣሪው የዋስትና መብቱ ከተከበረለት፣ ተጠርጣሪው ሊያመልጥ ስለሚችል ነው፤” ሲሉ አከሉበት፡፡</div>
<div></div>
<div> አስከትለውም፣ “በሙስና የተከሰሰ ሰው የዋስትና መብት እዳይኖረው የሚከለክል ሕግ መረቀቁንና በቅርብም ሥራ ላይ ይውላል፤” ሲሉ ነበር ያለባበሱት (አዲስ ዘመን፣ ሰኔ 17/1993 ዓ.ም፣ ገጽ-1)፡፡</div>
<div>የአሁኖቹም ተጠርጣሪዎችና የታሰሩበት ዕለት፣ የፍርድ ቤት አቀራረባቸው፣ እንዲሁም ተከሳሾቹ እያሰሙት ያለው አቤቱታ በ1993 ዓ.ም አቶ ስየ አብርሃና ባለቤታቸው እንዲሁም ሦስት ወንሞቻቸው ያሰሙት ከነበረው እምብዛም ልዩነት የለውም፡፡ (ቀንቀሎ ስልቻ፤ ስልቻም ቀንቀሎ ነው፡፡) ይሄንን አባባል ይበልጥ የሚያጠናክረው የናዝሬት ጉምሩክ ኃላፊ የተባሉት የአቶ ተመስጌን ጉልላትን “በጋንቤላ በኩል ወደ ደቡብ/ሱዳን ሊሸሹ ሲሉ ተያዙ!” የሚለውን ዜና በሐምሌ 12/1993 ዓ.ም ከወጣው የአቶ ሳሚ ዩሱፍ አኳኋን ጋር ካስተያዩት ነው፡፡ በወቅቱ አቶ ሳሚ በርካታ ብርና ዶላር ይዘው በሶማሊያ በኩል አድርገው ጂቡቲ ከገቡ በኋላ በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ፖሊስ ገልጾ ነበር፡፡ የአቶ ሳሚ ዩሱፍ ወንጀል እጅግ አስደንጋጭ ነበር፡፡ (ልክ የሌ/ኮሎኔል ሃይማኖት 61 ሚሊዮን ብር ግምት ያለው ሰነድ ይዛ ልታሸሽ ስትል ያዝናት እንደሚለው ዜና፣ የአቶ ሳሚም ወንጀል ለሰሚውም የሚቀፍ ነበር፡፡) አቶ ሳሚ ቤሳ-ቢስቲን ሳይኖረው/ሳያሲዝ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 22 ሚሊዮን ብር በሕገወጥ መንገድ ከተበደረ በኋላ፣ (ያን ጊዜ፣ “የስኳር ድጋፍ ሰጪ” ከሚባለው ተቋም) “156,000 ኩንታል ስኳር ያለጨረታ ገዝቶ አየር-ባየር ከሸጠ በኋላ ዕዳውንም ሳይመልስ በሶማሊያ በኩል ሊኮበልል ሲል ተያዘ፤” የሚል ነበር (አዲስ ዘመን፣ ሐምሌ 12/1993 ዓ.ም፣ ገጽ-1)፡፡ ዛሬም፣ አቶ ተመስገን የሚኮበልሉበት አቅጣጫ ተቀየረ እንጂ ኩብለላን ነው የመረጡት፡፡ ከሕግ ፊት ሸሽተው እንዳልሆነ ይታወቅልኝ፡፡</div>
<div></div>
<div>እና፣ አቶ ሳሚ ዩሱፍም ሆኑ አቶ ተመስጌን ጉልላት ከምንድነው የሸሹት? የሚል ጥያቄ መነሳቱ አይቀርም፡፡ በቀጥታ ወደ መልሱ ከመግባቴ በፊት፣ በግንቦት 4/2005 የወጣው ሪፖርተር ጋዜጣን ሳነብ ያገኘሁትን መረጃ ላካፍላችሁ፡፡ እንዲህ ይላል፤ “እነዚህ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ከመዋላቸው በፊት ላለፉት ሦስት ዓመታት ክትትልና ምርመራ ሲደረግባቸው እንደነበረ የታወቀ ሲሆን፣ <b><i><span style="text-decoration: underline;">ከመያዛቸው ሁለት ቀናት በፊት በመቀሌ ከተማ ከሙስና ጋር በተያያዘ ጠንከር ያለ ውይይት መደረጉን</span> </i></b>ለማወቅ ተችሏል፡፡ ከዚህ ስብሰባም በኋላ ጥንቃቄ በተሞላበት እንቅስቃሴ” ማረ በላዎቹን በቁጥጥር ሥር ማዋል ተችሏል” -ይላል (ገጽ-37)፡፡ ትልቁ ቁምነገር ያለው የተሰመረበት ንዑስ ዐረፍተ ነገር ላይ ነው፡፡ በፌዴራል መንግሥቱ ዋና ከተማ የሚደረጉ ስብሰባዎችም ሆኑ ውይይቶች “ፍሬ-ከርስኪ” እንደሆኑና የመቀሌቹ ስብሰባዎችና ውይይቶች ግን “መሬት ጠብ የማይሉ” እንደሆኑ ያሳብቃል፡፡ በርግጥም ይህ ለምን ተደረገ ብሎ መመርመር ያስፈልጋል፡፡</div>
<div></div>
<div>የመቀሌዎቹ፣ በ1993 ዓ.ም በእነአቶ ስየ አብርሃም ላይ የእስር ትዕዛዙን የወሰኑት ከዚያው ከመቀሌ ነበር፡፡ አዲስ አበባ በወቅቱ ምቹ አልነበረችም፡፡ ከሚያዝያ 3-7/1993 ዓ.ም ድረስ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች አመጽና፣ አመጹንም ተከትሎ የነበረው ዝርፊያና ግድያ፤ እንዲሁም የደሕንነትና ኢምግሬሽን ዋና ሥራ አስኪያጅ የነበሩት አቶ ክንፈ ገብረ መድኅን በግንቦት 4/1993 ዓ.ም በመኮንኖች ክበብ መገደል (ወዘተርፈ) አዲስ አበባን የማትታመን ሥፍራ አድርጓት ነበር፡፡ ምርጦቹ ሕወሀቶች መቀሌ ላይ ተሰብስበው፣ “የአቦይ አብረሃ ልጆችና ግብረ-አበሮቻቸው ይታሰሩ!” ቢሉ አያስደንቅም ነበር፡፡ ምክንያቱም፣ ከአዲስ አበባ ይልቅ “መቐለይ” ለሕወሀት ምቹ የቁጥጥር ዞን ስለሆነች ነው፡፡ አዲስ አበባ ላይ ስንቱ የእህት ድርጅት አባል ስለላና ብሰሳ እንደሚያደርግባቸው ስለሚያውቁም ነው መቐለይን የመረጡት (በተለይ ብአዴን)፡፡ ታዲያ “አሁን፣ በ2005 ዓ.ም ሚያዝያ ማለቂያና በግንቦት ልደታ ዋዜማስ መቀሌ ላይ ተሰብስቦ መወሰንን ምን ይሉታል?” የምትሉ እንደማትጠፉ እርግጠኛ ነኝ፡፡ አሁንም ቢሆን፣ አዲስ አበባ ውስጥ ሕዝቡ ባለፈው የቀበሌና የወረዳ/ክፍለ ከተማ ምርጫ እንደታየው ከሆነ ለወያኔ/ኢሕአዲግ ያለውን ስሜት በግልጽ አሳይቷል፡፡” ስለዚህም፣ ከፍተኛው ያገር ገዳይ መቐለይ ላይ ሸብ-ረብ ተደረገ፡፡</div>
<div></div>
<div>ሌላም ምክንያት አለው፡፡ የፌዴራል ዋና ኦዲተርን ሪፖርት ተከትሎ “ውስጣዊ ሴራዎች/Ineternal Conspirencies) መካሄደ ላይ ነበሩ፡፡ በ116 የፌደራል መንግሥቱ ተቋማት ውስጥ በተደረገው የኦዲት ምርመራ መሠረት፣ በ84 መ/ቤቶች ከ5.2 ሚሊዮን ብር በላይ ያልተወራረደ የጥሬ ገንዘብ ውዝፍ ተገኝቷል፡፡ ይህንን ገንዘብ ደግሞ በየመሥሪያ ቤቱ የአስተዳደርና ፋይናንስ ዋና መምሪያ ኃላፊዎች ሆነው እንዳሻቸው የሚያደርጉት የሕወሀት/ወያኔ አባላት ናቸው፡፡ ሰንደቅ ጋዜጣ በሚያዝያ 23/2005 ዓ.ም እንደዘገበው ከሆነ ደግሞ ችግሩ በይብጥ የሚጎላው በመከላከያ ሚኒስቴር ውስጥ ነው፡፡ 3.2 ቢሊዮን ብሩ ደብዛው የጠፋው በዚሁ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት ውስጥ ነው፡፡ ምናልባትም ደግሞ ከፍተኛዎቹን የጦር መኮንኖች የሚያነካካ ነው፡፡ ብዙዎቹ፣ በማረ በላነት ይታማሉ፡፡ በአንደ በጀት አመት ግን ይኼንን ያህል ገንዘብ ተመዝብሮ አያውቅም፡፡ ምናልባትም፣ አቶ መለሰ ዜናዊ ታመሙ (ሞቱ) የሚል የተምታታ ዘገባ በነበረበት የሰኔ/2004 ማለቂያ ላይ በስልጣናቸን አንቀጥልም በሚል ተስፋ-መቁረጥ ውስጥ የነበሩ አመራሮች ካቅማቸው በላይ አሽሽተዋል፡፡ ይሄንን ደግሞ የብአዴን መሪዎች በሚገባ አውቀውታል፡፡ ማወቃችንንም ያወቅነው በ11ኛው የኢሕአዲግ ጉባኤ ወቅት የአቶ በረከት ስምኦንንና የአቶ አዲሱ ለገሠን ቀና-ቀና ማለት አብጠርጥረን ስላየነው ነው፡፡</div>
<div></div>
<div>በዋናው ኦዲተር ሪፖርት አማካኝነት የብአዴን ሰዎች ራት ለመሆን የተዘጋጁት ሕወሀቶች ከጊ ጋር ሩጫ ጀመሩ፡፡ መቀሌ ላይ መሽገው ሁለት አባላቶቻቸውን “መናጆ” አድርገው በርካታ የብአዴን አባላትን ባላቸው የደሕንነትና የፀጥታ ዕዝ ሰንሰለት ተጠቅመው በቁጥጥር ሥር አዋሉት፡፡ እራት ሊያደርጋቸው ያሰበውን ብአዴንን፣ ሀሪፍ ምሳ አደረጉት፡፡ ብዘዎቹ የብዐዴን ሰዎች ሲታሰሩ “ችግር ይፈጥሩ ይሆናል የተባሉትም የፍትሕ ሚኒስትሩ አቶ ብርሀነ ኃይሉ፣ ሐሙስ ተወካዮች ምክር ቤቱ የሕግና ፍትሕ ቋሚ ኮሚቴ ሪፖርታቸውን ከቀረቡ በኋላ ከኃላፊነታቸው መታገዳቸውን አወቁት፡፡  ይህንንም ለማድረግ መቐለይ ላይ መሽጎ የነበረው “የትግራይ ሪፐብሊካን ፓርቲ” አመራር፣ የደሕነትና የፀጥታ ኃላፊዎችን ማዘዙ ብቻ በቂው እንደነበረ አልተጠራጠረም፡፡ በዕለተ አርብ፣ ግንቦት 2/2005 ዓ.ም መጋረጃው ተገልጦ “የሙስናው ወንጀልም ጉዳይ” ለሕዝቡ በሰበር-ዜናነት ተነገረው፡፡ (ሕዝቡ ግን የሚገርም ምላሽ ነበር የሰጠው፡፡ የፕሪሜር ሊጉና የሰውለሰው ድራማ ሲያልቅባቸው ጊዜ፣ “የሙስና ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር ዋሉ” የሚል ድራማ ሊያሳዩን ይፈልጋሉን? ሲል ተዘባበተባቸው፡፡ (ጎበዝ፣ ቸር እንሰንብት!)</div>
<div></div>
<div><b>በሳምናታዊው የ<span style="text-decoration: underline;">አዲስጉዳይ</span> መጽሔት ቅጽ 7፣ ቁ. 164 ላይ፤ </b>በግንቦት 1<b>0 ቀን 2005 ዓ.ም </b>(ገጽ 22-3)<b> የወጣ ነው::</b></div>
<div></div>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3329"     class="crp_title">የአዲስ ጉዳይ መጽሔት ርዕሠ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3201"     class="crp_title">በሙስና ተጠርጥረው የታሰሩት&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/420"     class="crp_title">ታስሮ የነበረው ኤርሚያስ አመልጋ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/705"     class="crp_title">የጁኔይዲ ሳዶን ወደ ኬኒያ መሰደድ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3148"     class="crp_title">የናዝሬት ጉምሩክ የህግ ማስከበር&hellip;</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=83274</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>Tower in the Sky (የሰማይ ላይ ግንብ) – የመጽሐፍ ግምገማ</title>
		<link>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3425</link>
		<comments>http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3425#comments</comments>
		<pubDate>Tue, 21 May 2013 14:45:42 +0000</pubDate>
		<dc:creator>ዘ-ህበሻ</dc:creator>
				<category><![CDATA[Amharic]]></category>
		<category><![CDATA[addis ababa]]></category>
		<category><![CDATA[business]]></category>
		<category><![CDATA[economy]]></category>
		<category><![CDATA[election]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopia]]></category>
		<category><![CDATA[Ethiopians]]></category>
		<category><![CDATA[export]]></category>
		<category><![CDATA[health]]></category>
		<category><![CDATA[immigration]]></category>
		<category><![CDATA[import/export]]></category>
		<category><![CDATA[market]]></category>
		<category><![CDATA[money transfer]]></category>
		<category><![CDATA[politics]]></category>
		<category><![CDATA[scholarship]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3425</guid>
		<description><![CDATA[የመፅሐፉ ርዕስ፡- Tower in the Sky (የሰማይ ላይ ግንብ) ደራሲ፡- ህይወት ተፈራ አሳታሚ፡- አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ የገፅ ብዛት፡- 437 የታተመበት ዘመን፡- እ.አ.አ. 2012 የመሸጫ ዋጋ፡- 74ብር በሰለሞን ኃይለማርያም ይህንን መፅሐፍ ሳነብ በልጅነቴ በአንድ ዕለት ሰንበት እናቴ እጄን ይዛ ወደ ቤ/ክርስቲያን ስትወስደኝ የተመለከትኩትን ልክ እንደፊልም ወደኋላ ወስዶ እንዳስታውስ አደረገኝ፡፡<div><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3375">የሚኒሶታው መድሃኔዓለም ሁለቱ&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3192">“በኢንቨስትመንት ስም የሚፈጸም&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1897">የጊዜው የኢትዮጵያ ጬኸት፤&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3226">የዓለም ህዝብ ሥጋትና በዚሁ ሥጋት&#8230;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/892">የአ.አበባው ሲኖዶስ ታዛቢዎች&#8230;</a></li></ul></div>]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/tower-in-the-sky-300x310.jpg"><img src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/tower-in-the-sky-300x310-290x300.jpg" alt="tower-in-the-sky-300x310" width="290" height="300" class="alignleft size-medium wp-image-3431" /></a> የመፅሐፉ ርዕስ፡- Tower in the Sky (የሰማይ ላይ ግንብ)<br />
ደራሲ፡- ህይወት ተፈራ<br />
አሳታሚ፡- አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ<br />
የገፅ ብዛት፡- 437<br />
የታተመበት ዘመን፡- እ.አ.አ. 2012<br />
የመሸጫ ዋጋ፡- 74ብር<br />
በሰለሞን ኃይለማርያም<br />
ይህንን መፅሐፍ ሳነብ በልጅነቴ በአንድ ዕለት ሰንበት እናቴ እጄን ይዛ ወደ ቤ/ክርስቲያን ስትወስደኝ የተመለከትኩትን ልክ እንደፊልም ወደኋላ ወስዶ እንዳስታውስ አደረገኝ፡፡ <iframe src="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/plugins/google-document-embedder/view.php?url=http%3A%2F%2Fwww.zehabesha.com%2Famharic%2Fwp-content%2Fuploads%2F2013%2F05%2FTOWER-IN-THE-SKY.pdf&hl=&gpid=1&embedded=true" class="gde-frame" style="width:100%; height:300px; border: none;" scrolling="no"></iframe>
<p class="gde-text"><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/05/TOWER-IN-THE-SKY.pdf" class="gde-link">Download (PDF, 134KB)</a></p></p>
<div class="crp_related"><h3>Related Posts:</h3><ul><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3375"     class="crp_title">የሚኒሶታው መድሃኔዓለም ሁለቱ&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3192"     class="crp_title">“በኢንቨስትመንት ስም የሚፈጸም&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/1897"     class="crp_title">የጊዜው የኢትዮጵያ ጬኸት፤&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/3226"     class="crp_title">የዓለም ህዝብ ሥጋትና በዚሁ ሥጋት&hellip;</a></li><li><a href="http://www.zehabesha.com/amharic/archives/892"     class="crp_title">የአ.አበባው ሲኖዶስ ታዛቢዎች&hellip;</a></li></ul></div>]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ethiopianreview.com/amharic/?feed=rss2&#038;p=83275</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
	</channel>
</rss>

<!-- Dynamic Page Served (once) in 0.357 seconds -->
