(ደጀ ሰላም፤ ጁላይ 28/2010)፦ ከአምስተኛው ፓትርያርክ ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ሲመት ማግስት ጀምሮ በቤተ ክርስቲያኒቱ የተነሣውን መከፋፈል ለማቆምና በአባቶች መካከልም የተፈጠረውን እስከ መወጋገዝ የሚያደርስ ልዩነት በእርቅ ለመጨረስ በተጀመረው እንቅስቃሴ ቅ/ሲኖዶስን ወክለው የሚወያዩት ልዑካን ከዚህ በፊት የዘገብናቸው ብፁዕ አቡነ በርተሎሜዎስ፣ ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ፣ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል፣ ብፁዕ አቡነ አትናቴዎስና ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ ሳይሆኑ ከሐምሌ ስድስቱ የቅ/ሲኖዶስ ጉባዔ ማግስት ስማቸው በየጋዜጣው የተጠቀሰው ብፁዕ አቡነ ገሪማ፣ ብፁዕ አቡነ አትናቴዎስ፣ ንቡረ ዕድ ኤልያስ አብርሃ እና መጋቤ ብሉይ ሰይፈ ሥላሴ ዮሐንስ ናቸው። የአሜሪካን አባቶችን ወክለው ደግሞ ብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ፣ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ እና ብፁዕ አቡነ ኤልያስ ይደራደራሉ ተብሏል።
አባቶችን የማደራደሩ ውይይት ይጀመራል
ደጀ ሰላም | July 28th, 2010We would like to hear your opinion.
Join Ethiopian Review's forum and post
your comments. Click here to join us.
If you are already a member, click here.
You must be logged in to post a comment.

