የአዜብ መስፍን የስራ ባልደረባ በታክስ ማጭበርበር ታሰሩ


መረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ


የቀድሞው የሕወሓት ታጋይ የኾኑት አቶ ዕቁባይ በርሄ አሁን ታክስ አልከፈለም ተብሎ ክስ የቀረበበትን የሜጋ ሥነጥበባት ማእከል በሥራ አስኪያጅነት ሲመሩ ነበር። ይኹንና እርሳቸው ይህ ድርጅት ታክስ አልከፈለም ተብሎ በተጠየቀበት በ1996 ዓ.ም በሐላፊነት ላይ አልነበሩም። የውስጥ ምንጮቻችን ዘገባ እንደሚጠቁመው በቅርቡ ከወይዘሮ አዜብ መስፍን ጋራ በፈጠሩት አለመግባባት ምክንያት “ታዛዥነት” ባለማሳየታቸው እስከ መሰዳደብ በመድረሳቸው ይህ ክስ ተደግሶላቸዋል ይላሉ የአዲስ ነገር የአዲስ አበባ ምንጮች።

እነዚሁ ምንጮች እንደገለጹት ወይዘሮ አዜብ መስፍን እና አቶ ዕቁባይ የነበራቸው የሥራ ግንኙነት “ነፋስ የማይገባበት” ነበር። ይህ በወይዘሮ አዜብ መስፍን ሥር የሚተዳደር ድርጅት ላለፉት ሰባት ዓመታት ታክስ ባለመክፈል ሲያጭበረብር ነበር በሚል የምርመራ መ፣ዝገብ ተከፍቶበታል። ለዚሁም ተጠያቂ ተደርገው በምርመራ ላይ የሚገኙት አቶ ዕቁባይ በርሄ ቀጣዩን ውጤት ለመስማት ፍርድ ቤቱ ለሚቀጥለው ሰኞ ቀጥሯቸዋል። [ሙሉ ዘገባውን ለማንብብ እዚህ ጋ ይጫኑ)