የአዜብ መስፍን የስራ ባልደረባ በታክስ ማጭበርበር ታሰሩ

አዲስ ነገር | October 17th, 2010

የቀድሞው የሕወሓት ታጋይ የኾኑት አቶ ዕቁባይ በርሄ አሁን ታክስ አልከፈለም ተብሎ ክስ የቀረበበትን የሜጋ ሥነጥበባት ማእከል በሥራ አስኪያጅነት ሲመሩ ነበር። ይኹንና እርሳቸው ይህ ድርጅት ታክስ አልከፈለም ተብሎ በተጠየቀበት በ1996 ዓ.ም በሐላፊነት ላይ አልነበሩም። የውስጥ ምንጮቻችን ዘገባ እንደሚጠቁመው በቅርቡ ከወይዘሮ አዜብ መስፍን ጋራ በፈጠሩት አለመግባባት ምክንያት “ታዛዥነት” ባለማሳየታቸው እስከ መሰዳደብ በመድረሳቸው ይህ ክስ ተደግሶላቸዋል ይላሉ የአዲስ ነገር የአዲስ አበባ ምንጮች።

እነዚሁ ምንጮች እንደገለጹት ወይዘሮ አዜብ መስፍን እና አቶ ዕቁባይ የነበራቸው የሥራ ግንኙነት “ነፋስ የማይገባበት” ነበር። ይህ በወይዘሮ አዜብ መስፍን ሥር የሚተዳደር ድርጅት ላለፉት ሰባት ዓመታት ታክስ ባለመክፈል ሲያጭበረብር ነበር በሚል የምርመራ መ፣ዝገብ ተከፍቶበታል። ለዚሁም ተጠያቂ ተደርገው በምርመራ ላይ የሚገኙት አቶ ዕቁባይ በርሄ ቀጣዩን ውጤት ለመስማት ፍርድ ቤቱ ለሚቀጥለው ሰኞ ቀጥሯቸዋል። [ሙሉ ዘገባውን ለማንብብ እዚህ ጋ ይጫኑ)




We would like to hear your opinion.
Join Ethiopian Review's forum and post
your comments. Click here to join us.
If you are already a member, click here.

You must be logged in to post a comment.