አንዳንድ ሃሳቦች ስለ ውሃ እና መብራት መጥፋት – ሄኖክ የሺጥላ


መረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ


ሄኖክ የሺጥላ

ያው እንደምታውቁት ኢትዮጵያ ግድብ እንጂ ውሃ የለም ። ሿ የሚል የውሃ ድምጽ ከጠፋ ቆየ ፣ አረ ተውት !

ድሮ ድሮ ሸራተን ርችት ሲተኮስ ነበር ሰው ጣራ ላይ ወጥቶ የሚያየው አሁን አሁን በቃ ድንገት አንድ ቡዋንቡዋ ለባቡር መንገድ ሲወጣ በስህተት ከፈነዳ በቃ ህዝቡ ከቦ ” ውሃ መጣ ውሃ መጣ ” ነው ። ውሃ ብርቅ የሆነባት ሀገር ሆናለች ። እደውም ከውሃ ዝናብ የመጣበት ቀን ይበልጣል።

በነገራችን ላይ አንድ በጣም ጥቁር ጉዋደኛ አለኝ እና ይሄ ወዳጄ በሚኖርበት አካባቢ ውሃ በተከታታይ ለ አምስት ቀን ጠፍቶ ነበር እናም እስኪ ምነው ይሄ ወዳጄ ጠፋ ብዬ ልጠይቀው ቤቱ ሄድኩኝ ፣ እናላችሁ ሀገር ሰላም ነው ብዬ በሩን አንኩዋኩቼ ስገባ ይሄ በጣም ጥቁር ወዳጄ አይኑ ላይ የተለደፈው አይን አር ፣ አረ ተውት ( አንተ ምነው አትታጠበውም እንዴ ? ) ስለው ፣ “ምን ባክህ ውሃ ከሄደ እኮ ሳምንት አለፈው” አለኝ ። እኔማ በቃ የሜዳ አህያ መስለከኝ አልፌህ ሄጄ ነበር አልኩት ። እንደውም ያ አልብቃ ብሎት “እስኪ ና እንውጣ እና ቁርስ እንብላ ” አይለኝም መሰላችሁ ?! ” ከማ ከኔ ጋ ? በል ዞር በል ደሞ አንተን ሊያድኑ ሲሉ ተሳስተው እኔን ዷ ! አረ አልሄድም ። ደሞ እሱስ ይቅር ቅርስ በማስኮብለል ቢከሱኝስ ? ለማንኛውም ውሃ እስኪመጣ ወይ ከቤት አትውጣ ወይ ካገር ውጣ ! ወይ ቆጥ ላይ ውጣ ! ወይ አይንህን አውጣ ! አልኩት
ለነገሩ ውሃ አልኩ እንጂ መብራቱም ያው ነው ፣ እኛ ሰፈር ጋሼ መብራቱ ብቻ ነው ያልሄዱት ( እሳቸውም አንድ ቀን በ አንቀጽ 39 እንደሚሄዱ ይገመታል )። እንጂ መብራት የተባለ ዘር ማነዘሯ ተነቃቅላ ነው የሄደችው ። እንደውም የሰፈራችን ሴቶች ” ባክሽ ዛሬ አይመጣም አስጭበት !” እያሉ የ ዔሌትሪክ ገመዱን ልብስ ማድረቂያ አድርገውታል ። መብራት ገንዘብ ተቀባዩ እንጂ መብራቱ መምጣት ካቆመ እኮ ቆየ።

ድሮ ድሮ ሰው ተስፋ ሲቆርጥ ” ሄጄ ዔሌትሪክ ነው የምጨብጠው!!! ” ይል ነበር ። አሁን አሁን እንደዚያ ብትል ” ሂድ ጨብጠው ፣ እንደውም አትልቀቀው መብራት ሲመጣ እንድናውቅ !” ነው የሚሉህ ። አይ መብራት ፣ ያፈር መብራት !

የሚገርመው ግን ሰው መብራት ሲሄድ ሳይሆን ሲመጣ ነው የሚጮኸው ! እንዴ ? ምንድን ነው ነገሩ ? ስንጣ ነው ወይስ ስናገኝ መጮህ ያለብን ? ስንፍጉን ወይስ ሲለግሱን ? ወይ እኛ ፣ እንቢ ስንባል ነው ሲፈቅዱልን መጮክ ያለብን ?

ለማንኛውም መብራትን ወስዶ ቻይናን ያመጣ ፣ ውሃን ወስዶ ግድብን ያመጣ አምላክ ይኑር !

ለነገሩ መብራት አልን እንጂ ኢትዮጵያ ምን ያልሄደ ነገር አለ ። እንደውም አንድ አባት ጫት እየቃመ ያስቸገረ ልጃቸውን ” አንተ ልጅ ሉሲ እንኩዋ ዞር ዞር ብላ መጣች። አክሱምም የፓስታ ሽታ ደብሮት ይኸው አሁን ከበሮ ያዳምጣል አንተ ግን መቼ ነው እንደ ሰው መነቃነቅ የምትጀምረው አሉት ። ነገርን ነገር ያነሳዋል እንዲሉ ፣ ዔርትራዊያኖች ከኢትዮጵያ የተገነጠሉት በሲና በርሃ በኩል እስራዔል ለመግባት ነበር እንዴ ? እኛ እኮ ቢነግሩን ፈላሻ ናቸው ብለን በ አውሮፕላን እንልካቸው ነበር ። በእውነት ተሳስተዋል ። ደሞ ሰሞኑን ነው አሉ ” በ አማሪካ ያሚገኘው የኢሳያስ አፈወርቄ ቡድን ለ ጋሼ ኢሳያስ ሶስት ምርጥ ጫማ ገዝቶ ልኮለት ሶስቱም ልኩ በመሆኑ ጋሼ ኢሳያስ ተገርሞ ፣ ” እናንተ እንዴት ቁጥሬን አውቃችሁት? ” ሲላቸው ምን ቢሉት ጥሩ ነው ” 23 ዓመት ረግጠህ ገዝተከን ያንተ የጫማ ቁጥር ይጥፋን ወይ ? ። ወይ መዓልትይ !!! አለ ወያኔ !

እኔ እምለው ሰሞኑን ሃይለማርያም ደሳለኝ መንጃ ፍቃድ ሊያወጡ ሄደው ቪዥን ቴስት ወደቁ አሉ ፣ እና ምነው ሲባሉ ” አይኔን የመለስን ራእይ ለማየት ስለምጠቀምበት ነው !” አይገርምም ?

እስኪ ቸር ይግጠመን !