ዝም አይልም ሕዝቡ፤ በቃ ወዮላቸው!

ዐብይ ኢትዮጵያዊ | January 31st, 2011

ከ አቢይ ኢትዮጵያዊ ሥጋዊ-ወ-መንፈሳዊ

እንደ ክቡር ደራሲው ከበደ ሚካኤል፦

***”ኩራትና ትዕቢት የሞሉት አናት፤
ሰይፍና ጎራዴ የመቱት አንገት፤
አይገላገሉም እንዲህ በቀላሉ፤
እመሬት ላይ ወድቀው ሳይንከባለሉ።”***
ብለው እንደተረጎሙት፤
ይኑር ብዕራቸው ለዘላለም አይሙት።

ሕዝቡ ዝም አይልም ፦በቃ ወዮላቸው!!!

ያጋዚ-ወያኔን
ጠርጎ እስኪፈጃቸው።
ዝም አይልም ሕዝቡ
በቃ ወዮላቸው!!!
እናም፦
እኔም እንደአቅሚቲ ለዘመኑ ብዬው፤
በደም ለታጠቡት ትዕቢተኞች ይሄው።
ኢትዮጵያን ያረዱ የፈጁ ሕፃናትን፤
ሕዝቧን በአደባባይ ገድለው ያስገድሉትን፤
በጊዜ በሥልጣን በገንዘብ ቢ-ገዙ፤
የስጋ-ትል ሆነው ሺህ መግደል ቢያበዙ፤
የእግዚአብሔር ትዕዛዝ ነው ሥርፅ ነው መዘዙ፤
በሞት-ሲቃ ትግል በጣዕር እስኪያዙ።
አይጠፋም እሣቱ የተቀጣጠለው፤
ደሙ “ዋይ!!! ዋይ!!!” ይላል፦
ሲቃ ነው ያጀለው።
እቶን ነው እሣቱ ጠርጎ እስኪፈጃቸው፤
ሲዖል ነች ኢትዮጵያ ለመጨረሻቸው።
ከተሸሸጉበት ሳይጎለጉላቸው፤
በደም እንዳጠቧት እሷም ሳታጥባቸው፤
እንደሲዖል ማንጉግ :-
ሕዝቡ ሳይበላቸው፤
ዝም አይልም ቀልቡ
ያውቀዋል ውስጣቸው።
ዝም አይልም ሕዝቡ
በቃ ወዮላቸው!!!
የእግዚአብሔር ትዕዛዝ ነው ሥርፅ ነው መዘዙ፤
በሞት-ሲቃ ትግል በጣዕር እስኪያዙ።
ቱኒሲያ ቢነድ
ትግሉ የመን ቢነጉድ
ግብፅ ቢቀጣጠል
ከኤርትርያ ቢዘል
እግዚአብሔርም ሰምቶ ለሕዝቧ ይሰጣል፤
ኢትዮጵያን የነካት የሞት ሞት ይቀጣል።
የኢትዮጵያ አምላክ:-
እንዲያ ሲታገሳቸው፤
ዝም አይልም ሕዝቡ
በቃ ወዮላቸው!!!




We would like to hear your opinion.
Join Ethiopian Review's forum and post
your comments. Click here to join us.
If you are already a member, click here.

You must be logged in to post a comment.