2ኛ የፓኪስታን ዜጋ በጋምቤላ ሞተ

VOA | May 3rd, 2012

በጋምቤላ ክልል ታጣቂዎች በከፈቱት ጥቃት ቆስለው ከነበሩት ፓኪስታናዊያን አንዱ ትናንት ሕይወቱ ማለፉን በኢትዮጵያ የፓኪስታን አምባሣደር አስታወቁ፡፡

በዚህም መሠረት ጥቃቱ በተፈፀመበት ዕለት የተገደለውን ጨምሮ የሞቱት የፓኪስታን ዜጎች ቁጥር ሁለት ደርሷል፡፡

ቆስሎ የነበረው ፓኪስታናዊ ሕክምና ያገኝ የነበረው በመቱ ሆስፒታል እንደነበር ታውቋል፡፡

በጋምቤላ ክልል በሰፊ የእርሻ ልማት ስራ ላይ ከተሰማራው ሳዑዲ ስታር ዋና ጣቢያ አምስት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ባለፈው ቅዳሜ በደረሰው ጥቃት የአራት ኢትዮጵያዊያንና የአንድ ፓኪስታናዊ ሕይወት ማለፉ ይታወሳል።

አራት ፓኪስታናዊያንና አራት ኢትዮጵያዊያን ደግሞ ቀላልና ከባድ ጉዳት ደርሶባቸው እንደነበር ተገልጿል።

በሌላ በኩል ደግሞ ትናንት ፖኬዲ በምትባል ቀበሌ የመንግሥት ወገን የሆኑ ታጣቂዎች፣ መምህራንና ተማሪዎች ተገድለዋል ሲሉ አንድ የአካባቢው ነዋሪና በሌላ በኩል ደግሞ የጋራ እንቅስቃሴ ለአዲሲቱ ኢትዮጵያ የሚባለው ቡድን ዋና ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ኦባንግ ሜቶ ለቪኦኤ ገልፀዋል፡፡

ዝርዝር ዘገባዎቹን ያድምጡ

Play below

 

One Response to “2ኛ የፓኪስታን ዜጋ በጋምቤላ ሞተ”

  1. abesha says:

    አይ ህገረ እድልሰ



We would like to hear your opinion.
Join Ethiopian Review's forum and post
your comments. Click here to join us.
If you are already a member, click here.

You must be logged in to post a comment.