አንድ ዜና፤ ርዕዮት አለሙ ለሽልማት ተመረጠች


መረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ


በፍትህ ጋዜጣ አምደኛ ሆና በምትሰራበት ወቅት “አሸበርሽ” ተብላ የታሰረችው ርዮት አለሙ “ኢንተርናሽናል ውመን ሚዲያ ፋውንዴሽን” የተባለ ድርጅት የሚዲያ ጀግና ሲል ለሽልማት መረጣት።

ሽልማቱ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ራስን ለአደጋ አጋልጦ በጋዜጠኝነታቸው ለተጉ ሴቶች የሚሰጥ ሲሆን፤ ከርዮት አለሙ ጋር አንዲት የፓልስቲን እና አንዲት የአዠርባዣን ጋዜጠኞች ለሽልማቱ ተመርጠዋል።

እንደሚታወቀው ርዮት አለሙ በአሁኑ ግዜ የገንዘብና የእስር ቅጣት ተወስኖባት በቃሊቲ እስር ቤት የምትገኝ ሲሆን “አሸባሪ” ተብላ በተከሰሰች ግዜ ለማስረጃነት ከቀረቡባት መካከል የፎቶ ካሜራ እና በፍትህ ጋዜጣ ላይ ያሳተመቻቸው ፅሁፎች እና በፌስ ቡክ በኩል ሰዎች “ታግ” ያደረጓት በጠቅላይ ሚኒስትሩ ላይ የሚያላግጡ ምስሎች ይገኙበታል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የእስክንድር ነጋን ሽልማት ባለቤቱ ሰርካለም ፋሲል አሜሪካ ሄዳ መቀበሏ ተሰምቷል። (እየተከታተላችሁ ያላችሁት… ልላችሁ እኮ ምንም አልቀረኝም…!)

ጥርጣሬ

መንግስታችን “አሸባሪ” ያላቸውን በሙሉ በተለይ በአሜሪካ የሚገኙ አለም አቀፍ ድርጅቶች ጀግና እያሉ እየሸለሙ ይገኛሉ። አሁን አንዳች ነገር ጠረጠርኩ። በዚህ ብስጭት መንግስት አሜሪካ አሸባሪ ብላ የገደለችውን ቢላደንን እዛው ያለበት ድረስ ሄጄ የጀግና ሽልማት ልስጠው እንዳይል እየሰጋሁ ነው። እልህ ጩቤ ያስውጣል አይደል የሚባለው!

በመጨረሻም

ርዮት አለሙ እና ወዳጅ ዘመዶቿ እንዲሁም የሙያ አጋሮቿን በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ እላለሁ!