ጠቅላይ ሚኒስትርዬ ከሱብኝ

አቤ ቶኪቻው | June 19th, 2012

ትላንትና ከስንት ጊዜ በኋላ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትርዬን በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን አየኋቸው። ያኔ አበበ ገላው በዋሽንግተን ዲሲ ቆሌያቸውን ከገፈፋቸው በኋላ በቴሌቪዥን መስኮት ስናያቸው ለመጀመሪያ ጊዜ መሆኑ ነው። (በቅንፍ፤ እንደ ድሮ ጎረቤት ብንሆን ኖሮ በቴሌቪዥን መስኮት ሲጠፉብን በሳሎናቸው መስኮት ለማየት ሙከራ እናደርግ ነበር። ዛሬ ግን ሩቅ ሆንና ናፍቆታቸው ሲያስቸግረን ሰነበተ! ብዬ ሀሳቢነቴን ለመግለፅ እወዳለሁ።)

አረ እዝች ጋ ሳይረሳ ባለፈው ጊዜ የአዲስ አድማስ ጋዜጣ ሰዎች “አበበ ገላው ዋሽንግተን ዲሲ ያልሄደው በርካታ የኢህአዴግ ደጋፊዎች ስላሉ እነርሱን ፈርቶ ነው!” ብላችሁን ነበረ። ረስቼላችሁ፤ ሰውየው እኮ አንገታቸውን የደፉት በዋሽንግተን ዲሲ ነው።

ታድያ የዛን ጊዜ ያ ሁሉ የአንገት እና የቅስም ስብራት ያጋጠማቸው የጋዜጠኛ አበበ ገላው ንግግር ብቻ መስሏችሁ ከሆነ ተሸወዳችሁ።

ከውጪ የነበሩት የአካባቢው ኢትዮጵያውያን የተቃውሞ ጩኸትም “ምነው እግሬን በሰበረው!” አስብሏቸው ነበር። ውስጥ ደግሞ አበበ ትንታግ ሲጨመርበት…!  እና ታድያ አዲስ አድማሶች ይሄ ሁሉ ነገር በዋሽንግተን ዲሲ ሲከናወን ደጋፊዎቻቸው የት ሄደው ይመስላችኋል? “በልማታዊ ስራ ተወጥረው ነበር!” ብላችሁ ሳቄን እስቲ አብዙልኝ! “ምን አይነት አዲስ አድማስ መጣ ደሞ ባካችሁ!?”

በነገራችን ላይ አሁንም እርሳቸው እርም የላቸውም የቡድን ሃያ አገራት ስብሰባ ላይ ደግሞ ሊገኙ ሲሄዱ ነው ያየኋቸው። እንደኔ እንደኔ ይሄ ቡድን ምናምን የሚባል ነገር ቢቀርባቸው ይሻላል። በርግጥ ስብሰባ ሊናፍቃቸው አንደሚችል ጠረጥራለሁ።  ምን ችግር አለው ታድየ በፈለጉ ጊዜ የሚሰበስቡት በፈለጉ ጊዜ የሚበትኑት ፓርላማ አላቸው አይደል እንዴ…!?  እዛው እንደሚሆኑ ቢሆኑ ይሻላቸዋል እንጂ፤ ገና ለገና የፈረንጆቹ “ቡድን” አያልቅም እና እርሳቸው “በድን” እየሆኑ የሚመጡበት ምክንያት ምንድነው!?

የሆነ ሆኖ “ታንክ ተደግፈው መፅሀፍ የሚያነቡት ጀግናው ጠቅላይ ሚኒስትራችን” በአበበ ገላው ንግግር የተነሳ ለአንድ ወር ያህል ተሸማቀው እና ተሸምቀው ሲያበቁ ትላንት በቴሌቪዥን መስኮት ብቅ ብለዋል።

ታድያልዎ፤ ትላንት ሳያቸው ክስት ብለዋል። ምን ሆኑ!? እንዴ ጠንከር ይበሉ እንጂ ጠቅላይ ሚኒስትርዬ! ቀጣዩ ጩኸት እኮ እየባሰ ነው የሚመጣው! ታድያ ጠንከር ጠንከር ማለት አይሻልም ይላሉ? ቁጣ እና ጩኸት ይህንን ያህል የሚረብሽዎት ከሆነ ግን ዘዴውን ልንገርዎት…!? እሺ አይሉኝም እንጂ ዛሬውኑ ስልጣንዎን ልቅቅ አድርገው አዲስ አገራዊ መግባባት፣ አዲስ አገራዊ ምርጫ ማከናወን! አቤት ያኔ ጤናዎ ላይ ራሱ ምን አይነት መሻሻል አንደሚመጣ ያዩት ነበር።


20 Responses to “ጠቅላይ ሚኒስትርዬ ከሱብኝ”

  1. tazab says:

    አቦ አንተ አበበ ያሚሉህ ምነው ይሂንን ሰው ለቀቅ ብታድርገው እሱ ለራሱ brain tumor ሊፈነዳ ድርስዋል አህን ድግሞ አንጅቱን ልታፈንዳው ነው እንዲ

  2. keba says:

    what’s wrong with him? wow he lost wait not look well.I think he time has reached.

  3. tazabe says:

    ተከላይ ሚነስትሩ ከሱ ? ተ ፍ 2000 ብር ነው ኮ ለምን አየከሱም

  4. abbe says:

    አቤ ምነው ጠቅላይ ሚንስቴሩን ጥምድ አድርገኽ ያዝካቸው በ 99.6 ፕርሰንት ህዝብ የመረጣቸውን አባይን የደፈሩትን ደጋፊዎቻቸው ታንክ አና መድፍ አስድግፈው መጽህፍ ሲያነቡ የሳላዋቸውን የአፊሪካ መሪ ፈንክትህ ፈንክተ ጃርት የበላው ዱባ አሰመስልካቸው አኮ, ለነገሩ ይገባቸዋል ደግ አደረክ ጎሽ አቤ ይመችህ ሁሌም ሽሙጦችህ ይጥሙኛል

  5. Tazabi says:

    Why wasn’t my comment posted?? I leave you for your conscious if you only post the comments which support the writer of the article. Leave everything for your conscious if you have a pure and healthy conscious.

  6. Ethiopiyawi says:

    I thought losing weight is a positive thing…How do you guys think?

  7. gash Tesfa says:

    መለስ ገብቶታል:: ፊዚካል ያሳየውን ሁኔታ እያየን:: እንደዚህ ከስቶ እይቸ ኣላውቅም:: ኣበበ ኣላማውን መትቶአል:: እድሜ ለኣቤ ሞት ለዲክታተር

  8. TD says:

    መለስ ሲያቅታቹህ ካንሰር ያዘው የምትሉ አሉባልታን እንደ ፖለቲካ ፍልስፍና የተሞላባቹህ የማንቦ ጃንቦ ዲስኩሮች እንዴት ናቹህ? አሁንስ ፍራስትሬት አደረጋቹህ::

  9. koster says:

    Fascist Meles will not give power alive and willingly. He has lots of blood on his hand. Accepting the result/the will of the people in the 2005 election was the right moment to give up power and lead a respecteable life. Now he has no choice other than to kill as much Amharas (his allergic of Amharas for whatever reason), loot and then die in a disgracefull manner like other dictators before him.

  10. Kedir says:

    እናንተ “ጸረ ልማት ጋዜጠኞች” እባካችሁ ተዉን፤ የእናንተን “ጸረ ልማት ሚዲያ” ለማፈን ብሎ “ልማታዊው መንግስታችን” ባሳለፍነው አመት ብቻ 1.5 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ለወዳጃችን ቻይና ከፍሏል፡፡ ይሄ ማለት ጠቅላላ የኢትዮጵ መንግስት ሰራተኞች ለአባይ ግድብ እንዲከፍሉት የተጣለባቸው ግዴታ ማለት ነው፡፡
    ስለዚህ እባካችሁ በውጭ ያላችሁ ኢትዮጵያውያን: ምንም አይነት ነገር ስለኢትዮጵያ አታቅርቡ ካልሆነ በድህነት ልናልቅ ነው፤

  11. erkihun says:

    Thank you Tazabi. I have the same concern, what they post is the comment appreciating the so call Washington Poleticians, Tamagne, Elias, the newly emerging Abebe. “Ezihi gibu yemayibalu yasitesaseb dehawoch”. Who ever is against their openion will be labeled as “woyane”. They advocate democracy, in reality they are tyrants. The time is near for them to be rejected.

    Anonymous Reply:

    እርቅይሁን

    ስለማነው የምታወራው? ቲራንት ወይም ዲክታተር የሚባለው እኮ የመንግሥት ሥልጣን ለያዙት ነው:: So who are you talking about? The admin has the right to evaluate what is worth for the page. He will not be liable to post your rubbish words full of lie with out rhythm. There are thousands of bowed yes-men like Tazabi who are getting devastated by free politics on account of the recent Tsunami of words by Brave Abebe Gellaw that let the PM get squeezed to appear the muzzle of Zu-23 anti aircraft cannon.

    Don’t be advocate of the Beast that turmoiled Ethiopia. If you are real Ethiopian think of the abled, gifted,respected, and above all elected scholars that cal lead the country towards unity in diversity then fast prosperity.

    Enough is Enough don’t roar the roar of defunct Lion!

  12. Tazabi says:

    Since my earlier comment wasn’t posted, let me post my comment again. I think losing weight and to be skinny and slim is an indication for a fresh, strong, healthy and joyful person. I, myself have been trying to lose weight to be a healthy person. I thought the PM has become the only African leader to be recognized as a smart leader in Africa. Once again, he has displayed his world class leadership to be invited to attend in the G20 summit in Mexico. He seems to enjoy life and politics and these could enable him to live a peaceful and joyful life. He, thus appeared to be skinny, fresh and healthy. So, his losing weight is a positive thing.

  13. tukchau says:

    አቢ ይህንን ባንዳ ደህና አርገህ ስለህዋል!!!!

  14. bereket says:

    መለስ(ወያነ)ተባይ

  15. Anonymous says:

    Dictators always look good until the last minutes;

  16. FETEH AWOKE says:

    ሁሉም ማድረግ የሚችል አምላክ ዛሬም እንደ ይሁዳ ለንስሃ ዕድል እየሰጠው ነው። አለምንም ካለ የሰራውን ያገኛል። የዋልድባ ጣጣ ገና እየጀመረ ነው። ብዙ ብዙ እናያለን። እድሜና ጤና ይስጠን። ተጀመር እንጅ አላለቀም። እግዚያብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ።

    Abebe Reply:

    ኣሜን

  17. Anonymous says:

    ሙባረክ ሲሞት ነው ሰውየው የኒም ደርሱአል ያለው የአበበ እንዳለ ሆኖ.

  18. Anonymous says:

    How can we say Meles is a democrat as he is in power for two decades?Have u noticed that his body guards are from one ethnic group?Menegistu never did this in his life time.If he trust other Ethiopians would be offered to take part. Do u dictators think there is no Ethiopian to lead this country?



We would like to hear your opinion.
Join Ethiopian Review's forum and post
your comments. Click here to join us.
If you are already a member, click here.

You must be logged in to post a comment.