የመለስ ዜናዊ ጤንነት ጉዳይ (ጀርመን ራዲዮ)

ዶይቸ ቬለ | July 17th, 2012

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ ታመው ቤልጅየም መዲና ብራስልስ በሚገኝ ሴይንት ሉክ በተባለ ሆስፒታል ሕክምና እየተደረገላቸው መሆኑን በኢንተርኔት የተለያዩ ምንጮች ዘግበዋል። ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ካለፉት ጥቂት ቀናት ወዲህ በአዲስ አበባ በይፋ አለመታየታቸው፡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውይይትም ሆነ ትናንት በተጠናቀቀው የአፍሪቃ ህብረት ጉባዔ ላይ አለመገኘታቸው ብዙ እያነጋገረ ነው። ስለዚሁ ጉዳይ በአዲስ አበባ የሚመለከታቸውን የመንግሥት ባለሥልጣናት ለማነጋገር ያደረግነው ጥረት አልተሳካልንም፤ በብራስልስ የሚገኘውን የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስተያየት ለማግኘት በኢሜይል ብንጠይቅም ዜናው ውሸት እና የተሳሳተ ነው በሚል ያቀረብነውን ጥያቄ ሳይቀበለው ቀርቷል። በመሆኑም፡ ብራስልስ የሚገኘው ወኪላችን ገበያው ንጉሤን ጠቅላይ ሚንስትር መለስ በዚያ ሕክምና እያደረጉ ነው ስለመባሉ በበኩሉ የሰማው እንዳለ ጠይቄው ቀጣዩን መልስ ሰጥቶኛል። … [ያዳምጡ]

Play below

 

2 Responses to “የመለስ ዜናዊ ጤንነት ጉዳይ (ጀርመን ራዲዮ)”

  1. hagere says:

    ዋናው ትልቁ ቁም ነገር አበበ ገላው በሽታውን ቀስቅሶበት መታመሙና መንገላታቱ ነው እንጂ ለምን ገደል ገብቶ አይታከምም ይሀ ነፍሰ ገዳይ ምንም በሽታ የለበትም የሱ በሽታ እንደውሃ ያፈሰሰው የድሃ ህዝብ ደም ያስከተለበት የመንፈስ መረበሽ ነው

  2. Anonymous says:

    ይህን ያሂል ለአንድ ሰው ኖር ሞተ ሚንዲነው ለዉቱ



We would like to hear your opinion.
Join Ethiopian Review's forum and post
your comments. Click here to join us.
If you are already a member, click here.

You must be logged in to post a comment.