ፍትህ ጋዜጣ እንዳትሰራጭ ታገደች

EthiopianReview.com | July 21st, 2012

(ፍትህ – ተመስገን ደሳለኝ) በትላ ንትናው ዕለት ለስርጭት መብቃት የነበረባት ፍትህ የጠቅላይ ሚንስትሩን መታተም ተከትሎ በተፈጠረው የስልጣን ትግል እያሸነፈ በመጣው አክራሪ ሀይል ተስተጓጉላ የነበረ ቢሆንም በማግስቱ እንድትታተም ተፈቅዷል ተብሎ ታተመች፡፡ ትላንት ከምሽቱ 2 ሰዓት ላይም ሙሉ በሙሉ ታትማም አለቀች፡፡ ነገር ግን አንባቢያን እጅ ልትደርስ አልቻለችም፡፡ ምክንያቱ ደግሞ (በዛው ኃይል ትዕዛዛ ይመስለኛል) በአቃቢ ህግ ብርሃኑ ወንድምአገኝ ‹‹ለሀገር ደህንንት የሚያሰጋ ዘገባ በጋዜጣው ላይ መታተሙ መረጃ ስለደረሰን እንዲታገድ ወስነናል›› በሚል የተፈረመ የዕግድ ደብዳቤ ማተሚያ ቤቱ እንደደረሰው ገለፀልን፡፡ በዚህም ምክንያት በአሁኑ ሰዓት 30 ሺህ የፍትህ ጋዜጣ እትም በብርሃና ሰላም ማተሚያ ቤት ተቆልፎበት ይገኛል፡፡

…እንዴት ነው ነገሩ? ‹‹ትሻልን ፈትቼ ትብስን አገባሁ›› እየሆነ ነው? ይህ ሁኔታ ወደስልጣን እየመጣ ያለው ሀይል የባሰ እንደሆነ ምልክት እያሳየስ ይሆን? ለማንኛውም መጨረሻውን አይተን የራሳችንን እርምጃ እንወስዳለን፡፡

(ማተሚያ ቤቱ ለጋዜጣው ዝግጅት ክፍል የላከውን ደብዳቤ ከስር ይመልከቱ)


3 Responses to “ፍትህ ጋዜጣ እንዳትሰራጭ ታገደች”

  1. Eth says:

    የፍትህ ሚኒስቴር ሳይሆን “የአፈና ሚኒስቴር” ነው::

  2. Yigermal says:

    Dear Moderator:

    Please delete the previous two comments and post this one–

    It is surprising!! Let us only hope that Aiga Forum won’t be the only news outlet allowed both in Diaspora and at home. In its recent article on optimizing the trinity of politics, it argues that modern politics emanates from instinct whereas primitive politics traces its origin to principles. Judging from its philosophy, Aiga belongs to the later :) This is not joke. Here is Aiga’s own statements:
    Aesop 22/07/2012-The major difference between modern and primitive politics is that the former is driven by instinct while the latter is guided by principles. Modern politics has three principles: equality, fraternity and liberty.

  3. molla says:

    የማወቅ መብታችን ታፍኖአ



We would like to hear your opinion.
Join Ethiopian Review's forum and post
your comments. Click here to join us.
If you are already a member, click here.

You must be logged in to post a comment.