የኢትዮጵያ ውርስና ቅርስ ማሕበር ሁለተኛ ክብረ በዓል/ፌስቲቫል በደማቅ ሁኔታ ተጠናቀቀ
የኢትዮጵያ ውርስና ቅርስ ማሕበር ከጁላይ 27 እስከ ጁላይ 29, 2012 ድረስ በጆርጅ ታውን ዩኒቨርስቲ ውስጥ ሁለተኛውን ክብረ በዓል በደማቅና በተሳካ ሁኔታ አካሄዷል። በዚህ ዝግጅት ላይ ስፍር ቁጥር የሌላቸው ኢትዮጵያዊያን የተሳተፉ ከመሆኑም በላይ በተላይ የልጆች ተሳትፎ እጅግ የጎላ ነበር። በዝግጅቱ ላይ የተለያዩ ዝግጅቶች የቀረቡ ከመሆናቸው በላይ ከብዙ በጥቂቱ የእግር ኳስ ጨዋታ፣ የሩጫ ውድድር፣ የባህል ሙዚቃ፣የመጽሃፍ ምረቃ፣ ይገኙበታል።
የዘንድሮ የክብር እንግዳ ብጹዕ አቡነ መልክጻዲቅ ሲሆኑ አባታዊ የሆነ ምክራቸውንና አበረታች መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። በተለይም በመዝጊያው ዝግጅት ላይ ታዋቂውና ጀግናው ጋዜጠኛ አበበ ገላው ተገኝቶ ታዳሚውን በሙሉ ያነቃነቀ በአፈና አገዛዝ በመማቀቅ ላይ ለሚገኘው ለኢትዮጵያ ሕዝብ ነጻነት እንደሚያስፈልገው ጥሪውን በድጋሚ አቅርቧል። ከዚህም በላይ ታዋቂና አገር ወዳድ ከሆኑት ድምጻዊያን መካከል ሻምበል በላይነህ፣ ጸሃዬ ዮሐንስና አብዱ ኪያር ተገኝተው የአገር ፍቅርና ብሔራዊ ኩራትን የሚያንጸባርቁ ታላቅ መልዕክት ያላቸውን ዘፈኖቻቸውን ተጫውተዋል። አርቲስት ታማኝ በየነም ተገኝቶ ቀስቃሽ መልዕክት አስተላልፏል።
በዚህ ክብረ በዓል ላይ ኢትዮጵያዊያን እንደዚህ በነቂስ በመውጣት የአገርና የወገን ፍቅር እንጅ አላፊ ጠፊ ገንዘብ እንደማይገዛቸው ለወያኔ/አላሙዲ ተላላኪዎች አስፈላጊ መልዕክት አስተላልፈዋል። በዲሲው የአላሙዲ ፌስቲቫል ላይ ከ 5 ሚሊዮን ዶላር በላይ የተረጨ ቢሆንም ዝግጅቱ በተመልካች ድርቅ ተመቶ እንደነበርና ወያኔዎች ለአሳሳች ፖሮፓጋንዳ እንዲያመቻቸው እስቴዲዮሙ ውስጥ ኢትዮጵያዊ ያልሆኑ ሰዎችን ሰንደቅ አላማ አስይዘው፣ አለክፍያ አስገብተው ሲያስተናግዱና ሲያሽሞነሙኑ እንደነበር ይታወሳል። እዚህ ክብረ በዓል ላይ ግን በዋናነት የተገኙት ኢትዮጵያዊያን ሲሆኑ ጥቂት ጥሪ የተደረገላቸው ኢትዮጵያዊ ያልሆኑ እንግዶችም ተገኝተዋል። “ብዙ ከመስማት አንዴ ማየት ይሻላል” እንደሚባለው እራሳቸው አስረጅ የሆኑትን ከዚህ በታች የተለጠፉትን ፎቶግራፎች ይመልከቱ።







እጅግ በጣም የተሳካና ያማረ ዝግጅት ነበር። ኢትዮጵያውያን በአንድነት ተገኝተው የወያኔን የውድቀት መጀመሪያ ያሳዩበት ነበር ለማለት ይቻላል። ኢትዮጵያዊነት ሲሞገስ፣ሲከበርና እንዲሁም ኢትዮጵያውያን በሕብረት ሲቆሙ የሚበግኑና የሚያዝኑ ወያኔዎች ብቻ ናቸው።
I am very much satisfied with the accomplishment of EHSNA. Every Ethiopian was welcomed and accepted. Most importantly, the children were giver prominent role and front seats. I would like to thank everyone who made this celebration a success.
ደስ ይላል ያገሬ ሰው እንደዚሁ ሳየው.መልኩና ቅንዸንው ቅርጹና ስብእናው ዋህ ይላል.አድነትና ቅንዽት አንድ ሲሆን ጥላው ኤትዮጵያ ናትና በዛ እናምን የወያነ ምናሙኑ ትጨርሰዋል.
ውብ ነው ቀዩ
አረንጋዴው መልኩ
ብጫ ቀለም ብቻ አይደልም
ቅርስናና ውርስ
ስው ሆንኩ አሁኑ..
ሰው ሳይ ሰው ስይናፍቅጝ.
ህዝብ ለህዝብ ሳይቅጝ .
ከረምኩ.
መላ አገጝሁ አሁን በሞትኩ..አልኩ..
ወያነ ሳይለቅስ ብሩዘል ተጝቶ
ውሃ ስጥግ ሲል ሰማሁ
ወያነ በአልጋ..
ይህ ህዝብ ስደምቅ
ለተራበ ወያነ አስጝቶ..
ማቅ ይዞ ምሀረት ሲጠይቅ
ይሀ ማልዳ ባንዳ
መሬት ይዘረጋ
ውጋው በዛንዻ..
አቤት ስይምር
ወያነ ሲሞት
ኤትዮጵያ ስትወልደ ገና..
ዝግዽት ወደ ሃገር
ያ.. ጨለማ ሲወድቅ..
እንካን እዚህ ደርስን
በዛ ተጠነቀቅ..
ፍርሃቴ አርዽቶ
የናጽነት ወጣትኔተ አድጎ.
ወያኔ ኢትዮጵያ ህዝብ ላይ የሚሰራው ግፍ የሚያበቃበት ጊዜ የደረሰ ይመስለኛል፡፡ የህዝቡ ለቅሶ ብቻ እንኳንስ መለስን ማሳመም አይደለም ገና አንድ በአንድ እንደገለባ ይበናሉ፡፡እናንተ በውጭ የምትኖሩ ኢትዮጵያውያን የታፈነ ድምፃችንን ለአለም አስተጋቡልን በዘር በሀይማኖት ሳትከፋፈሉ ልክ እንደኛ እንደመገናኛ ልጆች፡፡ ፍልፍሉ ነኝ ከመገናኛ |በነገራችን ላይ ፍልፍሉ ማነው ብለው ቢያጠኑ ኮሜዲያኑ ፍልፍሉ አለመሆኑን ወያኔ ደደቦች እንዲገነዘቡልኝ እፈልጋለሁ፡፡|