ከፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም ከነጻነት ለሃገሬ
ለአሜሪካ ድምጽ በቅርቡ በስጠሁት ቃለ ምልልስ ላይ በኢትዮጵያ ሕገ መንግስት መሰረት ጠቅላይ ሚኒሰተሩ በህመም፤ በእክል በሞት በአካለ ጉዳት በተለያዩ ሰበቦቸ በሰራው ላይ መገኘት ባይችል የስልጣን ዝውውሩ አንደት ይሆናል የሚል ጥያቄ ቀርቦልኝ ነበር ነበር። መልስ የሰጠሁት ብዙዎችን አሰግረምዋል፤ አሰደነግጦአል። ባጭሩ በኢትዮጲያ ሕገ መንግስት ስለ ስልጣን ዘውውር በግልጥ ያስቀመጠው ድነጋጌ ምንም የለም።
በማንኛውም ምክንያት ጠ/ሚኒሰትሩ ተግባራችውን መወጣት ቢያዳግታቸው፤ስልጣኑ ለምክትል ጠ/ሚኒስትር ይትላለፋል ይላሉ ተቃዋሚ ድርጅቶችም:: ይህ ግን በምንም መንገድ በሕገ መንገስቱ ላይ የተጠቀሰ ጉዳይ አይደለም። ስለዚህም ሕገ መንግስቱን ደጋግሞ መመልክት ያስፈልጋል።
በኢትዮጵያ ሕገ መንግስት ላይ የምክትል ጠ/ሚኒስትር ቢሮ በተደጋጋሚ 4 ጊዘ ይነሳል። ከነዚህ ሶሰቱ በአንቀጽ 75 አንዱ በአንቀጽ 76 ሲሆን ይህም የካወንሰል አባለንቱን የሚያሳይ ሲሆን ብ76 ላይ ደግሞ ስለ ተገባሩና ሃላፊነቱ የሚያስርዳው ነው። ዲፒዩቲ ጠ/ሚሩ ሀ) በጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚስጥውን ተግባር ያክናውናል። ለ) ጠ/ሚሩ በማይኖርብት ውቅት ትከቶ ይሰራል። ምክትል ጠ/ሚኒስትር ተጠሪነቱ ለጠ/ሚሩ ነው የሚሉ ናቸው::
በአንቀጽ 75 ስር ምክትል የጠቅላይ ሚኒስትሩ የፖለቲካ ስሪት ነው አንጂ ተግባሩና ሃላፊነቱ በሕገ መንግስቱ የተረጋገጠለት አየደለም። አንደ ጠ/ሚኒሰተሩ በተወካዮቸ ም/በት ወይም በፓርቲው የተመረጠ አለያም አበላጫ ወንበር በያዘው በጥምር ፓርቲው የተመረጠም አይደለም። ይልቁንም ምክትል ጠ/ሚኒስትር በጠ/ሚ የተመደበና የጠቅላይ ሚኒስትሩነ ፍላጎት የሚያሙዋላ የፖለቲካ ሹመኛ ባለስልጣን ነው። ማንኛውም ስልጣኑ ክጥ/ሚኒስትሩ የተቸረው አንጂ በሕገ መንግስቱ የተደገፈ አይደለም። በጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚመደብልትነ ስራዎቸ ያከናውናል አንጂ በራሱ ተነሳሽነት የሚያከናውነው በሕገ መንግስቱ የተሰጠው አንዳችም ተግባር የለውም። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለምክትል ጠ/ሚኒስትሩ ባስኝውና ሲምስለው ብቻ የሚሰጥው ስራ ነው ስራው የሚባለው። ምክትል ጠ/ሚኒስትር በማንኛውም ውቅት ጠ/ሚኒሰትሩ ሊያባርረውና በቦታው ሊተካ ይችላል። በደፈናው ምክትል ጠ/ሚኒስትር ባዶ የሕገ መንግስት ገንቦ ሊባል ይችላል። ከማንኛውመ ሕገ መንግስታዊ ስልጣን የተገለለ ማሰምሰያ፤ ማሳሳቻ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ስራው ተመለስም አለትመለሰ የምክትል ጠ/ሚኒስትር የቢሮ ሃላፊነትና ተግባር በጥንቃቀ መመርምር ተገቢ ነው። በዚሀም ኢትዮጵያ ያጋጠማትነ ሕገ መንግስታዊ ቀውስ መመርመርና መርዳት ተገቢ ነው። ምክትል ጠ/ሚኒስትር በሕገመንግስቱ ላይ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ተወካይ ነው ቢልም አቀማምጡና ትርጉሙ ለተውካዮቸ ምክር ቤት አባላት ለአምስት አመታት የሕዝብ ውክልና ተሰጥቶአችው ይምረጣሉ አንደሚለው ይዘት ያለው አይደለም።
ምክትል ጠ/ሚኒስትሩ አንደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተወካይነቱ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሚሰጠው መመርያ መሰረት ወክሎ ሊገኝ ይችላል።አንደ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ተወካይንቱ ግን ሕገ መንግስታዊ አውቅና የለውምና ከመታዘዝ ውጪ ምንም ሊያድርግ አይችልም። ለምሳለ ዲፒዩቲው አንደተወካይነቱ የጠቅላይ ሚኒስትሩነ ቦታ የመያዝ፤የጦር ሃይሎች አዛዥ ይሚኒስትሮች ምክር በት ሰበሳቢ ሆኖ በምንም መልኩ ሊስየም አይችልም። በሰበብ አስባቡ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቦታ ባዶ ቢሆነ ተገባራትን ለማከናወን ሕግመንግስታዊ አውቅናና ድጋፍ ስለሌለው መመረያ ሊሰጥ ውሳነ ሊያስተላልፍ፤ ሹመት ሊስጥ ምክትል ጠ/ሚኒስትሩ አይችልም። በአጠቃላይ ምክትል ጠ/ሚኒስትሩ በሕገመንግስቱ ተደግፎ በራሱ ሀሊና አየተምራ ሊያከናውን የሚቸልው አንዳችመ ተግባር የለውም፤ ምክትል ጠ/ሚኒስትሩ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ተላላኪ አእለያመ ጉዳይ ፈጻሚ ብቻ ነው።
በአንቀጽ 72-75 ላይ ያለው የሚያስርዳው፤ የየምክትል ጠ/ሚኒስትር ቢሮ አምሰራረት ለይስሙላ በመሆኑ አንዲያው ለነገሩ ተብሎ መሆኑን ባግባቡ ያሳያል። ሕዝቡ ተተኪ አለ ጠቅ/ሚኒስትሩ በማይኖርበት ወቅት የምክትል ጠ/ሚኒስትር ይተካል በሚል ለማሳመን አንጂ በተጨባጩ ግን ለየምክትል ጠ/ሚኒስትር የተሰጠው ነገር ቢኖር ቢሮና ስም ብቻ ነው። የምክትል ጠ/ሚኒስትር የተፈጠረው በሕገ መንግስት ጨረርና፤ንፋስ ባመጣው ጠረነ ብቻ ነው።
ኢትዮጵያ በሕግ መንግስት ቀውስ ውስጥ ነች?
አሁን የኢትዮጵያ ችግር የተፈጠረው የአመራር ክፍተት ብቻ ሳይሆን፤ዘላቂነት ያለው የሕገ መንግስታዊ ችግርም ነው። አመራሩን ለመተካተ አለመቻልና ሕገ መንግስቱ ሲነደፍና ተግባር ላይ ሲውል ያልታሰበበት አለያም ሆን ተብሎ የተፈጠረ ክፍተት በመሆኑ በሃገሪቱ ላይ ብጥብጥና የፖልቲካ ቀውስ መፍጠርያ ነው የሚሆነው። በማንኛውም ሃገር አመሪካንንም ጨምሮ፤ ባብዛኛዎቹ የሃገራት ሕገመንግስት ፕረዝዳነቱ ሰራቸውን ማከናወን ቢሳናችው ካላንዳች ውጣ ውረድ ማን ሊተካ እንደሚገባ በሕገ መንገሰቱ ላይ በግልጥ በመቀመጡ በምንም ሰበብ ቦታው ክፍት አይሆነም ውዝግብም አያስከትልም። በአመሪካመ ቢሆን ፕሬዘዳንቱ በአክል ቢሮአቸው መግባት ቢሳናቸው ምክትላቸው ቦታችውን ይዘው ይሰራሉ ሲመልሱም ምክትሉ ወደቦታችው ይሄዳሉ። ይህም በሕግ መንግስቱ ላይ በማያሻማ መልኩ ሰፍሮአል።
በቅርቡ በሰሜን ኮርያ ለማየት እንደቻልነው ምንም እንኩዋን የሽግግሩ ስሪት የተለየና ከአባት ወደ ልጅ የሚተላልፍ ቢሆንም ይሀውም ቢሆን በሕገ መንግስቱ ላይ ተደንግጎ በዚያ ነው የሚመራው። ታዲያ ለምንድን ነው በኢትዮጵያ ሕግ መንግስት ላይ የስልጣን ሽግግርን በተመለከተ በግልጥ መንገድ ያልተቀመጠው? በተለይም የምክትል ጠ/ሚኒስትር ስልጣን በተመለከተ የሕገ መንግስት አወቃቀሩ ላይ የተሰራው ተንኮል:: ይህ ግድፈት ጨርሶ ተቀባይነት የሌለወ ደባ ነው ሊባል ይቻላል። አወቃቀሩ፤ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አስከ መቸውም በምንም ምክንያት ከስልጣን መንበሩ ላይ የማይነቃነቅ፤ አንዳችም ሁነታ ከስልጣኑ ገለል የማያድረገው ልዩ ስብእና ያለው አእንደሆነና ተተኪም አእንደማያስፈልገው ተደርጎ ነው በ1995 አርቃቂዎች ሕገ መንግስቱ የተሰራውና ነው የምክትል ጠ/ሚኒስትር ሁንይታ ባለበት መንገድ ያስቀመጡት። ይህ የግብር ይውጣ አስራር መቸም ይሁን መቸ ከትውልድ ወቀሳ አያድንም። በስህትተም የተደረገ ነው ማለትም አይቻልም።
ምክንያታዊ ግምገማ ሲድረግም ውጤቱ አርቃቂዎቹ የምክትል ጠ/ሚኒስትር ጥርስ የሌለው አንበሳ፤አቅመ ቢስ ደካማ ስራ አጥ ቁጭ በሉ አድርገው በመሾም ጠ/ሚኒስትሩ በምንም መልኩ ስጋት አእንዳይስማው በጥንቃቄ ነው ያስቀመጡት። በአጨሩ ሰማይ አይየታርሰ …… አንዲሉ። ለመሸፈን የተሞከረውም ጠ/ሚሩ የአንድ ብሄር ተወላጅ ከሆነ የምክትል ጠ/ሚኒስትር የሌላ ብሔር መሆን አለብት የሚለውን መመርያ ለመሸፋፈን የትደረገ ሴራ ነው። ይህ የብሄር የስልጣን ክፍፍል በትክክለኛው መልኩ ቢተገበር ደግሞ ምናለባት ጠ/ሚኒስትሩ በአንዳቸ አጋጣሚ ስራውን ማከናወን ቢያዳግተውና ሸግግሩ በደንቡና በህጋዊ ሂደቱ ቢፈጽም በጠ/ሚኒስትሩ ዙርያ የተሰባሰቡተን የስልጣን ጠባቂዎች ፎሪ ስለሚያስውጣችው ይህንን ለማስወግድ ሲሉ ነው አሁን ባለበት መልኩ ያስቀምጡት። ካልሆነማ የምክትል ጠ/ሚኒስትሩን በደንቡ መሰረት የሚተካው ከሆነ የጠቀላይ ሚኒስትሩ ተተኪ የምክትል ጠ/ሚኒስትር ደጋፊዎቹ የጠ/ሚኒስትሩን ቦታ ሲይዙ የጠቀላይ ሚኒስትሩ ደጋፊዎች መና መሆናቸው ነው። በዚህም እጣ ፈንታችው ቦታውን በተካው በአዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ስር መሆኑ ስለሆነ ይህንን ነው አስቀድመው የተዋጉት።
ያም ሆኖ የቀድሞው ጠ/ሚኒስትር ሰዎችም ቢሆኑ ቀጣዩን የምክትል ጠ/ሚኒስትር ከሌላ በሕዝብ ብዛት አነስተኛ ከሆነ ወገን ለማስመረጥ ከቻሉ ጥቅማቸውን ማስጠበቅ አይሳናቸውም። ይህ አካሄድ ደግሞ ጥቅም አለው። የቀድሞው ባለስልጣናት አሁንም የሕዝብ ፍቅር አላችው፤ስልጣናቸውም አልትነካም መልካምነታቸው ተረጋገጠ ያስብልላችዋል።በዚህም ቀድሞ የነበራቸውን ሁንይታ እንደነበረ አድርገው ጥቅማቸውን በማስጥብቅ ይቀጥላሉ። ቦታውን የያዘውም የምክትል ጠ/ሚኒስትር ዲፒዩቲ ስልጣኑን በራሱ እሳብይ ሊጠቀምበት አያስችሉትም። ያልፈውን ጠ/ሚኒስትር ፍላጎትና እምነት፤ ሃሳብና ህልም ተግባራዊ ለማድርግ መንገዱ ክፍት ይሆንላቸዋል። አዲሱ ጠ/ሚኒስትር የጦሩና ቀድሞ በነበረው የጠ/ሚኒስትር አወቃቀር የተካተቱት የሲቪክ ማህበራትም የቢሮክራሲውም ድጋፍ ስልማየኖረው ሂደቱ ሁሉ የቀድሞው ጠ/ሚኒስትር ነው የሚሆነው።በዚህም ዲፒዩቲወ ምንም ተግባር የሌልው አሻነጉሊት ከመሆን አያልፍም።
በአንቀጽ 75 በአፍሪካ የሕገ መንገሰተ አቀራረጽ ታሪክ ከፍተኛ የፖለቲካ ክስርት ተብሎ ሊዘገብ ይችላል።አሁን ባለው ሁኔታ ጠ/ ሚኒስትሩ ወደ ስራው መመለስ ካዳገተውና ሸግግሩ እንቅፋተ ብዙ ሆኖ ከተገኘ ሌሎቸ የስልጣን ተጋሪዎች አዲስ ምርጫ አንዲካህይድ ሊጠይቁ ይቸላሉ፤ የጠ/ሚኒስትሩ ከባቢዎች ደግሞ ይህ አንዳይከናወን በርካታ እንቅፋቶች በመፍጠርና በመሃልም አለመግባባት እንዲከሰት ያደርጋሉ። ምናልባትም በሃገርና ከውጭም ችግር በመፍጠር ሃግሪቱ አደጋ ላይ ነች በማልትና ለሌላ ተንኮላቸው ጊዜ ለመግዛት ሲሉ የአሰቸኩዋይ ጊዜ አዋጅም ሊያውጁ ይችላሉ። ወይም የጠ/ ሚኒስትሩን ሁኔታ በመሽፋፈንመ ሊቀጥሉበት ይችላሉ። ካለያም ዘላቂ መፍትሄ እስኪገኝ ድረስ ጊዜያዊ መፍትሄ ለማግኝትና በሕገ መንግስቱ መሰረት አለያም በምርጫ ሸግግር እንዲከናወን ሲሉም የውጭ መንግስታትን ጣልቃ ገብነት ይሹ ይሆናል። ቀላሉና ጥሩው ምንገድ ደግሞ ይሄው ብቻ ነው። የዘንባባ ዝንጣፊ በመያዝ ተቃዋሚዎቸነ ችግሩን አብረን በሰላማዊና በሰከነ የሰለጠነ መንገድ በመፍታት ለሃገርም ለሕዝብም የሚብጅውን እናድርግ በማለት አንድ ላይ ለመቆም መወሰን።
ከተቁዋሚዎች ጋር ሰላም መፍጠር የሚያሳፍር ወይም ጉዳት ያለው ነገር አይደለም። በኬንያም በዝንባብዌም የታየ ጉዳይ ነው። እጅግ አስቸጋሪ በሆነው ወቅት እንኩዋን በደቡብ አፍሪካ ሆኖአል። በ2009 ኬንያ እጅጉን በተካርሩ ፓርቲዎች መሃል ጥምር መንግስት ማቁዋቁዋም ችለዋል።ለጥቀውም 67 በመቶ የሕዝብ ድጋፍ ያገኘውን ሕግ መንግስት ለማጽደቅ በቅተዋል። በ2008 ፕሬዜዳንት ሙጋቤና ተቃዋሚው ጠ/ሚኒስትር ሞርጋን ሲቫንጋሪ ባለፈው ሳምንት አዲሱን ሕገ መንግስት ፓርላማው እንዲያጸድቅ ስምምነት ላይ ደርሰዋል። ሁለቱም ሃግሮቸ ወደ ድይሞክራሲ አምባ በሙሉው ሁኔታ ለመቀላቀል ገና ቢሆኑም ትክክለኛውን መንገድ ግን ይዘዋል። በተለያየ መልኩ በብሩንዲ በጊኒ በማዳጋስካር ተሞከሮአል።
ከአምባገነን አገዛዝ ወደ ዴሞክራሲ ሕገመንግስታዊ ሽግግር
የምክትል ጠ/ሚኒስትር ጉዳይ አኢትዮጵያን ለገጠማት የሕገ መንግስት ጉዳይ አጫሪ ሆነ እንጂ ችግሩ ከዚያ ያለፈ ነው። አብዛኛዎቻችን በሕገ መንግስት ላይ እሳቤ ያለን የአኢትዮጵያ ሕገ መንግስት በምክትል ጠ/ሚኒስትር ቢሮና ስልጣን አመዳደብ ላይና ሌሎችንም ያሉበትን በርካታ ሕጸፆቸና ችግር በሚገባ እንረዳለን። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ዲክታተርንትም ቢሆን በግምት ሳይሆን በተጭባጭ እውንነቱ ገሃድ የወጣ ሃቅ ነው።ይህም ከተለያዩ ተግባራትና አካሄድ፤ ክጠ/ሚንስትሩ ድርጊትም ተረጋግጦል። ማናኛውም ስልጣን ባንድ ሰው ስር መሆኑም የዚሁ የፈላጨ ቆራጭነት ባህሪ ነው። የዲክታትርነት መገለጫው፤ምላት ስልጣንን አንቆ መያዝ ሲሆን፤ ይህ ደግሞ በ1995ቱ በተፈጠርው ሕገ መንግስት አንቀጽ 74 ላይ ተቀምጦአል። አንቀጽ 72-75 እንደሚገልጸው ደግሞ የሃገሪቱ ቁንጮ ባለስልጣን በመሆኑ የሀገሪቱ ስልጣናት ሁሉ በጠ/ሚሩና በሚኒስትሮች ምክር ቤት ስር ናቸው ይላል። ጠቅላይ ሚኒስትሩም፤የሀገሪቱ የበላይ ቁንጮ ባለስልጣን ነው፤የሚኒስትሮች ምክር ቤት ሰብሳቢ፤የጦር ሀይሎቸ ጠቅላይ አዛዥ ነው። ጠ/ሚኒስትሩ ለሚኒስትሮች ምክር ቤትም ሆነ ለማንም ያለበት የተጠያቂነት ግዴታ ከቁጥር የሚገባ አይደለም:: እንዲያውም ጠ/ሚሩ በሃገሪቱ ላይ ያለውን ስልጣን በሙሉ ጠቅልሎ ይዞታል። በሁሉም የስልጣን እርክኖቸ ላየ አዛዠ በመሆኑ ማንኛችውንም መዋቅሮች ባሰኝው ወቅት ሊያፈርሳቸው፤ስማቸውን ሊለውጥ ይችላል። ከሚኒስትሮችም በኩል ያልተስማማውን ሊያነሳ፤ዳኞችን ሊመርጥ ሊሽረ ሊሾም የሚችል ሲሆን በአኢትዮጵያ ሕገ መንግስት መሰረት ለማንም ተጠያቂም አይደለም። የጠ/ሚሩ ቃለ አእሰትንፋስ የሓገሪቱ ሕግ ነው። ምንም እንኩዋን አባባሉ ቢከብድም፤ጠ/ሚኒስትሩ ገደብ የለሸ ፈላጭ ቆራጭ ገዢ ነው።
የአፍሪካ መሪዎች ሕይወትና ሕልፈት
ሁሉም ፈላጭ ቆራጭ ግዢዎች ሕይውታቸው ዘላለማዊ ነው ብለው ያምናሉ። ዘላለማዊ ሆኖ የሚኖረው ግን እነሱ ሳይሆኑ በሕይወት ዘመናችው የፈጸሙት ግፍና በደል ብቻ ነው። የአፍሪካ መሪዎች በስልጣን ኮርቻቸው ላይ በሚኖሩበት ዘመናት ሃገራቸውንም ሕዝቡንም ሳይፈሩ እግዚአብሐርንም ከቁብ ሳይቆጥሩ ይኖራሉ። እራሳቸውን ጀግኖችና አምላክ አድርገው አስቀምጠዋል። በዚህም ያምናሉ። ሁሉንም ግን አይደሉም ሃላፊ ጠፊ ናቸው። ይታመማሉ፤ ይሰቃያሉ ልክ ሲቀጠቅጡት ሲያስሩት ሲያንገላቱት ሲያስድዱት አንደንበረው ሕዝብ። ሕዝቡን ታምው ጤናማነታቸውን፤ ሲሞቱም ነፍሳችው እንዳለ ተደርጎ ይታወጅላቸዋል። የቶጎው ፕረዘዳንት አኢያደማ ለበርካታ አመታት ባደረብት የልብ ህመም ተሰቃየቶ መሞቱ ትደብቆ በበድኑ ሲገዛ ሰንብቶ በመጨረሻው በድንገት ላይ መሞቱ ታወጀ። ከሕዝብ ተደብቆ የነበረው እውንት ቀኑን ጠብቆ አደባባይ ወጣ። የጋቦኑ ዲከታተር ኦማር ቦነጎ፤የናይጀርያው ኡማሩ ያር አዱዋ፤የጊኒ ቢሳዋው ባቻይ ሳንሃ፤የማላዊው ቢንጉ ዋ ሙሀታሪካ ሁሉም መታመማችው በድብቅ ተይዞ፤ በሃግር ውስጥ ህክምና በማይድን ክፉ ደዌ ተይዘው ሳሉ ደህና ናቸው እየተባለላችው ሁኔታው ተስፋ ሲያስቆርጥ ለመሞት ወደ ሃገር ገብትወ ደህና ናችው የተባለላቸው ሞቱ ይባልላቸዋል። ከሕዝብ የተደበቀው በሸታ በሞታቸው ተተክቶ ለሕዝብ ይፋ ይሆናል።
ባለፈው ሳምንት ያረፉት የጋናው ፕረዚዳንት አታ ሚልስ ከሌሎቹ የአፍሪካ ፈላጭ ቆራጭ መሪዎች ሁኔታው ይለያል። ለበርካታ ወራተ ሕዝቡ ስለሕመማችወ ያውቅ ነበር። በቦታቸው ለምክትላቸው ድራማኒ ማሃሚ ተተኪነትን በመስጠት እሳችው በማይችሉብት ሁሉ ወክለዋቸው አንዲገኙ አደርገው በይፋ አሳውቅው ነበር። ምንም እንኩዋን ምርጫውን በጠበበ ውጤተ ቢያሸንፉም በሕዝብ ዘንድ በአጭር ጊዜ ተወዳጅነትን አእትርፈው ነበር።ይህን አይነቱ መሪ ነው በለሎቸም የአፍሪካ ሃገሮች ሊኖርና የአፍሪካ መሪዎችም እንደምሳሌ ወስደው ሊከተሉተ የሚገባ።በጋናም ጎዳናዎች ሆነ በአካባቢው ባሉ የምእራብ አፍሪካ ጎዳናዎች ሕዝብ ከዳረ እስከዳር ጋናዊያን በያሉበት ቅስማቸው ተሰበሮ አይኖቻቸው በእንባ ታጥቡ። የተለቪዥን ጣቢያው የጋና ሕዝብ “የሰላም ንጉስ” ብሎ ስለስይማችው መሪ የሞት ዘገባ ገና አውርቶ ሳይጨርስ ነበር የጋና ሕዘብ ማልቀስ የጀመረው።ጋንዲ በአፍሪካ ስለሚገኙት ዲክታተሮች አስቅደመው ነበር የተናገሩት። “ነፍሰ ገዳዮቸና ጨካኘ አርመኔ ገዢዎቸ ለጊዘው የማይደፈሩ ቢመስላቸውም፤ መውድቃቸው ግን አይቀሬ ነው። ሁል ጊዘም ይወድቃሉ።ስልዚህ ሁል ጊዜ ተገንዘቡ::
ኢተዮጵያ አሁን ከገባችብተ የሕገ መንግስት ዝቅጠት መውጫ መንገድ አለ። ነልሰን ማንደላ ይህን መንታ መንገድ በደቡብ አፍሪካ “ይቅር ባይነትና መልካምነት””ብለው ቀይሰውታል። ሁላቸንም በዚያ መንገድ ለመጉዋዝ መዘጋጀት ይኖርብናል። ለብሐራዊ ውይይት ወቅቱ አሁን ነው።
(ይህን ጦማር ለሌሎችም ያካፍሉ::)
ካሁን በፊት የቀረቡ የጸሃፊው ጦማሮችን ለማግኘት እዚህ ይጫኑ::

I am still in Dilemma;
Yes, change is mandatory, whether the prime minister is alive or not. But there are important challenges to be considered 1st.
1-Who? Who should be next is a dilemma for many of us. Opposition parties do not seem to have a better agenda except to lined up as opposition parties only. They are not the best choices as they are not yet with clear cut vision for this country, which should be presented very visibly, as far as any ordinary citizen may get it, be inspired by it and be willing to vote for them. You all know Meles’s vision 22 yrs ago. See how he articulated it,whether he was faithful to his claims or not. We need simply articulated vision as this. Sometimes I am tempted to think that EPRDF may still be better despite its flows.
Individuals like Birhanu Nega are with all moral deficiencies be it ethical or religious, and I have piles of back ups that he could never fit.
Dr Fissiha Eshete is similarly unfit, as he could not even manage his own private family life. I still have enough evidence about him while he was leading his “so called” university. Ask any student who attended that university. You will get the fact. Why is he now interested in politics? What was he doing with them? How smart was he to collect all money he snatched from the free land? And then he run away.
The Oldies-politicians, whether Aregawi,Siye,Gidey,Negasso,Marara, can’t fit as they were the history makers and therefore still accountable for all such a mess.
All media(ESAT;VOA;ETHIOPIAN REVEIW;FITIH;etcetra… seem strongly ambitious to nail down EPRDF. Here I see role confusion. clear your way whether you are politicians, freedom fighters or professional news makers. I say this from the item lists of your media consumption which is very much congested with politics issues only and your emotions very visibly sided. I see you accuse EPRDF with ethnicity but all of you in the media are essentially from one ethnic group, including Aleayehu Gebremariam, Tamagne Beyene. Why? Tesfaye Gebreab is obviously Shabiya from who he really is and what he really talks by his pen. If this is not true then prove it. You seem to make Ethiopianism your cover.Is your blood purely Ethiopian?
Media should be there just as a media, telling reliable facts as much as possible,not pro or anti governments. One way or the other you will be accountable for the subtle destructive roles you are playing over against innocents and a nation as a whole. I am not trying to side with EPRDF. I surely know that EPRDF has overridden the freedom of Media, human rights, justice systems etc. My plea is justify your roles as reliable news makers.
2-What? What should be the task ahead if this may be the termination for EPRDF? No one is so far able to articulate the matrix of the next power play. That is why we see no one trying to grab the tail of this provision(the absence of the prime minister).
3-When? All seem waiting for a miracle to happen or just wait until the last cell of EPRDF dies. With this therefore EPRDF is still the better choice. What I mean is you just choose between two evils; and you take the better evil. I can assure you that no one will qualify for the sit with such a gut.
So What?
LET’S FORGET THE PAST; ALL UNTIL THIS MOMENT; AND CALL FOR RECONCILIATION OF THE RIGHTIEST, THE LEFTIEST AND THE CENTERIST.
ALL POLITICIANS LISTED ABOVE AND THOSE WHO WERE IN DIFFERENT PARTIES,(1940′s todate), SHOULD ALL BE RECOGNIZED FOR THEIR COMMITMENT, AND MAY BE PROVIDED WITH THE SIT OF TRANSITIONAL PARLIAMENT(2013-2017). NO VENGEANCE, NO NEED TO DIG INTO THE PAST AND MAKE THEM ACCOUNTABLE AND THIS SHOULD BE DONE THROUGH NATIONAL RECONCILIATION, LEAVING THE REST FOR THE ROLE OF HISTORY TO DEAL WITH IT.
WE NEED OLDIES, PROFESSIONALLY EXCELLENT,ETHICALLY UPRIGHT JUDGES, FOR OUR COURT SYSTEM.
WE NEED YOUNG ADULTS (ALL BELOW 48) FOR OUR EXECUTIVE POSITIONS INCLUDING THE PRIME MINISTERS OFFICE.
WE NEED A LITTLE POLISH TO OUR CONSTITUTION AND THE POLICIES TO BE REFINED THROUGH PROCESS WHILE BUILDING UP ON WHATEVER IS GOING ON.
SINZIRO.
Our problem starts from focusing on individuals in the way looking for peoples as to who should fit to the PM post rather we have to question our institutions meaning we have to ask weather our institutions are democratically established & are they free or not ?
Looking & selecting for leaders will depend on the answer we give to the above questions .
For eg see our military ,security,police ,justice ,election board etc …how they are formed including the heads, they are not freely established & the leaders also are not selected by merit but by loyalty to one party not to the interest of Ethiopia & its people ,in this situation no one can bring freedom & justice for all even if you bring Angles .So first let’s have free institutions then we can look for individuals that can be able to fit for leadership .
I believe Ethiopia has enough politicians ,generals,technocrats ,lawyers etc not only for herself but for inernational institutions too
.