የኢኮኖሚ ማዕቀብ ግብረሃይል
ከሃገራቸው ውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በጋራ ሆነው የህዝብን ብሶት እንዳያሰሙና ወያኔን በማስወገድ ትግል በቀጥታ እንዳይሳተፉ ለማድረግ አገዛዙ የማይሸርበው ተንኮል የለም። የወያኔ ህልውና መሰረት በማንኛውም መንገድ ህዝቡንና ተቃዋሚውን መከፋፈል በመሆኑ እስትንፋሱ እስካለ ድረስ ስልቱን በመቀያየር መሞከሩ አይቀርም።
በቅርቡ በሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያውያን ስፖርትና ባህል ፌደሬሽን አመራርን በመያዝ ተልእኮውን ለማስለወጥ ያደደረገው ጥረት በህዝብ ወገኖች ትግል መክሸፉ ይታወቃል። ከዚያም 29ኛውን የአንጋፋው ስፖርት ፌደሬሽን የዳላስ ዝግጅት ለማሰናከልና የህዝብ ወገኖችን ለመነጣጠል AESA ONE የሚባል ምንደኛ ቡድን በሼህ አላሙዲን ገንዘብ በመመስረት፤ በዋሽንግተን ዲሲ “ፌስቲቫል አዘጋጅቻለሁ” ብሎ ነበር። ይህ በሚሊዮን ዶላር የሚቆጠር ገንዘብ የተረጨበት የሆድአደሮች ዝግጅት ግን በኢትዮጵያውያን አገር ወዳዶች ጠንካራ ተቃውሞና እቀባ ብኩን ሆኖ ቀርቷል። ይህ ታሪካዊ ድርጊት ወያኔንና አጋፋሪዎቹን የውርደት ማቅ ከማልበሱ በተጨማሪ፤ ግልፅ በሆነ የተግባር አላማ ስር በአንድነት ለተሰለፈ ወገን ያሰበውን ለማሳካት የሚያግደው ሃይል አለመኖሩን አሳይቷል።
በመሆኑም የኢኮኖሚ ማዕቀብ ግብረሃይል BOYCOTT-TPLF Task Force ይህን በወያኔ ደጀንነት በአላሙዲና ጥቂት ሆድ-አደሮቹ የተቀነባበረውን ESFNA የማፍረስና ኢትዮጵያውያንን የመከፋፈል ሴራ በግንባርና በቁርጠኝነት ላከሸፉ ወገኖች፧ በተለይም በዲሲና አካባቢው ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን ያለውን ከፍተኛ አክብሮትና አድናቆት ይገልፃል። ከዚሁ ባልተናነሰ አለኝታችን ESFNA ነው! አንከፋፈልም! በማለት ወደዳላስ በመትመም 29ኛው የስፖርት ክብረ-በዓል ከመቼውም በበለጠ ኢትዮጵያዊነት እንዲደምቅ ላደረጉ ሁሉ አድናቆታችን ከፍተኛ ነው።
ውድ ወገኖች!
በነፃ መገናኛ ብዙሃን ህብረት የተመሰረተው የኢኮኖሚ ማዕቀብ ግብረሃይል BOYCOTT-TPLF ግብረሃይል ዋና አላማ በወያኔና በሸሪኮቹ የንግድ ተቋማት ላይ ማእቀብ በመጣል ለህልውናው መራዘም አስተዋፅኦ የሚያደርጉ የውጭ ምንዛሪ ምንጮችን ማድረቅ መሆኑን ማስታወስ እንፈልጋለን። ስለሆነም የማያባራውን የወያኔ ከፋፋይ እንቅስቃሴ ነቅተን እየጠበቅን በሚከተሉት የማእቀብ እቅዶች ላይ በየአካባቢያችን ተደራጅተን እንድንረባረብ እንጠይቃለን።
1ኛ. ፀረ-አላሙዲን ESFNAን የማፍረስ ሙከራና የዲሲው ዝግጅት ቢከሽፍም በዘርፉ የሚካሄደው ትግል ግን አልተጠናቀቀም። በተለይም የዲሲውን ዝግጅት አላማ ቢነግሯቸውና ቢመክሯቸውም አልቀበልም በማለት በአዘጋጅነት፧ በአዝማሪነትና በመሳሪያ ተጫዋችነት፤ እንዲሁም በንግድ ዘርፍ የእለት ትርፍ አገኛለሁ በሚል የተባበሩትን ሁሉ በያሉበት ኢላማ አድርገን ማግለልና ከንግድ ድርጅታቸው ጋር የነበርንን ግንኙነት ማቋረጥ ስለሚገባ ሃገር-ወዳድ
ኢትዮጵያውያን ሁሉ ከሃዲዎችን አበጥሮ በመለየት በያሉበት የማግለል እርምጃ እንዲወስዱ እንጠይቃለን።
2ኛ. ብሄራዊ ኩራታችን አድርገን እንመካበት የነበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዛሬ የወያኔና አጋሮቹ ጥገት ሆኗል። አስተዳደሩ በወያኔ ከፍተኛ ሹማምንት ተይዞ ዘረፋና ሙስና ነግሶበታል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ አንጡራ ገቢ አንድም አገዛዙን ለማጠናከርያ፥ ሁለትም ሹማምንቱ ከባህር ማዶ ለከፈቱት የባንክ ሂሳብ ማደለቢያ እየሆነ ይገኛል። ለኢትዮጵያ ህዝብ የተረፈው ነገር ቢኖር ስሙ ብቻ ሆኗል።
ስለዚህም በኢትዮጵያ አየር መንገድ ባለመብረርና ሌሎች አማራጮችን በመጠቀም የወያኔን ከፍተኛ የገቢ ምንጩን እንድናደርቅ የኢኮኖሙ ማዕቀብ ግብረሃይል በኢትዮጵያና በህዝብዋ ስም ጥሪ ያደርጋል። አንድ ሰውም ቢሆን ለውጥ ማምጣት ይችላልና በግልና በጋራ በምንወስደው እርምጃ ወያኔን በአጭር ጊዜ አዳክመን ውድቀቱን እንደምናፋጥን እርግጠኛ እንሁን።
የኢኮኖሚ ማዕቀብ ግብረሃይል
Email: boycott.tplf@gmail.com
Tel: 703 828 4821

ከንቱ
ሃሃሃሃ elias amtataw ..next day you will tell us to fly on ERITREA AIRLINES NOT EMIRATES..BUT YOU DON’T EVEN KNOW HOW WE REJECTED YOUR OUTCRY AND CONTINUE TO FLY USING THE HISTORIC ETHIOPIAN AIRLINES …AM PROUD TO FLY USING ETHIOPIAN AIRLINES…
please be specific and expose names who should be targeted for the boyctt.For instance i donot know who is who in my area,Atlanta.If you have credible information bring it on. This is the time ,rhan ever before,to confront woyane and its crumb collectors agressively in unison.
eliyas kifile you and your AGENDA WERE BEING EXPOSED , You are 100 % shaibia’s buchula,so ethiopian can not buy dog’s
barking
ልክ ነው
እባካሁ በወያኒዎቹ ዝግጅት አዳማቂና ተሳታፊ የሆኑትን ዝርዝር ይፋ ብታደርጉልን ቢቻል ክነምስላቸው ብታወጡልን ለትግላችን ጠቃሚ ነው
elisa i think you are going insane.
አየር ምንገዱን ለቀቅ አርጉልነ ሌላውን እንዳሻ
who are the the musicians,the instrument players and the restaurants? you have to make them out.
ህልመኛ
ማለት ተስፈኛ
የአገር መትፋት መፈለግ ፖሎቲካ አይደለም:: ደደብነት ነው.ጉዳያቹህ ከመለሰ ሳየሆን ከህዝብ ይመሰላል::
እጅግ አሳዛኝ ህዝብ ማለት ህበሳ ነው;; ምክንያት አያስፈልገውም
ሆዳም ማን ነዉ ?ዬዳያስፖራ ፖለቲከ————————————-::