የመለስ ዜናዊ ከህዝብ እይታ መሰወር


መረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ


የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የጤንነት ይዞታና ያሉበት ሁኔታ አነጋጋሪ የሆነዉ በኢትዮጵያዉያን ዘንድ ብቻ አይደለም። ጉዳዩ በሀገር ዉስጥና በዉጭ በሚገኙ በርካታ የዲፕሎማሲዉ ማኅብረሰብ አባትም ጭምር መነጋገሪያ ስለመሆኑ ከየአቅጣጫዉ እየተገለፀ ነዉ።

በዓለም ዓቀፍ ደረጃ የታወቁ መፅሔቶችና ጋዜጦችም ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥተዉ አቶ መለስ ዜናዊ የትናቸዉ በማለት እየጠየቁ፤ ስለጤንነታቸዉም ሆነ ስላሉበት ሁኔታ በመንግስት በኩል እስካሁን የተሰጠዉ መግለጫም የሚያረካ ሳይሆን ጥርጣሬዎችን የሚያጭር መሆኑን በመግለፅ ፅፈዉ አስነብበዋል። አንዳንዶቹ ዘገባዎች ሁኔታዉ በየዓመቱ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ዶላሮችን ለመንግስታቸዉ የሚለግሱ ወገኖችንም ማሳሰቡን ነዉ ያመለከቱት።