የመለስ ዜናዊ ከህዝብ እይታ መሰወር

ዶይቸ ቬለ | August 10th, 2012

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የጤንነት ይዞታና ያሉበት ሁኔታ አነጋጋሪ የሆነዉ በኢትዮጵያዉያን ዘንድ ብቻ አይደለም። ጉዳዩ በሀገር ዉስጥና በዉጭ በሚገኙ በርካታ የዲፕሎማሲዉ ማኅብረሰብ አባትም ጭምር መነጋገሪያ ስለመሆኑ ከየአቅጣጫዉ እየተገለፀ ነዉ።

በዓለም ዓቀፍ ደረጃ የታወቁ መፅሔቶችና ጋዜጦችም ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥተዉ አቶ መለስ ዜናዊ የትናቸዉ በማለት እየጠየቁ፤ ስለጤንነታቸዉም ሆነ ስላሉበት ሁኔታ በመንግስት በኩል እስካሁን የተሰጠዉ መግለጫም የሚያረካ ሳይሆን ጥርጣሬዎችን የሚያጭር መሆኑን በመግለፅ ፅፈዉ አስነብበዋል። አንዳንዶቹ ዘገባዎች ሁኔታዉ በየዓመቱ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ዶላሮችን ለመንግስታቸዉ የሚለግሱ ወገኖችንም ማሳሰቡን ነዉ ያመለከቱት።

Play below

 


We would like to hear your opinion.
Join Ethiopian Review's forum and post
your comments. Click here to join us.
If you are already a member, click here.

You must be logged in to post a comment.