የመለስ ዜናዊ መልእክተኞች ስብሰባ በዳላስ


መረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ


ቅዳሜ አፕሪል 9 ቀን 2011 በዳላስ ከተማ የመለስ ዜናዊ መልእክተኞች ስብሰባ ለማድረግ ሕዝብ ጠርተዋል። ይህ የሕወሐት/ኢሕአዴግ መልእክተኛ ቡድን አላማው የኢትዮጵያውያንን አንድነት የተቃዋሚውን ሊመጣ የሚችል ትብብር ለማናጋት ታስቦ የተሰራ በመሆኑ፤ ይህን መሰሪ አላማ በውጭ በነጻነት የምንኖር ሁሉ ልንቃወም ይገባል። በመሆኑም በዳላስ ነዋሪ የሆንን አገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን በዚህ ስብሰባ ተቃውሞ ስልፍ ስለምናደርግ እንድትተባበሩ ጥሪያችን ይድረሳችሁ።

በቴክሳስ፡ ሒውስተን፣ ኦስተን ከተሞች የምትኖሩ ወገኖቻችን ቅዳሜ ለሚደረገው የተቃውሞ ሰልፍ ተካፋይ እንድትሆኑ። እንዲሁም በኦክላሆማ፣ በአርካንሳስ፣ በሉዚያንና እና በቴነሲ ላላችሁ ጥሪ እናደርጋለን። በርሐብ በሚታወቅ ሕዝብ ስልጣናቸውን ለማቆየት ከፍተኛ ወጭ ተደርጎላቸው የመጡ የመለስ ልዑካንን አሳፍረን ልንመልሳቸው ይገባል።

የተቃውሞ ቦታ Marriott hotel 14901 Dallas Parkway. በተጨማሪ ሆቴሉን ለመደወልና የወንጀለኞች አስተናጋጅ መሆኑን ለመንቀፍ በዚህ መደወል ይቻላል 972-661-2800