አቶ ኢሳይያስ አፈወርቂ በቅርቡ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ደቡብ ሱዳን ከሰሜኑ ሱዳን መቆረስ ትክክል እንዳልሆነ አስምረውበታል። የሻቢያው መሪ ነገር ከተማታባቸው ውሎ ያደረ ቢሆንም እየቆየ ግን የሚሉት ሁሉ አስቂኝ እየሆነ እየመጣ ነው። ነፃነት ወይም ባርነትን ምረጥ ተብሎ ነጻነትን መረጠ የተባለለት የኤርትራ ህዝብ ቀንና ሌሊት ባገኘው አጋጣሚ ሁሉ ሃገሩን እየሸሸ ለሞትና ለእሥራት እየተጋለጠ ለመሆኑ የየጊዜው የዜና ዘገባዎች ያመላክታሉ።
በቅርቡ ለሥራ ጉዳይ ወደ ደቡብ ሱዳን ዋና ከተማ ጅባ ተጉዤ የገጠሙኝ ኤርትራዊያንን የኑሮ ሁኔታና የፓለቲካ ሽርክና ላጫውታችሁ። የጁባ ከተማ ይህ ነው የሚሉት ህንጻ የሌለባት፤ ሰው በደመነፍስ የሚመላለስባት፤ ጠበንጃ አንጋች የሚንጋጋባት፤ አሉ የተባሉት የደቡብ ሱዳን ተወላጆች በዘመናዊ ክሩዘር መኪና ከአጃቢ ጋር የሚፈላሰሱበት፤ ባጭሩ የህይወት እሰጣ ገባ አለቅጥ የተሰባጠረባት አሳዛኝ ምድር ናት። በዚህች ከተማ ምግብ ቤቱ፤ ሆቴሉ፤ ኢንሹራንሱ (አዎን ኢንሹራንስ)፤ ሱቆችና ሌሎች ነገሮች የተያዙት በኤርትራዊያን ነው። ለምሳሌ እኔ ያረፍኩበት ሆቴል ለአንድ ሌሊት መቶ ሰላሳ የአሜሪካን ዶላር ሲያስከፍል የሚሰጠው አገልግሎት ሲተመን ግን ሃያ ዶላር ሲበዛበት ነው። የሆቴሉ በዙ ክፍል የተያዘው በደቡብ ሱዳን የጦር ባልደረቦች ሲሆን፤ ቀሪው እንደ እኔው ለሥራ ጉዳይ ብቅ ባሉ የወጭ ሃገር ዜጎች ነው። ታዲያ በዚህ መካከል ነው በደቡብ ሱዳን ወታደራዊ ባለስልጣናትና በኤርትራዊያን ነጋዴዎች መካከል ያለው ጥምረት ቁልጭ ብሎ የታየኝ። ኤርትራዊያን በዚህች ሃገር ለመነገድና ለመኖር የሚከፍሉት ዋጋ ድብቅና ጋሃዳዊ ነው። ድብቁ ጉቦ ነው። ገሃዳዊው ደግሞ ከአቶ ኢሳይያስ የመረረ አገዛዝ እየሸሹ ወደ ደቡብ ሱዳን የሚገቡ ሴቶች ያለፈቃዳቸው ዋጋ እንዲከፍሉ መገደዳቸው ነው። አንድ ከሃማሴን የመጣች ሴት እንዳጫወተችኝ። በንግድ ሥራ ላይ የምታያቸው ሁሉም ባይሆኑ ብዙዎቹ የሻብያ ወኪሎች ናቸው። የመነገጃ ገንዘብም ለመነሻ የተሰጣቸው ከሻቢያ ነው። የተነገደው ገንዘብ ትርፍም ወደ ዓረብ ሃገሮች ይላክና ተመልሶ ዕቃ ተገዝቶበት አስመራ ይገባል አለችኝ። እዚህ የምታየን ብዙዎቻችን በኤርትራ ባለስልጣኖች በጎ ፈቃድ እንድንወጣ የተፈቀደልን ነን በማለት ከፍራቻ አንጻር ዙሪያዋን እየተገላመጠች አጫወተችኝ።
ለዚህም ይመስለኛል ሁሉት ነገሮችን ለመታዘብ የቻልኩት። ኤርትራዊያኑ ነጻ ሆነው ስለፓለቲካ መነጋገር አይመርጡም። ወሬው ሲነሳ ጫወታ እንቀይር በማለት በቀልድ ይሸፍኑታል። ለምሳሌ አንድ የድሮ ጀበሃ (ELF) አሁን በኤርትራ ስላለው ሁኔታ ሲያወራን በዙሪያው ተቀምጠው ቢራ ይጠጡ የነበሩ ኤርትራዊያን ሁሉ አንድ ባንድ ወጥተው ሄድ። የኢሳያስ እጅ በቅርብም በሩቅም ይሰራል ፈርተው ነው አለኝ። እናንተ ከኤርትራ ውጭ ያላቹህ እንዲህ የፈራቹሁ በሃገር ውስጥ እንዴት ይሆን በማለት ጠየኩት። እሱን በቃላት መናገር አይቻልም። ባጭሩ የምድር ቤት እሥር ቤት ናት ኤርትራ በማለት እሱም ሃዘንና ንዴት ይዞት ትቶኝ ተፈተለከ።
ከጁባ ወደ ናይሮቢ ለመሄድ አንድ ቀን ሲቀረኝ። ለቁርስ ቁጭ ባልኩበት ሆቴል ውስጥ ፊቱ ያበጠ ሰው ሲገባ አየሁ። ወደ እኔ ቀረብ ሲል ለየሁትና ቁጭ በል ቁርስ እንብላ ምን ሆነህ ነው አልኩት። ተሰብስበው ደበደቡኝ እኮ አለ። እነማን? ያኔ ቢራ እየጠጣን ጥለውኝ የወጡት ኤርትራዊያን። ለፓሊስ አላመለከትክም አልኩት። ወዳጄ ሁሉ በእጃቸው ነው። የሱዳን ፓሊስ (ወታደር) ገንዘብና ሴት ካገኘ ለመዳኘት ጊዜ የለውም። ግደል ብትለው ይገላል አለኝና በሰላም ያድርስህ በማለት ተሰናብቶኝ ወጣ።
ዜና ላይ ኢትዮጵያ ወደ አራት ሺህ የሚሆኑ ሰላም አስከባሪ ወታደሮች ወደ ሱዳን ለመላክ ተስማማች ይላል። በውነቱ ደቡብና ሰሜን ሱዳንን የሚያስታርቅ ምንም አይነት ሃይል አይኖርም። ነገር የተበላሽው ደቡብ ሱዳን ሃገር መሆን ስትመርጥ ነው። እዚህም ላይ ነው ከአቶ ኢሳይያስ ጋር የእኔም ሃሳብ የሚስማማው። ጦርነቱ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ይቀጥላል። እሳቱ እንዳይጠፋ የሚያናፍሱት ብዙ ናቸው። አሁን በደቡብ ሱዳን ኤምባሲ ጽ/ቤት የሚከፍቱ ሁሉ የሰላሙ ተካፋይ አይደሉም። የሚበልጡት እሳት ለመለኮስ እንዲመቻቸው ስፍራ ለመያዝ እንጂ። ወያኔም ከድሃ አብራክ የወጡ ወጣቶችን ወደማያውቁት ስፍራ በመላክ የእሳት ራት ማድረጉን ማቆም አለበት። ይህ ሰራዊት ተልኮውን(ተልኮ ካለው) እንዳይወጣ አቶ ኢሳይያስ፤ ግብፅና ሌሎችም የአረብ ሃገሮች በሱማሊያ አክራሪ ድርጅቶች በመደገፍ ስፍራ ስፍራ ይዘው እየጠበቁ ነው። የኤርትራዊያን የሰላሳ ዓመት እልቂት ምንም አይነት ለውጥ እንዳላመጣው ሁሉ የደቡብ ሱዳን ነጻነትም በስም ብቻ እንጂ ፍትሃዊነት ኑሮት የደቡብ ሱዳንን ህዝብ በሰላምና በደስታ ከራሱ ጋርና ከጎረቤቱ ጋር እንዲኖር የሚያስችል የነጻነት ድልድይ አይሆንም። በደቡብ ሱዳን የሚገኙ ከበርቴ ኤርትራዊያንም የደቡብ ሱዳን ህዝብ ሲነቃባቸው የሚጠጉበት ሥፍራ አይኖርም። መዝባሪና ተመዝባሪ ዘለቄታዊ ሽርክና የላቸውምና!
ቆይተን እንይ
ኤርትራዊያን በደቡብ ሱዳን (ከአደፍርስ ተሰማ)
አደፍርስ ተሰማ | July 6th, 201122 Responses to “ኤርትራዊያን በደቡብ ሱዳን (ከአደፍርስ ተሰማ)”
We would like to hear your opinion.
Join Ethiopian Review's forum and post
your comments. Click here to join us.
If you are already a member, click here.
You must be logged in to post a comment.

I am totally unsire what the writer wants to say. So, what is wrong if Eritreans go to Sounth Sudan and lead their life. High prices of services is a reflection of limited supply, Economics 101. So what? My friend, Eritrean contributed to the Ethiopian economy way back and before the racist regime in Ethiopia came to power and deported all of them. The bottomline, Eritreans are filling the vacuum created by the decades of repression and backwardness created by North Sudanese. They will do so until South Sudanese learn to do the same. That is what Eritreans did in Ethiopia, after the Italians created the same kind of vacuume in Ethiopia. That is the truth … there is nothing Jewish about Eritreans. They are just smart and they took the risk to invest in a country that is still in turmoil. The rest are waiting for the dust to settle including the Sudanese. Eritrean are used to playing in the dust and taking risk to better themselves. We all need to learn from that and not despise them.
H.E ISAYAS AFEWORKI IS OUR 4EVR PRZ,z only africa leader NO bank account in western country,lovd by his ppl,united inside & outside..manem bechohena bekena yEritrean yedeget godana makome yemechele hile yelen..weyane,igad,au,eu,u.s ayekomewem,ega 5milion ppl issayas nen, esu ega hulachenem new..pls read wiki ‘engage diaspora’ yeweyane fm keaby marseashew gedebe ahun wede eritrea sunction metetuale..yefurstration ena yeritrea yegsegase economy yasdenegetew weyane..antem yebergeke temeselalhe,rehab bhornafrica kefetgtega dereja balebet dereja..Eritrea gene the land of can do ppl ”SELF RELIANCE”shabiazem princeple injoy the fruiat of hardworkig economy, food sefisient.NO handout,aid,nvr knell down 2wyt ppl unlik ur house slave weyane ‘WE R Z GOV ..Z GOV IS US’. case close
Adefris Tessema Reply:
July 7th, 2011 at 6:58 am
MatiT – Make your points clear, so readers can understand your points.
So What,
Shame on u! No matter for u, how the money comes from.
Forced prostitute is normal for u moron gays.
*60years slaves(not investor) under Italy colony
*30years bandit/ሽፍታ
*20years hopless refugees over all the world specialy
Tigraye and Addis Abeba
That makes u proud???
Ato Adefris Tesema ….
If you are sure that my responses are “misguided and a heap of rubbish” as you have said it above, why don’t you leave it to be posted and the reader decide. It makes you uncomfortable eh???
That is it … truth only hurts and my response only shows how cheap and shallow your observation is …. and by the way your way of typesetting resembles some one from Aiga Forume. What forces you to make a U turn?
Adefris Tessema Reply:
July 8th, 2011 at 7:33 am
You are right, I thought I did. My apologies to you. I will try again.
Adefris before u comment on the Eritreans living in Juba,first you have to think about your Government genocide on its own people of Ogaden.
Adefris Tessema Reply:
July 8th, 2011 at 7:32 am
Listen Mr. Eritrean, I have no share with the Weyane regime. Go find and tell them what you feel!
The writer is jealous of Eritreans success. do you also wish to confiscate what Eritreans has earned by working hard like what you have done in Addis. by the way if you could think with your head (not your stomach) there is no difference b/n Sudan police and you. weyane agame is fooling you by giving money and women just the same as what you have written above about Sudan to steal your money and buy weapon to silence you and your brothers.
Adefris Tessema Reply:
July 8th, 2011 at 7:15 am
Dubdub,
Foolish men like you attack people without facts. You have no idea who I am, but you bundle me with weyane with whom you (EPLF) helped destroy Ethiopia. I have no problem with hard working Eritreans. I am just pointing out the facts I observed on the ground in Southern Sudan.
በኢትዮጵያ ውስጥ በአሁኑ ወቅት ፀሐይ የሇችም፡፡ በሀገራችን እውነት የሇችም፤ ቅንነት የምትባሌ ቃሌ ከመዜገበ ቃሊት ተፍቃሇች፤ ፍትህ ርትዕ የለም፤ ሃይማኖት የሇም፤ ባህሌና ወግ ሇታይታና ሇገንብ ማግኛነት ካሌሆነ በስተቀር እውናዊ ኅሌውና የሊቸውም፡፡ መንግሥት የሇም፡፡ ሕዜብም የሇም፡፡ እርግጥ ነው መንግሥት የላሇው ያሇእረኛ ተበትኖ የሚገኝ ሕዜብ አሇ፡፡ ሕዜብ የላሇው የወሮበልች ወይም በተሇምድ እንዯምንሇው የማፊያዎች መንግሥትም ሇስሙ ያህሌም ቢሆን እንዲሇ አንዲንድቻችን እንናገራሇን፤ እንዯውነቱ ግን በተኩሊና ቀበሮ የታጨቀ መንግሥታዊ ተቅዋም እንዯመንግሥት ሉቆጠር የሚገባው አይመስሇኝም፡፡ በተጨማሪም ወያኔን በመጠኑም ቢሆን ኀሉና ካሇው ከማፊያ ጋር ማነጻጸር አግባብ አይዯሇም፡፡ ማፊያዎች ይጠግባለ፤ ወያኔዎች ግን አይጠግቡም፡፡ ወያኔዎች በበለ ቁጥር ይርባቸዋሌ፤ በጠገቡ ቁጥር ጠኔ ይሇቅባቸዋሌ፤ ባገኙ ቁጥር ያጡ የነጡ ይመስሊቸዋሌ፤ በተበቀለ ቁጥር የበቀሌ ስሜታቸው እያገረሸ ይብስባቸዋሌ፣ ሥነ ሌቦናዊ ጭንቀትም ይነዚባቸውና ሇበሇጠ ብቀሊ ያነሳሳቸዋሌ፡፡ በዙያም ምክንያት ይህን የፈረዯበትን ሕዜብ በተከታታይ የመርገምት አኮርባጅ ባሌተወሇዯ አንጀታቸው ይገሸሌጡታሌ፤ ነጋ ጠባ ይገርፉታሌ፤ መፈጠሩንም እስኪራገም ዴረስ አማራጭ እያሳጡ እንዯክርስቶስ ኤልሄ ያሰኙታሌ፤ ኤልሄው እስካሁኒትዋ ቅጽበት ባይዯመጥሇትም፡፡
Adefris Tessema Reply:
July 8th, 2011 at 7:10 am
አስተያየትዎ እውነትን ያቀፈ ነው። ሃገርና ሃይማኖት የተካደበት፤ የቆመው በሞተው ሬሳ ላይ ተጫምቶ ከፍ ብሎ የሚታይበት ምድር ናት።
I think “shabianisem” or as you blind Ertrians described it we the people are the government and vise versa…is the same trick used by the Libyan leader under the title “Jemharia” which is baptized to your leader years back. Gays open your eyes your heart is in Ethiopia if not you would not have been here in the first place.
I think “shabianisem” or as you blind people who call yr self Ertrian described it “we the people are the government and vise versa…”is the same trick used by the Libyan leader under the title “Jemharia” which is baptized to your leader years back. Gays open your eyes your heart is in Ethiopia if not you would not have been here in the first place.
Essayas is Eveil> Belive it or not.
Dear Adefris,
I am living in Juba since 2008. I am an Ethiopian but living together with Ertereas. Juba is one of the places where you see both Habeshas are living in Harmoney. Yihen lemadefres sayihone ayikerim Gash adefris yihen ye tsafkew.
Yes there are few who are politically motivated from both sides. These are appointees of Shabia and Woyane. But the rest of us are just living peacefully, preying togther and eating on the same plate. Please see also the positive side of Juba.
Adefris Tessema Reply:
July 12th, 2011 at 6:17 pm
Tesfaezigi,
Your assessment is objective. Thank you.
Your comment is misguided and a heap of rubbish. Clean up man (THT)!!
MatiT,
If I were you, I shut up and try to learn from others. You have no legs to stand on.
Sembel,
You failed to get the underline message of my writings. I have no problem with any Eritrean succeeding in any corner of the world. The name calling and the insult indicates you are still thinking with the barrel of the gun, not with your brains.
MatiT,
Are you living in a dream world? Wake up and face the truth. How do you measure a country’s independence? Are the people of Eritrea free? For the record, I do not see much of a difference between TPLF in Ethiopia and EPLF in Eritrea. They are two sides of the same coin.
Mr. Rabish,
The name calling indicates you would need your head inspected. If I were you, I check myself to a hospital. Why can you not communicate in a civilized manner?