የግንቦት ሰባት ተከሳሾች ጉዳይ
(DW) — የኢትዮጵያን መንግሥት በሐይል ለመገልበጥ ተንቀሳቅሰዋል የሚል ክስ የተመሰረተባቸዉን የጦር መኮንኖች እና የግንቦት ሰባት አባላት ናቸው የተባሉ ግለሰቦችን ጉዳይ ዛሬ የተመለከተው የከፍተኛው ፍርድ ቤት ሁለተኛ ወንጀል ችሎት ፣ አቃቤ ህግ እንዲወረስለት የጠየቀው የተከሳሾች ንብረት በዝርዝር ተለይቶ እንዲቀርብለት ጠይቋል ።
አቃቤ ህግ በበኩሉ በተከሳሽ ቤተሰቦች የቀረበው የንብረት ይለይልን ጥያቄ በጣልቃ ገብቶ ሊታይ አይችልም ጥያቄው ከችሎቱ ውሳኔ በኃላ የሚታይ ነው ሲል ተከራክሯል ። በመጨረሻም ፍርድ ቤቱ አቃቤ ሕግ እንዲወረስ የጠየቀውን ንብረት በዝርዝር ለይቶ እንዲያቀርብ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል ። ታደሰ ዕንግዳው ዝርዝሩን ልኮልናል ። (Click here to listen)
|
|
Write a Comment
Related posts: