የኢትዮጵያ ፍርድ ቤት ብይንና ተቃዉሞዉ
(DW) — የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ህገ መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለማፍረስ አድመዋል ፤ ግንቦት ሰባት ከተባለው ድርጅት ጋር ዓላማቸውን በኃይል ለማስፈፀም ተንቀሳቅሰዋል ፤ በሚሉና በሌሎችም ተያያዥ ጉዳዮች ክስ በተመሰረተባቸው ከፍተኛ መኮንኖችና ሲቪሎች ላይ ዛሬ የመጨረሻ የቅጣት ውሳኔ ሰጥቷል። በዚሁ ውሳኔ አምስት ተከሳሾች የሞት ቅጣት ሲበየንባቸው ሰላሳ ሶስት ደግሞ የዕድሜ ልክ ዕስራት ተፈርዶባቸዋል ። ከተከሳሾቹም የአንዳንዶቹ ንብረት እንዲወረስ ፍርድ ቤቱ ውሳኔ አሳልፏል ። ዝርዝሩን ታደሰ ዕንግዳው ከአዲስ አበባ ልኮልናል ። Listen below