የኢትዮጵያ መንግሥትና ዉጪ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን
(DW-RADIO) — የኢትዮጵያ መንግሥትና ከፍተኛ ባለሥልጣናት በዉጪ ሐገር ከሚኖሩና ከዉጪ ከተመለሱ ኢትዮጵያዉያን ጋር ዛሬ አዲስ አበባ ዉስጥ እየተወያዩ ነዉ።በዉይይቱ መክፈቻ ላይ የሐገሪቱ ፕሬዝዳት ግርማ ወልደ ጊዮርዮርጊስ ባደረጉት ንግግር በዉጪ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን ያካበቱትን ሐብትና እዉቀት ለሐገር ልማት እንዲያዉሉት ጥሪ አድርገዋል።ፕሬዝዳቱ በዉጪ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን በልማቱ መስክ እንዲሳተፉ መንግሥታቸዉ ድጋፍ እንደሚያደርግም አስታዉቀዋል።ከዉጪ ከተመለሱ አንዳዶቹ ግን የመንግሥት ቢሮ ክራሲ አላሰራም አለን በማለት ያማርራሉ።የዉጪ ጉዳይ ሚንስትር ደ ኤታ ዶክተር ተቀዳ አለሙ በበኩላቸዉ ቢሮክራሲዉን ለማስተካከል መስሪያ ቤታቸዉ እንደሚጥር አስታዉቀዋል።ታደሰ እንግዳዉ ዝር ዝሩን ልኮልናል። (ለማዳመጥ እዚህ ላይ ይጫኑ)
|
|
Write a Comment
Related posts: