የኢትዮጵያው አውሮፕላን አደጋ መንስኤ እስካሁን አልታወቀም
(Deutsche Welle) — የአውሮፕላኑን የአደጋ መረጃ መሰብሰቢያ መሳሪያ ማለትም ብላክ ቦክስ ለማግኘት የሚደረገው ፍለጋም እንደቀጠለ ነው ። እስካሁን ድረስ አውሮፕላኑ አስፍሯቸው ከነበሩት ሰዎች ውስጥ የተገኘው አስከሬን አስራ አምስት ብቻ ነው
ከአስር ቀን በፊት አየር ላይ ተበታትኖ ሜዲትራንያን ባህር ላይ የወደቀው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ለአደጋ የተጋለጠበት ምክንያት እስከሁን ድረስ በውል አልታወቀም ። የአውሮፕላኑን የአደጋ መረጃ መሰብሰቢያ መሳሪያ ማለትም ብላክ ቦክስ ለማግኘት የሚደረገው ፍለጋም እንደቀጠለ ነው ። እስካሁን ድረስ አውሮፕላኑ አስፍሯቸው ከነበሩት ሰዎች ውስጥ የተገኘው አስከሬን አስራ አምስት ብቻ ነው ። የሟቾቹን ማንነት ለመለየት ከወላጅ ዘመዶቻቸው ላይ የምርመራ ናሙና ተወስዷል ። ነጋሽ መሀመድ አደጋውን የሚከታተለው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ልዩ ግብረ ኃይል አስተባባሪ ካፒቴን ደስታ ዘርዑን በስልክ አነጋግሯቸዋል ። (Click here to listen)
|
|
Write a Comment
Related posts:
- የኢትዮጵያ ወቅታዊ ፓለቲካ – ከዶክተር ነጋሶ ጋር የተደረገ ቃለ መጠይቅ
- ግንቦት 22 ከተገደሉት ከወ/ሮ አማረች ገላኔ ባለቤት ከአቶ ገልገሎ ኩይታ ጋር የተደረገ ቃለ-መጠይቅ
- አቶ መለስና ወ/ት ብርቱካን ሲነጻጸሩ
- የበቀለ ሞላ ሆቴል ላንጋኖ ታሸገ