Ethiopian News and Opinion Journal


  • HOME
  • SUBSCRIBE
  • CONTACT
  • FORUM
  • VIDEO
  • DIRECTORY
  • ADVERTISE
  • ALBUM
  • DICTIONARY
  • CLASSIFIEDS
  • EXERCISE
  • Login

የቅንጅት ምክትል ፕሬዚደንት ብርቱካን ሚደቅሳ መኪና ተሸለሙ

August 26th, 2007 |

በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ ፈረንሳይ ለጋሲዮን እየተባለ በሚጠራው አካባቢ የሚኖሩ ነዋሪዎች የአካባቢያቸው ልጅ ለሆነችው ወ/ት ብርቱካን ሚዴቅሳ መኪና በመሸለም ደስታቸውን ገለጹ፡፡ በተጨማሪም ከእስር ለተፈቱት የቅንጅት አመራሮች የምሳ ግብዣ አደረጉ፡፡ በግብዣው ላይ ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማሪያም እና ወ/ት ብርቱካን ንግግር አድርገዋል፡፡ ከቀኑ አምስት ሰአት ጀምሮ ነበር ግብዣውን ያዘጋጁት የአካባቢው ነዋሪዎች ጉድ ጉድ ማለት የጀመሩት፡፡ እንግዶቹ በተጠሩበት 7፡00 ሰአት ሲመጡ ግን አካባቢው በጩኅት ተናወጠ፡፡ ሁሉም ደስታውን በጭብጨባ መግለጽ ጀመረ፡፡

ዝግጅቱ ወደተደረገበት የቀበሌ እድር አዳራሽ ሲገባ አዳራሹ ውስጥ የተሰበሰበው ህዝብ ደስታውን የሚገልጽበት ስሜት ምናልባትም ከምርጫው በሓላ የመጀመሪያው የህዝብ ስሜት ሊባል የሚችል ነበር፡፡ ሁሉም ታዳሚ የቅንጅት አርማ የሆነውን የጣት ምልክት በማውጣት በፉጨት ደስታውን ይገልጻል፡፡
አዘጋጆቹ ንግግር ካደረጉ በሓላ የምሳው ግብዣ ሥነስርአት የተከናወነ ሲሆን ኣቶ ኃይሉ ሻውል ባለመገኘታቸው የተዘጋጀላቸውን ስጦታ በልጃቸው አማካኝነት ተሰተቸዋል፡፡

በተጨማሪም ለፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማሪያም ስጦታ የተሰጠ ሲሆን ይህ ለሁለቱም የተሰጠው ስጦታ የቅንጅት አርማ የሆነው የጣት ምልክት የተቀረጸበት ዱላ ሲሆን ‹‹በትረ መንግስት›› ሲሉም ሰይመውላቸዋል፡፡

ለአቶ ሙሉነህ ኢዩኤል እና አቶ አለማየሁ ለተባለ የአካባቢቸው ወጣት ተጨማሪ ሥጦታን ከሰጡ በኋላ ለወ/ት ብርቱካን ሚዴቅሳ ሽልማት እንዳላቸው ተናገሩ፡፡ ህዝቡ ሽልማቱን ለማወቅ በከፍተኛ ጉጉት የጠበቀ ሲሆን ‹‹ጀግና›› ላለት የአካባቢያቸው ልጅ የመኪና ቁልፍ አስረከቡ፡፡ ህዝቡ ደስታውን በጭብጨባ ገለጸ፡፡

ወ/ት ብርቱካን ምን እንደምትናገር የጠፋት በሚመስል ስሜት በሁለት እጆችዋ አርማውን እያሳየች ከወገቧ በመጎንበስ ምስጋናዋን ገልጻለች፡፡ ወደ መኪናዋም በመሄድ የተሸፈነችበትን ጨርቅ ገልጣ ተረክባለች፡፡

አዘጋጆቹም ሽልማታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ‹‹አቅማችን ፈቅዶ ሁላችሁንም ብንሸልም ደሰ ባለን ነበር… ግን ለሁላችሁም የሚሆን አንድ ስጦታ አለን እሱም ልባችን ነው›› ብለዋል፡፡

ወ/ት ብርቱካን ሚዴቅሳና ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማሪያም ረዘም ያለ ንግግር አድርገው ፕሮግራሙ ተፈጽሟል፡፡

Email This Post | Add a comment FORUM



Related Posts

  1. An Addis Ababa neighborhood honors Bertukan Mideksa
  2. ወደ አሜሪካና አውሮፓ ጉዞ የሚያደርጉት የቅንጅት አመራሮች ቪዛ አላገኙም
  3. እስረኞችን ለማስፈታት የቅንጅት ስራ አስፈጻሚ ከአገር ሽማግሌዎች ጋር እየሰራ ነው
  4. የቅንጅት ስራ አስፈጻሚ አዲሱን የፓርቲ ስያሜ ነገ ያወጣል
  5. የቅንጅት የላእላይ ም/ቤት ወሳኝ ስብሰባውን በማካሄድ ላይ ይገኛል

Leave a Comment

To write your comment in Amharic click here. አስተያየትዎን በአማርኛ ለመጻፍ እዚህ ይጫኑ:: ጽፈው ከጨረሱ በኋላ የጻፉትን ኮፒ አድርገው ወደዚህ ተመልሰው አስተያየት መስጫ ቦክስ ውስጥ ፔስት ያድርጉ::



Click to cancel reply








Recent Posts
  • Ethiopian Youth Public Meeting in Dallas – Saturday, Feb. 11
  • DC area Ethiopian churches under attack
  • Saudi pressured to release detained Ethiopians
  • International Ethiopian Women Conference March 9-11
  • ALEJE and OLF Public Meeting in Washington DC – Feb. 19
  • Where the truth lies in Ethiopia
  • Transformative Reconciliation for Unity in a Nutshell
  • When we were the peacemakers
  • Cooperative Behavior for Transformatve Reconciliation & Unity
  • A resurgent Ethiopian opposition in a new form
  • African Beggars Union Hall?
  • Kilil system is an instrument of Ethiopian disenfrachisement – Part 4
  • Several Meles Zenawi bodyguards arrested
  • UN experts dismayed by growing repression in Ethiopia
  • Swedish journalists appeal to Ethiopia’s dictator
  • Another sign of worsening repression in Ethiopia – IFEX
  • Using Anti-Terror Laws to Terrorize Dissent
  • We’ve met the enemy and he is us
  • Essentials to Resolve Differences for Reconciliation
  • Ethiopian delegation delivers letter to Saudi Arabia embassy in DC


©2012 Ethiopian Review
Publisher & Editor-in-Chief: Elias Kifle
Powered by WordPress