Ethiopian News and Opinion Journal


  • HOME
  • SUBSCRIBE
  • CONTACT
  • FORUM
  • VIDEO
  • DIRECTORY
  • ADVERTISE
  • ALBUM
  • DICTIONARY
  • CLASSIFIEDS
  • EXERCISE
  • Login

የምርጫ ካርድ አንወስድም ያሉ የአንድ ቤተሰብ አባላት ታሰሩ

January 29th, 2008 |

በምስራቅ ሸዋ ዞን ዝዋይ ከተማ ቀበሌ 02 የሚኖሩና በንግድ ስራ የሚተዳደሩ አራት የቤተሰብ አባላት በሚያዝያ ለሚካሄደው ምርጫ ካርድ አንወስድም በማለታቸው በታጣቂዎች ተወስደው መታሰራቸውን ሪፖርተራችን ከስፍራው ዘገበ፡፡

ወራት የቀሩትና ተመዝጋቢ በማጣት እስከቀጣዩ ወር መጀመርያ የተራዘመውን የመራጮች ምዝገባ ለመቀስቀስ በየቤቱ መዞር የጀመሩት የዝዋይ ከተማ የምርጫ አስተባባሪዎች በየቤቱ በመዞር ነዋሪዎቹ የመምረጫ ካርድ መውሰዳቸውን መጠየቅ የጀመሩት ባለፈው ሳምንት መጀመርያ ላይ መሆኑን ዘገባው ያመለከተ ሲሆን ትናንት ማምሻው ላይ በተለመደው ተግባር ላይ ተሰማርተው ማስፈራርያ የተሞላባቸው መጠይቆችን ሲያደርጉ በ02 ቀበሌ ጅንአድ ጀርባ የሚኖሩትና በንግድ ስራ ላይ የተሰማሩት አቶ ግዛው አበጋዝ የምርጫ ካርድ ያለመውሰድ መብት አለኝ በማለት ባነሱት የመብት ጥያቄ በተፈጠረ ውዝግብ ከሁለት ልጆቻቸውና በግሮሰሪያቸው ውስጥ ከሚረዳቸው ዘመዳቸው ጋር ወደ ፖሊስ ጣቢያ ተወስደው እስከዛሬ ከሰአት በኋላ ከቆዩ በኋላ በዋስ ተለቀዋል፡፡

የቅንጅት ተወዳዳሪዎች በምርጫ 97 ወቅት ባሳዩት ከፍተኛ ተሳትፎ ለምርጫው ልዩ ተነሳሽነት አሳይቶ የነበረው መራጭ ህዝብ ሂደቱ ባልታሰበ መንገድ ተደነቃቅፎ ከቀረ በኋላና በተለይም የዝዋይ ህዝብ በመረጣቸው የቅንጅቱ ተወካይ ፋንታ ኦህዴድን ወክለው የተወዳደሩት ግለሰብ በማጭበርበር ለህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ካለፉ በኋላ ቀጣዩ የማሟያ ምርጫ ትኩረት መሳብ እንዳልቻለ የከተማዋን ነዋሪዎች አስተያየት ዋቢ ያደረገው ዘገባ ያመለክታል፡፡

በከተማዋ ኦህዴድን በመወከል የተወዳደሩትና በከፍተኛ የድምጽ ልዩነት የተሸነፉት የዝዋይ ከፍተኛ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ም/ር/መምህር የሆኑት አቶ ሚሊዮን ጋረደው ብሩ የሚባሉ ግለሰብ እንደሆኑ ከትናንቱ አሳፋሪ ክስተት በኋላ ዘጋቢያችን ያነጋገራቸው ነዋሪዎች የጠቆሙ ሲሆኑ ቅንጅቱን በመወከል ያሸነፉት ተወዳዳሪ እንዲሸማቀቁ የሚያደርጉ ጫናዎች ሲደረጉባቸው እንደከረሙ ተገልጧል፡፡

Email This Post | Add a comment FORUM



Related Posts

  1. የምርጫ ጣቢያዎች በዝግ ችሎት እየሰሩ ነው
  2. የምርጫ ቦርድ ጨዋታ ዛሬም ቀጥሏል
  3. የወያኔ እጩዎች ህገ-መንግስታዊ መብታችን ተጥሷል እያሉ ነው
  4. የሚያዝያው ምርጫ መመዝገቢያ ወቅት ለአንድ ወር ተራዘመ
  5. የወያኔ የምርጫ ቅስቀሳ ስልት አደጋ እያስከተለ ነው

Leave a Comment

To write your comment in Amharic click here. አስተያየትዎን በአማርኛ ለመጻፍ እዚህ ይጫኑ:: ጽፈው ከጨረሱ በኋላ የጻፉትን ኮፒ አድርገው ወደዚህ ተመልሰው አስተያየት መስጫ ቦክስ ውስጥ ፔስት ያድርጉ::



Click to cancel reply








Recent Posts
  • Ethiopian Youth Public Meeting in Dallas – Saturday, Feb. 11
  • DC area Ethiopian churches under attack
  • Saudi pressured to release detained Ethiopians
  • International Ethiopian Women Conference March 9-11
  • ALEJE and OLF Public Meeting in Washington DC – Feb. 19
  • Where the truth lies in Ethiopia
  • Transformative Reconciliation for Unity in a Nutshell
  • When we were the peacemakers
  • Cooperative Behavior for Transformatve Reconciliation & Unity
  • A resurgent Ethiopian opposition in a new form
  • African Beggars Union Hall?
  • Kilil system is an instrument of Ethiopian disenfrachisement – Part 4
  • Several Meles Zenawi bodyguards arrested
  • UN experts dismayed by growing repression in Ethiopia
  • Swedish journalists appeal to Ethiopia’s dictator
  • Another sign of worsening repression in Ethiopia – IFEX
  • Using Anti-Terror Laws to Terrorize Dissent
  • We’ve met the enemy and he is us
  • Essentials to Resolve Differences for Reconciliation
  • Ethiopian delegation delivers letter to Saudi Arabia embassy in DC


©2012 Ethiopian Review
Publisher & Editor-in-Chief: Elias Kifle
Powered by WordPress