Ethiopian News and Opinion Journal


  • HOME
  • SUBSCRIBE
  • CONTACT
  • FORUM
  • VIDEO
  • DIRECTORY
  • ADVERTISE
  • ALBUM
  • DICTIONARY
  • CLASSIFIEDS
  • EXERCISE
  • Login

የወያኔ ካድሬዎች የቤት ለቤት ቅስቀሳ ጀመሩ

February 24th, 2008 |

በቀጣዩ ሚያዝያ ለሚካሄደው የአከባቢና የማሟያ ምርጫ የህዝቡን አመለካከት ለመገንዘብ በሚል በዛሬው እለት ከረፋዱ 4፡00 ሰአት ጀምሮ የወያኔ ካድሬዎች በአዲስ አበባ ክፍለ ከተሞች የቤት ለቤት ቅስቀሳ ጀመሩ፡፡

አብዛኛው ሰው ከጠዋት የአምልኮ ስፍራዎች ተመልሶ እቤት ይገኛል ተብሎ በሚታሰብበት ሰአት ቅስቀሳው የተጀመረ ሲሆን ህዝቡ ለካድሬዎቹ ይሰጥ የነበረው ምላሽ ተቃውሞ የነበረበት ነው ባይባልም ጉዳዩን በዝምታ በመመልከት የተወሰነና ለምርጫው ባለቤት ያለመሆኑን እንደሚያመለክት ከምልልሱ መረዳት ይቻል እንደነበር ሂደቱን የተከታተሉት ሪፖርተሮቻችን ዘገባ ያመለክታል፡፡

በቤት ለቤት ቅስቀሳው ወቅት ካድሬዎቹ ያነሷቸው ከነበሩት ጥያቄዎች የተወሰኑት ‹‹እስካሁን የነበረውን ኢኮኖሚያዊ እድገት የበለጠ ለማሳደግ መንግስት ምን ማድረግ አለበት ይላሉ?››፤ ‹‹የቤት እመቤቶች ኑሯቸውን ለማሻሻል በመንግስት ምን አይነት እገዛ ሊደረግላቸው ይገባል… (ይህ ጥያቄ የሚቀርበው ካድሬው በሩን ሲያንኳኳ የሚከፍቱት የቤት እመቤቶች ከሆኑ ነው)፤ በምርጫ 97 ያጋጠሙት ችግሮች እንዳይደገሙ ከመንግስት፤ ከህዝቡና ከተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምን ይጠበቃል ብለው ያስባሉ?›› እና የመሳሰሉት የተለሳለሱ ውይይታዊ መሰል ጥያቄዎች ይገኙባቸዋል፡፡

በህዝቡ በኩል በምርጫ ታሪክ ይወክለኛል በሚል ሙሉ እምነት ጥሎ የመረጠው ቅንጅት ባለበት አሳሳቢ ችግር (ቀውስ) ውስጥ በመሆኑ፤ በቀጣዩ ምርጫ ራሳቸውን በተቃዋሚነት ካቀረቡት ጠንካራ ሊባሉ የሚችሉ ፓርቲዎች የተወሰኑት ብሄር ተኮር መሆናቸውና ህብረብሔራዊ ፓርቲዎቹም የጎላ ሚና መጫወት እንደማይችሉ በተለያዩ አጋጣሚዎች በማሳየታቸው፤ በጸጥታ ውስጥ ሆኖ የቅንጅትን ትንሳኤ የሚጠብቅ በመሆኑ፤ ለካድሬዎቹ መጠይቆች ተቃውሞ ማሳየቱ እርባና እንደሌለው የቆጠረ እንዳስመሰለው ሁኔታውን የተከታተሉት ሪፖርተሮቻችን ዘገባ ይጠቁማል፡፡

Email This Post | Add a comment FORUM



Related Posts

  1. የወያኔ የምርጫ ቅስቀሳ ስልት አደጋ እያስከተለ ነው
  2. ይፋ የሆነው የወያኔ እጩዎች ዝርዝር ውዝግብ አስነሳ
  3. ተስፋዬ መንገሻ የወያኔ ካድሬዎችን አስጠነቀቁ!
  4. ተቃዋሚ ፓርቲዎች ስለቀጣዩ ወር ምርጫ እየተወያዩ ነው
  5. የቅንጅት የላእላይ ም/ቤት በቀጣዩ ሳምንት ወሳኝ ስብሰባ ያደርጋል

Leave a Comment

To write your comment in Amharic click here. አስተያየትዎን በአማርኛ ለመጻፍ እዚህ ይጫኑ:: ጽፈው ከጨረሱ በኋላ የጻፉትን ኮፒ አድርገው ወደዚህ ተመልሰው አስተያየት መስጫ ቦክስ ውስጥ ፔስት ያድርጉ::



Click to cancel reply








Recent Posts
  • Ethiopian Youth Public Meeting in Dallas – Saturday, Feb. 11
  • DC area Ethiopian churches under attack
  • Saudi pressured to release detained Ethiopians
  • International Ethiopian Women Conference March 9-11
  • ALEJE and OLF Public Meeting in Washington DC – Feb. 19
  • Where the truth lies in Ethiopia
  • Transformative Reconciliation for Unity in a Nutshell
  • When we were the peacemakers
  • Cooperative Behavior for Transformatve Reconciliation & Unity
  • A resurgent Ethiopian opposition in a new form
  • African Beggars Union Hall?
  • Kilil system is an instrument of Ethiopian disenfrachisement – Part 4
  • Several Meles Zenawi bodyguards arrested
  • UN experts dismayed by growing repression in Ethiopia
  • Swedish journalists appeal to Ethiopia’s dictator
  • Another sign of worsening repression in Ethiopia – IFEX
  • Using Anti-Terror Laws to Terrorize Dissent
  • We’ve met the enemy and he is us
  • Essentials to Resolve Differences for Reconciliation
  • Ethiopian delegation delivers letter to Saudi Arabia embassy in DC


©2012 Ethiopian Review
Publisher & Editor-in-Chief: Elias Kifle
Powered by WordPress