Ethiopian News and Opinion Journal


  • HOME
  • SUBSCRIBE
  • CONTACT
  • FORUM
  • VIDEO
  • DIRECTORY
  • ADVERTISE
  • ALBUM
  • DICTIONARY
  • CLASSIFIEDS
  • EXERCISE
  • Login

አንድነት ፓርቲ ሁለት ከፍተኛ ስብሰባዎችን አካሄደ

March 23rd, 2008 |

በተቀዳሚ ፕሬዝዳንት ወ/ሪት ብርቱካን የሚመራው የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በዛሬው እለት ጠዋትና ከሰአት በኋላ ሁለት የተለያዩ ውጤታማ ስብሰባዎችን አካሄደ፡፡

የመጀመርያውና እስከ እኩለ ቀን የቆየው ስብሰባ በወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳና በዶ/ር ኃይሉ አርአያ የተመራ ሲሆን የቀድሞ የቅንጅት ታዋቂና ብቃት ያላቸው አባላትን ያሰባሰበ ነበር፡፡ በዚህ 42 የአስተባባሪነት ብቃት ያላቸውን የቀድሞ አባላት ባሰባሰበ የውይይት መድረክ ላይ በርካታ ሃሳቦች ተነስተው የተንሸራሸሩ ሲሆን በቀጣዩ የትግል ሂደት ላይ መከናወን ያለባቸው አበይት ጉዳዮች ተነስተው ገንቢ ውሳኔዎች ተላልፈዋል፡፡

አባላቱ ቀደም ባሉት ቀናት በአቶ አባይነህ የሚመራውን ስብስብ በማነጋገር ወደ ትግሉ ለመመለስ ጊዜው እንዳልመሸበት ቢያሳስቡም ቡድኑ በአፍራሽ እንቅስቃሴው እንደቀጠለበት በስብሰባው ላይ ተጠቁሟል፡፡ በመጨረሻም ለትግሉ ፍሬያማነት ከምንጊዜውም በበለጠ መስራት እንዳለባቸው በመወሰን የመስራች አባላት ፊርማ የማሰባሰቡን ሂደት በሃላፊነት እንደሚረከቡ አረጋግጠዋል፡፡

ከሰአት በኋላ በተካሄደው ስብሰባ ላይ ደግሞ በ1997 ቅንጅትን በመወከል የአዲስ አበባ የቅንጅት የክልል ም/ቤት ተመራጮች የነበሩ አባላት በፓርቲው ጽ/ቤት ባደረጉት ስብሰባ ቀጣዩን የትግል ስልት አስመልክቶ የመከሩ ሲሆን ፓርቲው የሚጠናከርባቸውንና ከህዝቡ ጋር የሚኖረው ግንኙነት ከምንጊዜውም በበለጠ እንዲሻሻል ለማድረግ በየተመረጡባቸው ክ/ከተሞች ሰፊ ስራ እንደሚሰሩ በመስማማት ተጠናቋል፡፡ በስብሰባው ላይ ዶ/ር ኃይሉ የተገኙ ሲሆን በአጠቃላይ 25 ተመራጮች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡

Email This Post | Add a comment FORUM



Related Posts

  1. አቶ አባይነህ የጠሩት የላእላይ ም/ቤት ስብሰባ አባላት ባለመገኘታቸው ሳይካሄድ ቀረ
  2. የቅንጅት የላእላይ ም/ቤት ወሳኝ ስብሰባውን በማካሄድ ላይ ይገኛል
  3. የነተመስገን ዘውዴ ያለመከሰስ መብት እንዲነሳ አየለ ጫሚሶ ጠየቁ
  4. ቀሪ እስረኞችን ለማስፈታት ጥረት እየተደረገ ነው
  5. የቅንጅት ከፍተኛ አመራር በደቡብ ኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት ሊያድርግ ነው

Leave a Comment

To write your comment in Amharic click here. አስተያየትዎን በአማርኛ ለመጻፍ እዚህ ይጫኑ:: ጽፈው ከጨረሱ በኋላ የጻፉትን ኮፒ አድርገው ወደዚህ ተመልሰው አስተያየት መስጫ ቦክስ ውስጥ ፔስት ያድርጉ::



Click to cancel reply








Recent Posts
  • Ethiopian Youth Public Meeting in Dallas – Saturday, Feb. 11
  • DC area Ethiopian churches under attack
  • Saudi pressured to release detained Ethiopians
  • International Ethiopian Women Conference March 9-11
  • ALEJE and OLF Public Meeting in Washington DC – Feb. 19
  • Where the truth lies in Ethiopia
  • Transformative Reconciliation for Unity in a Nutshell
  • When we were the peacemakers
  • Cooperative Behavior for Transformatve Reconciliation & Unity
  • A resurgent Ethiopian opposition in a new form
  • African Beggars Union Hall?
  • Kilil system is an instrument of Ethiopian disenfrachisement – Part 4
  • Several Meles Zenawi bodyguards arrested
  • UN experts dismayed by growing repression in Ethiopia
  • Swedish journalists appeal to Ethiopia’s dictator
  • Another sign of worsening repression in Ethiopia – IFEX
  • Using Anti-Terror Laws to Terrorize Dissent
  • We’ve met the enemy and he is us
  • Essentials to Resolve Differences for Reconciliation
  • Ethiopian delegation delivers letter to Saudi Arabia embassy in DC


©2012 Ethiopian Review
Publisher & Editor-in-Chief: Elias Kifle
Powered by WordPress