Ethiopian News and Opinion Journal


  • HOME
  • SUBSCRIBE
  • CONTACT
  • FORUM
  • VIDEO
  • DIRECTORY
  • ADVERTISE
  • ALBUM
  • DICTIONARY
  • CLASSIFIEDS
  • EXERCISE
  • Login

ተቃዋሚ ፓርቲዎች ስለቀጣዩ ወር ምርጫ እየተወያዩ ነው

March 23rd, 2008 |

በቀጣዩ ወር በመላው አገሪቱ የሚካሄደውን የአከባቢና የማሟያ ምርጫ ከፍተኛ የመብት ጥሰትና ወከባ በመፍጠር የወያኔ ካድሬዎች በነጻ ምርጫ ስም በህዝቡ ላይ ተጨማሪ የጭቆና ዘመን ከመፍጠር ባለፈ ተቃዋሚዎች አንዳችም ወንበር የማያገኙበት በመሆኑ ከምርጫው ለመውጣት ጥምረታዊ ውይይት በማካሄድ ላይ መሆናቸውን ማንነታቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ ታማኝ ምንጮቻችን ገለጹ፡፡

በኢትዮጵያ የምርጫ ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ከፍተኛ አሃዝ ያለው የእጩዎች ስብስብ በግዳጅና በተለያዩ መደለያዎች ያዘጋጀው ወያኔ በቀጣዩ ምርጫ የተወሰኑ መቀመጫዎችን ራሱ ላዘጋጃቸው ተቃዋሚ ተብዬዎች ከመልቀቅ ባለፈ ህዝቡ የሚደግፋቸውን ተቃዋሚዎች የመምረጥ እድሉ ሙሉ ለሙሉ በአደጋ ስለተከበበ በምርጫው መሳተፍ ሳይጀመር መጨረሻው የታወቀውን ምርጫ ህጋዊ ካባ ማላበስ ነው ሲሉ ፓርቲያቸውን በመወከል በጉዳዩ ዙርያ ከሌሎች ተቃዋሚ ፓርቲዎች በመወያየት ላይ ያሉት ምንጫችን እምነታቸውን ገልጸዋል፡፡ ህዝቡ ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርግ ለምን ይፋዊ መግለጫ አትሰጡም በማለት ከዜና አገልግሎቱ ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱም ያንን ማድረጋችን አይቀርም ሆኖም በአሁኑ ሰአት መግለጫውን መስጠቱ በእጩዎች ላይ እንግልት የሚፈጥር ከመሆኑም በላይ ውይይቱ ስላልተቋጨ የተወሰኑ ጊዜያት ያስፈልጋሉ በሚል እምነት መሆኑን አስታውሰዋል፡፡

በትግል ውስጥ ረዥም ዘመን በማሳለፍ የሚታወቁት እኒህ የፖለቲካ ሰው ጨምረው እንደገለጹት አብዛኞቹ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ለአላማው ያሳዩት አዎንታዊ ምላሽ ከፍተኛ መሆኑን በመግለጽ ይህ ዴሞክራሲያዊ መብትን የመጠቀም እርምጃ ከዴሞክራሲ ጋር እስከወዲያኛው የተጣሉትን ወያኔዎችን አስቆጥቶ ወደ ሃይል እርምጃ ሊከታቸው ወይም በምርጫ 97 እንደሆነው ‹‹የአመጽ አማራጭ›› ተብሎ መስዋእትነት ሊያስከፍል ቢችልም አብዛኞቹ ተቃዋሚ ፓርቲዎች መንፈሳዊ ዝግጅት ማድረጋቸውን ገልጸዋል፡፡

ውሳኔው ይፋ በሚደረግበት ወቅት ሊደርሱ የሚችሉ የመብት ጥሰቶችን አስመልክቶ በአገር ውስጥ ያሉም ሆኑ በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ከጎናቸው በመቆም የተለመደ ድጋፋቸውን እንደሚያሳዩዋቸው ያላቸውን እምነትም ገልጸዋል፡፡

Email This Post | Add a comment FORUM



Related Posts

  1. ተስፋዬ መንገሻ የወያኔ ካድሬዎችን አስጠነቀቁ!
  2. የተቃዋሚ ፓርቲ ተወዳዳሪዎች ያለ ህግ ስርአት እየታሰሩ ነው
  3. ፓርቲዎች ቁጥጥር እየተደረገባቸው አላማቸውን አስተዋወቁ
  4. የቅንጅት የላእላይ ም/ቤት በቀጣዩ ሳምንት ወሳኝ ስብሰባ ያደርጋል
  5. የአዲስ አበባ እጩዎች ዝርዝር ይፋ ሆነ

Leave a Comment

To write your comment in Amharic click here. አስተያየትዎን በአማርኛ ለመጻፍ እዚህ ይጫኑ:: ጽፈው ከጨረሱ በኋላ የጻፉትን ኮፒ አድርገው ወደዚህ ተመልሰው አስተያየት መስጫ ቦክስ ውስጥ ፔስት ያድርጉ::



Click to cancel reply








Recent Posts
  • Ethiopian Youth Public Meeting in Dallas – Saturday, Feb. 11
  • DC area Ethiopian churches under attack
  • Saudi pressured to release detained Ethiopians
  • International Ethiopian Women Conference March 9-11
  • ALEJE and OLF Public Meeting in Washington DC – Feb. 19
  • Where the truth lies in Ethiopia
  • Transformative Reconciliation for Unity in a Nutshell
  • When we were the peacemakers
  • Cooperative Behavior for Transformatve Reconciliation & Unity
  • A resurgent Ethiopian opposition in a new form
  • African Beggars Union Hall?
  • Kilil system is an instrument of Ethiopian disenfrachisement – Part 4
  • Several Meles Zenawi bodyguards arrested
  • UN experts dismayed by growing repression in Ethiopia
  • Swedish journalists appeal to Ethiopia’s dictator
  • Another sign of worsening repression in Ethiopia – IFEX
  • Using Anti-Terror Laws to Terrorize Dissent
  • We’ve met the enemy and he is us
  • Essentials to Resolve Differences for Reconciliation
  • Ethiopian delegation delivers letter to Saudi Arabia embassy in DC


©2012 Ethiopian Review
Publisher & Editor-in-Chief: Elias Kifle
Powered by WordPress