Ethiopian News and Opinion Journal


  • HOME
  • SUBSCRIBE
  • CONTACT
  • FORUM
  • VIDEO
  • DIRECTORY
  • ADVERTISE
  • ALBUM
  • DICTIONARY
  • CLASSIFIEDS
  • EXERCISE
  • Login

ታላቁ የኢትዮጵያ ሩጫ ላይ ሃይሉ ሻውል ተወገዙ

November 22nd, 2009 |

Great Ethiopian Run Nov 21 2009aአውራምባ ታይምስ (አዲስ አበባ)፡- በ1994 ዓ.ም. የተጀመረው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ለ9ኛ ጊዜ በዛሬው እለት ተካሄደ፡፡ ውድድሩን እንግሊዛዊቷ አትሌት ፓውላ ራድክሊፍ ከደራርቱ ቱሉ እና ከኃይሌ ገ/ሥላሴ ጋር በመሆን አስጀምራለች፡፡

በታላቁ ሩጫ የተቃውሞ ድምጾች መሰማት የጀመሩት በ1998 ዓ.ም ህዳር ወር የቅንጅት አመራሮችና ጋዜጠኞች መታሰራቸውን በመቃወም ሲሆን ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በየአመቱ ወቅታዊ የተቃውሞ ድምጾችን እያስተናገደ እዚህ ደርሷል፡፡ ዘንድሮም ውድድሩ በተካሄደባቸው ጐዳናዎች ላይ

እንነጋገር
የብርቱዬን ነገር
እንነጋገር
የቤንዚኑን ነገር
መሰናበቻ መሰናበቻ
የቀረችን ብርቱካን ብቻ
ልብ የሌለው ኃይሉ ሻውል ብቻ
የአለም ጅሉ
የኢትዮጵያው ኃይሉ
ወኔ የሌለው
ኃይሉ ሻውል ነው
ቡርቱካን ማንዴላ
ልደቱ ሌባ
ጫሚሶ ሌባ

እና መሰል ተቃውሟዊ ኃሳቦች የተንሸራሸሩ ሲሆን ካለፉት ዓመታት አንፃር ሲታይ ግን የበረከቱ የተቃውሞ መልዕክቶች እና ተሳታፊዎች አልነበሩም፡፡

መከላከያ ሚኒስቴር፣ ፍርድ ቤት፣ ቤተ-መንግስት፣ ፍትህ ሚኒስቴር አካባቢ የደረሱ ሯጮች (ተሳታፊዎች) በኢህአዴግ መንግስት ላይ ከፍተኛ የጩኸት እና የተቃውሞ ድምጾች ያሰሙ ነበር፡፡ ባለፈው ዓመትም ቴዲ አፍሮ እንዲፈታ ለመጠየቅ ‹ኦባማ ይፈታ› የሚል ተቃውሞ መቅረቡ አይዘነጋም፡፡

በዛሬው የታላቁ ሩጫ ውድድር በሴቶች ኮረኒ ጀሊላ፣ በወንዶች ጥላሁን ረጋሳ የውድድሩን ሪከርድ በመስበር ጭምር አሸናፊ መሆን ችለዋል፡፡

በክብረ እንግድነት የተገኘችው የዓለም የሴቶች ማራቶን ሪከርድ ባለቤቷ ፓውላ ራድክሊፍ ባለፈው አርብ ወደ አዲስ አበባ የገባች ሲሆን ወደ ኢትዮጵያ በመምጣቷ ደስተኛ መሆኗን ገልፃለች፡፡ የረጅም ዓመት የሩጫ መድረክ ተፋላሚዋ ደራርቱ ቱሉን “በትራክም ሆነ በጐዳና ላይ የሩጫ ውድድር ሳውቃት ፀባዩዋ አንድ አይነት ነው፡፡ ጥሩ፣ መልካም እና ለሰው የምታስብ ታላቅ አትሌት ናት፡፡” ስትል ባለፈው አርብ ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በሒልተን ሆቴል ጠርቶት በነበረው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ለአውራምባ ታይምስ ገልጻለች፡፡

Email This Post | Add a comment FORUM



Related Posts

  1. የኢትዮጵያ የነዳጅ ዘይት ፍለጋ ስምምነት
  2. የኢትዮጵያ ሕዝብ ለሰጠን ኃላፊነት ብቁ ሆነን አልተገኘንም – ዶ/ር ያዕቆብ ኃ/ማርያም
  3. በኢትዮጵያ ጋዜጠኞች ላይ የተላለፈው የእሥራት ብያኔ ተኮነነ
  4. Protest rally in DC against land giveaway to Sudan – June 2
  5. ወደ አሜሪካና አውሮፓ ጉዞ የሚያደርጉት የቅንጅት አመራሮች ቪዛ አላገኙም

Leave a Comment

To write your comment in Amharic click here. አስተያየትዎን በአማርኛ ለመጻፍ እዚህ ይጫኑ:: ጽፈው ከጨረሱ በኋላ የጻፉትን ኮፒ አድርገው ወደዚህ ተመልሰው አስተያየት መስጫ ቦክስ ውስጥ ፔስት ያድርጉ::



Click to cancel reply








Recent Posts
  • Ethiopian Youth Public Meeting in Dallas – Saturday, Feb. 11
  • DC area Ethiopian churches under attack
  • Saudi pressured to release detained Ethiopians
  • International Ethiopian Women Conference March 9-11
  • ALEJE and OLF Public Meeting in Washington DC – Feb. 19
  • Where the truth lies in Ethiopia
  • Transformative Reconciliation for Unity in a Nutshell
  • When we were the peacemakers
  • Cooperative Behavior for Transformatve Reconciliation & Unity
  • A resurgent Ethiopian opposition in a new form
  • African Beggars Union Hall?
  • Kilil system is an instrument of Ethiopian disenfrachisement – Part 4
  • Several Meles Zenawi bodyguards arrested
  • UN experts dismayed by growing repression in Ethiopia
  • Swedish journalists appeal to Ethiopia’s dictator
  • Another sign of worsening repression in Ethiopia – IFEX
  • Using Anti-Terror Laws to Terrorize Dissent
  • We’ve met the enemy and he is us
  • Essentials to Resolve Differences for Reconciliation
  • Ethiopian delegation delivers letter to Saudi Arabia embassy in DC


©2012 Ethiopian Review
Publisher & Editor-in-Chief: Elias Kifle
Powered by WordPress