Ethiopian News & Opinion Journal
  • HOME
  • Contact
  • Advertise
  • Subscribe
  • Ge'ez Fonts
  • FORUM
  • ALBUM
  • ARCHIVE
  • CLASSIFIEDS
  • Login

Kinijit Dallas opposes giving Ethiopian land to Sudan

May 11th, 2008 |  |  1 Comment

The Kinijit Support Group in Dallas, Texas, has issued the follwing statement opposing the illegal land give away of Ethiopian land to Sudan.

መሐል ዳር እንዳይሆን

ከዳላስ ቅንጅት ድጋፍ ቻፕተር የተሰጠ መግለጫ

የኢትዮጵያ ህዝብ ፀር እና ባላንጣ የሆነው የወያኔ ኢሀአዴግ ፋሽስታዊ አስተዳደር ገና ከመነሻው የጀመረውን አገርንና ህዝብን የመከፋፈል አባዜ በመቀጠል ለዘመናት ተከባብሮ፤ ተስማምቶና ተግባብቶ የኖረውንና በጋራ መተሳሰብ ፤ መረዳዳት እና በጽኑ ወዳጅነት ላይ የተገነባውን የኢትዮጵያ ህዝብ እንድነት ለመናድ በጎሳ እና በዘር እየከፋፈለ እንዱ ወገን ከሌላው ጋር እንዲጋጭ እና ህዝቡ እርስ በርሱ እንዳይተማመን ለማድረግ የሚሽርበው ሴራ እና እፀያፌ ድርጊት በሰፊው ቀጥሎ ባለበት ባሁኑ ወቅት ይኽው እረመኔ መንግስት በህዝቡ ላይ የግፍ እገዛዝ ቀንበሩን ከጫነበት ጊዜ እንስቶ እስካሁን ህዝቡን ብፋሽስታዊ እገዛዙ ከማሰቃየቱም ሌላ እገርን ቆርሶ ለባእዳን የመስጠት ደባውንም ቀጥሎበታል።

ሁላችንም እንደምናውቀው ከዚህ በፊት ኤርትራንና የባህር ክልላችንን ያለምንም ህዘበ-ውሳኔ በራሱ ፈቃድ ብቻ ለፈጣሪዎቹ ለኤርትራ ገንጣዮች አሳልፎ በመስጠቱ ይኽው ዛሬ በባህር ንግድና በወደቦቿ ታዋቂ የነበረችው ሐገራችን ወደበ-አልባ ሆና የጎረቤት አገሮችን ወደቦች በመጠቀም ለነዚህ ሀገራት የወደብ ግልጋሎት ፣ የ ጉሙሩክ እና ኤክሳይዝ ቀረጥ ሲሳይ ለመሆን በቅታለች ። ይህም ብቻ አይደለም ወያኔ የሰሜናዊ ትግራይ ግዛት የሆነውንና ከሁሉም የኢትዮጵያ ግዛቶች የተውጣጡ ከ 70 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን መ ለዮ ለባሾች የተሰውበትን ባድመን አስመልከቶ ከሻብያ ጋር በተነሳው የግዛት ይገባኛልጥያቄ ላይ ውሳኔ ለመስጠት በሄግ ተሰይሞ በነበረው አለም አቀፍ ፍርድ ቤት፣ ወያኔ ያለበቂ ጥናት ዝግጅትና ማስረጃ ለይስሙላ ብቻ ለክርክር በመቅረቡ እነሆ የዓለም እቀፉ ፍርድ ቤት ባድመ የኤርትራ ግዛት እንደሆነች አድርጎ ፈርዳል።

ይህ በእንዲህ እያለ ሰሞኑን ደግሞ አንድ አስገራሚና አሳዛኝም የሆነ ጉዳይ ተፈጥሮ በሐገር ውስጥም ሆነ በዓልም ዙሬያ ያሉ ኢትዮጵያውያንን በሰፊው እያነጋገረ እያስቆጣና ምናልባትም ኢትዮጵያውያን በዘረኛው አገዛዝ ላይ ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ የማያዳግም እርምጃ እንዲውስዱ እየገፋፋ ይገኛል፣ ይኸውም ጉድይ የ 1600 ኪ/ሜ ርዝመትና ከ 30-50 ኪ/ሜ የጎን ስፋት ያለውንና ከሰሜናዊ ጎንደር አካባቢ ጅምሮ አስከ ጋምቤላ ድረስ የሚዘልቀውን የኢትዮጵያ ለም መሬት ለሱዳን መንግስት አሳልፎ መስጠቱ ነው። ይህ አይነቱ የወያኔ ተግባር ከ ሐገር ክህደት ወንጀል ተነጥሎ የሚታይ አይደለም። ውያኔ ዝም ከተባለና በዚሁ ከቀጠለ እገሪቷን በየአቅጣጫው ቆራርጦና በጣጥሶ በመቸብቸብ መሃል ዳር እንዲሆን ካማድርግ አይመለስም። ስለሆንም “መሃል ዳር እንዳይሆን” መላው የኢትዮጵያ ህዝብ እንደቀድሞው ሁሉ ዛሬም እምቢ ለሃገሬ ለዳር ድንበሬ ብሎ ክንዱንና አንድነቱን አስተባብሮ በግፈኛው አገዛዝ ላይ መነሳቱና የግዛት አንድነቱንና ሰብአዊ ክብሩን ከማስጠበቅ ሌላ አማራጭ ይኖረዋል ብሎ መገመት የዋህነት ይሆናል።

በዳላስ እና ፎርትዎርዝ የቅንጅት ለአንድነትና ለ ዲሞክራሲ ፓርቲ ድጋፍ ቻፕተር በወያኔ መልካም ፈቃድ ለሱዳን የተሰጠውን የኢትዮጵንያ ግዛት በሚመለከት ይህ ድርጊት ፍጹም ሃላፊነት የጎደለውና ከሃገር ክህደት ወንጀል ተለይቶ የማይታይ በሃገር ላይ የተፈጸመ ደባ መሆኑን በማመን የከረረ ተቃውሞውን ያሰማል ። ከዚህም በተጨማሪ ይህን አምባገነናዊ የወያኔ ኢህአዴግ አሳፋሪና በሃገር ዳር ድንበር ላይ የተቃጣ ሴራ ለማጋለጥ እና የሱዳን መንግስትም በህገወጥ መንገድ ከያዘው የኢትዮጵያ ግዛት በአስቸኳይ ለቆ እንዲወጣ በሚደረገው ሁለገብ ጥረትና ትግል ሁሉ የበኩሉን ድርሻ በቆራጥነት ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን አበክሮ አየገለፀ፣ በሐገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሐገር የምንገኝ ኢትዮጵያውያን እንዲሁም መላው የኢትዮጵያ መለዮ ለባሽ ይህንን የወያኔ አሳፋሪ ድርጊት ለማጋለጥ እና በህገ-ወጥ መንገድ ግዛታችንን የያዘው የሱዳን ጦርም አካባቢን ለቆ እንዲወጣና ከመሬታችው ላይ በግፍ የተነሱትና የደረሱበት ያልታወቀው ወገኖቻችን ወደ ነበሩበት ቀያቸው እንዲመለሱ ለማስቻል ከመቸውም ጊዜ ይልቅ አሁን የተባበረ ክንዳችንን በወያኔው ዘረኛ አገዛዝ ላይ ማንሳት እንደሚገባ ለማስገንዘብ ይወዳል።

ድል ለ ኢትዮጵያ ህዝብ!!!!

በዳልስ የቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ፓርቲ ድጋፍ ቻፕተር
ዳላስ ሜይ10/2008





Related Posts

  1. Kinijit North America opposes land give away to Sudan
  2. Protest rally in DC against land giveaway to Sudan – June 2
  3. On Woyanne's handing over of Ethiopian land to Sudan – by Solomon Getaneh
  4. On Woyanne's handing over of Ethiopian land to Sudan – by Solomon Getaneh
  5. Ethiopians in Switzerland to commemorate May 15




Email This Post Email This Post | Add a comment Write a Comment

One Response to “Kinijit Dallas opposes giving Ethiopian land to Sudan”

  1. Alemu says:

    Bravo Texans!
    Tell Woyane that our solidarity is with our people. Woyane is giving Ethiopian lands for Tigray benefit.

    May 12th, 2008 at 11:58 am

Leave a Comment

To write your comment in Amharic or download Amharic fonts click here. አስተያየትዎን በአማርኛ ለመጻፍ እዚህ ይጫኑ:: ጽፈው ከጨረሱ በኋላ የጻፉትን ኮፒ አድርገው ወደዚህ ተመልሰው አስተያየት መስጫ ቦክስ ውስጥ ፔስት ያድርጉ:: ወይም ከዚህ በታች ያለውን በመጫን መልእክትዎትን በድምጽ መቅዳት ይችላሉ::



Archive




Ethiopian News & Opinion Journal







Recent Posts
  • Powers of Ten
  • Nomination for Ethiopian Review’s “2009 Person of the Year”
  • Over 2,200 children were adopted from Ethiopia this year
  • EDP officials in Tigray resign over Meles-Lidetu deal
  • Meles Zenawi: Ethiopia’s Idumaean
  • The missing 8.6 million Ethiopians, where art thou?
  • U.S. official gives lips service on repression in Ethiopia
  • Ethiopian ‘virgin land’ for sale
  • What do you expect from the coming elections in Ethiopia?
  • ONLF killed 985 Woyannes, burned 6 vehicles
  • Memher Zebene, Ethiopia’s Jimmy Swaggart?
  • Woyanne kangaroo court convicts alleged coup plotters
  • EPPF strives to fill the leadership gap
  • Yemen police detain 191 refugees from Ethiopia
  • Ethiopia is sliding deeper into authoritarian controls
  • Ethiopia’s regime tries to cover up a new famine
  • Hailu Shawel dines with Woyannes after surrender
  • Interview with EPPF Fighter (Part II)
  • Witness for the Future
  • ONLF killed 626 Woyanne troops in lastest fighting


©2009 Ethiopian Review
Publisher & Editor-in-Chief: Elias Kifle
Powered by WordPress