- ምኒሊክ ከኣድዋ በፊት
- menelik_awaj.jpg (106.73 KiB) Viewed 868 times
|
Beles wrote:
Beles wrote:ዮሃ
ምኒሊክ ለኤርትራ ለምን አልተዋጋም የሚል ስሞታ አቅርበህ የሚመስለኝን ለማለት ስሞክር ተሰርዞ ደረስኩበት:: ለማንኛውም ሰሞኑን በዚህ ጉዳይ እያሰብኩ ነበርና ከሞራል ግዴታና ወቅታዊ ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር (practical) ብለን ብንከፋፍላቸው ምናልባት የተሻለ መልስ እናገኝ ይሆናል:: ኢትዮጵያ በኤርtra ላይ የይገባኛል ጥያቄ ካላት ያ መብት ከግዴታ ጋርም የተያያዘ መሆን ይገባዋል:: ከግዴታው አንዱ ከባዕድ አገዛዝ መከላከል ነው:: ይህ አስተሳሰብ በተለይ በዛሬ ጊዜ ላይ ሆነን ስንመለከተው የበለጠ ትክክል ነው የሚል ግምት አለኝ:: ይህ እንግዲህ በኢኮኖሚም ሆነ ቤእውቀት በከፍተኛ ደረጃ የሰለጠነ አስተሳሰብና አመለካከትን ይጠይቃል:: ኢኮኖሚ ከፍተኛ የሆነ አስተዋጽዖ አለው:: በቀላሉ በግለሰብ ደረጃ እንኳን ኪስህ ሞላ ሲልና ሲጎል ከአንደበትህ የሚወጣው ድምጽ ይለያያል:: አንደኛው የሚለማመጥ ሲሆን ሌላኛው በራስ መተማመን ያለበት ጎርነን ያለ ነው:: ለአብዛናው ሰው ማለት ነው:: አንዳንድ ግን አሉ በድህነታቸውም ቢሆን ክብራቸውን አቅማቸው እስከቻለ ድረስ ለማስከበር ወደኋላ የማይሉ::
እንግዲህ ከዚ አንጻር ምንም እንኳን ምኒሊክ ጣሊያንን ባህር ውስጥ ገፍቶ በጣላቸው ብለን ብንመኝም አቅሙን ስናገናዝበው ግን የሰራው ስራ ምን ያህል ጀግንነት የተሞላበት እንደሆነ መጋንዘብ እንችላለን:: በየትኛውም መለኪያ ላይ የወቅቱን ጣሊያንና ኢትዮጵያን ብንመዝን ምኒሊክ ተሸንፎ እንደ ቴዎድሮስ ራሱን መግደል ነበረበት:: ምርኮኛ እንደማይሆን ጥርጥር የለውም:: ለዚህም ተዘጋጅቶ እንደሄደ ከአዋጁ ማንበብ ይቻላል:: የተገኘው ድል በሚኒሊክና በጦሩ የሂሊና ጥንካሬ የተገኘ (እምነት ካለህ እግዚአብሄር ታክሎበት) እንጂ ሰው በሚመካበት በገንዘብ, በዕውቀት, በጉልበት የተገኘ አይደለም:: ለዚህ ነው ይህ ድልና ለዚህ ድል ያበቁት ጀግኖች በታሪክ ወደር የማይገኝላቸው ድንቅ መባል የሚገባቸው::
አንድ ደጋግመው ኤርትራዊያን (ከየት እንዳመጡት አላውቅም) ኢትዮጵያውያን የኤርትራን መሬት እንጂ ህዝቡን አይፈልጉትም የሚባለው ነገር ነው:: ምንም እንኳን የኤርትራ መሬት በጣሊያን እጅ ቢወድቅም ኤርትራዊያን በኢትዮጵያ ውስጥ ያላቸውን ክብርና መብት ተነፍገው እንደማያውቁ በኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ ውስጥ የነበራቸውን ድርሻ በማየት መረዳት ይቻላል:: እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ እንዲያውም በኢትዮጵያ ላይ ከሌላው ኢትዮጵያዊ የበለጠ ሃብት, ስልጣንና ከዚያም ጋር ተያይዞ የሚመጣው መብት እንደነበራቸው ምስክር ሆነን ያየነው ነገር ነው:: በጣም የሚገርመው ኤርትራዊያን ይህንን መብት የተነጠቁት በነጻ አውጪዎቻቸው መሆኑ ነው::
Registered users: Bing [Bot], Bwendimu, Google [Bot], Google Adsense [Bot], Google Feedfetcher, Gurezza, Rhino, TurnitinBot [Bot]