Ethiopian News and Opinion Forum


Re: ምኒሊክና ኣድዋ

Postby Beles » 03 Mar 2012, 05:53


ዮሃ
በድጋሚ ኢትዮጵያ ለኤርትራ መዋጋት ነበረባት የሚለው ጥያቄህ ተገቢነት ያለው ነው:: ነገር ግን በሚኒሊክም ሆነ በኢትዮጵያ ላይ የምታወርደው ፍርድ ፍትህ የጎደለው ነው:: ሚኒሊክ ተጠያቂነት አለበት, ግን እሱ ብቻ አይደለም ተጠያቂነት ያለበት:: በወቅቱ ከጣላያን ጋር የተሰለፉ የኤርትራ አስካሪዎችና ለጣሊያን ያደሩ የትግራይ መኳንንት ለምሳሌ ከሚኒሊክ የበለጠ ተጠያቂነት ይኖርባቸዋል:: በኋይለስላሴም ሆነ በደርግም ጊዜ እንዲሁ:: ግን ኤርትራዊያኑና ትግሬዎቹ ተጠያቂነትን ለሌላው ማከናነብና እራሳቸውን ከተጠያቂነት ነፃ ማድረግ እንደሚያዋጣ ነገር አድርገው ይዘውታል:: ይህም ዛሬ በሌላው ህዝብ አመኔታን ከማሳጣቱም በላይ ለወደፊት ፍጥቻና ጦርነት መሰረት እየጣለ ይገኛል:: ምኒሊክ የሚጠየቀው በወቅቱ ራሱ በሰራው ነው እንጂ ሻቢያና ወያኔን በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ለከፈቱት ጦርነት ተጠያቂ አይሆንም:: ወደፊትም ለማይቀረው በባሕር በሩ ምክንያት ለሚነሳው ጦርነት ማለት ነው:: ሰው ለራሱ የፈለገውን ጊዜ ሊዋሽ ይችላል:: ለሌላ ሰው ግን ከአንድ ወይ ከሁለት ጊዜ በላይ በላይ ዋሽቶ ውጤት አያገኝበትም:: እንደ ዋሾና ቀጣፊ ተቆጥሮ, አመኔታ አጥቶ ከዚያ በኋላ ሁሉም ነገር ወደቁልቁል ይሆናል ማለት ነው:: አሁን ኤርትራ እንዳለው ማለት ነው::


yoha wrote:
Beles wrote:ዮሃ
ምኒሊክ ለኤርትራ ለምን አልተዋጋም የሚል ስሞታ አቅርበህ የሚመስለኝን ለማለት ስሞክር ተሰርዞ ደረስኩበት:: ለማንኛውም ሰሞኑን በዚህ ጉዳይ እያሰብኩ ነበርና ከሞራል ግዴታና ወቅታዊ ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር (practical) ብለን ብንከፋፍላቸው ምናልባት የተሻለ መልስ እናገኝ ይሆናል:: ኢትዮጵያ በኤርtra ላይ የይገባኛል ጥያቄ ካላት ያ መብት ከግዴታ ጋርም የተያያዘ መሆን ይገባዋል:: ከግዴታው አንዱ ከባዕድ አገዛዝ መከላከል ነው:: ይህ አስተሳሰብ በተለይ በዛሬ ጊዜ ላይ ሆነን ስንመለከተው የበለጠ ትክክል ነው የሚል ግምት አለኝ:: ይህ እንግዲህ በኢኮኖሚም ሆነ ቤእውቀት በከፍተኛ ደረጃ የሰለጠነ አስተሳሰብና አመለካከትን ይጠይቃል:: ኢኮኖሚ ከፍተኛ የሆነ አስተዋጽዖ አለው:: በቀላሉ በግለሰብ ደረጃ እንኳን ኪስህ ሞላ ሲልና ሲጎል ከአንደበትህ የሚወጣው ድምጽ ይለያያል:: አንደኛው የሚለማመጥ ሲሆን ሌላኛው በራስ መተማመን ያለበት ጎርነን ያለ ነው:: ለአብዛናው ሰው ማለት ነው:: አንዳንድ ግን አሉ በድህነታቸውም ቢሆን ክብራቸውን አቅማቸው እስከቻለ ድረስ ለማስከበር ወደኋላ የማይሉ::
እንግዲህ ከዚ አንጻር ምንም እንኳን ምኒሊክ ጣሊያንን ባህር ውስጥ ገፍቶ በጣላቸው ብለን ብንመኝም አቅሙን ስናገናዝበው ግን የሰራው ስራ ምን ያህል ጀግንነት የተሞላበት እንደሆነ መጋንዘብ እንችላለን:: በየትኛውም መለኪያ ላይ የወቅቱን ጣሊያንና ኢትዮጵያን ብንመዝን ምኒሊክ ተሸንፎ እንደ ቴዎድሮስ ራሱን መግደል ነበረበት:: ምርኮኛ እንደማይሆን ጥርጥር የለውም:: ለዚህም ተዘጋጅቶ እንደሄደ ከአዋጁ ማንበብ ይቻላል:: የተገኘው ድል በሚኒሊክና በጦሩ የሂሊና ጥንካሬ የተገኘ (እምነት ካለህ እግዚአብሄር ታክሎበት) እንጂ ሰው በሚመካበት በገንዘብ, በዕውቀት, በጉልበት የተገኘ አይደለም:: ለዚህ ነው ይህ ድልና ለዚህ ድል ያበቁት ጀግኖች በታሪክ ወደር የማይገኝላቸው ድንቅ መባል የሚገባቸው::
አንድ ደጋግመው ኤርትራዊያን (ከየት እንዳመጡት አላውቅም) ኢትዮጵያውያን የኤርትራን መሬት እንጂ ህዝቡን አይፈልጉትም የሚባለው ነገር ነው:: ምንም እንኳን የኤርትራ መሬት በጣሊያን እጅ ቢወድቅም ኤርትራዊያን በኢትዮጵያ ውስጥ ያላቸውን ክብርና መብት ተነፍገው እንደማያውቁ በኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ ውስጥ የነበራቸውን ድርሻ በማየት መረዳት ይቻላል:: እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ እንዲያውም በኢትዮጵያ ላይ ከሌላው ኢትዮጵያዊ የበለጠ ሃብት, ስልጣንና ከዚያም ጋር ተያይዞ የሚመጣው መብት እንደነበራቸው ምስክር ሆነን ያየነው ነገር ነው:: በጣም የሚገርመው ኤርትራዊያን ይህንን መብት የተነጠቁት በነጻ አውጪዎቻቸው መሆኑ ነው::



Beles !

ልጽፍ ጀምሬ የነበርው በኔ አመለካከት ሚኒሊክን እንደ ጀግና ሳይሆን እንደ አንድ ተራ መሃይም መሪ ነው የማያቸው ምክንያቱም ምንም ዛሬ ኤርትራና ትግራይ ህዝብ መቃቃር ቢኖርም የሁለት ህዝብ የዘር ግንድ አንድ ከመሆን አልፎም አንድ አገርም የነበረ ሲሆን በሚኒሊክ አማካኝንት ከጣሊያን ጋ ሶስት ግዜ መዋዋል ኢትዮጵያ ኤርትራን አጥታለች በሌላ መልኩ የአድዋ ድል ለየኢትዮጵያ ህዝብ እንደአኩሪነት የጠቀሳል በሌላው መልኩ ደግሞ ኤርትራ የኢትዮጵያ አካል ነበረች ካልንና የኤርትራ ህዝብ ለ70አመታት በጣሊያን ሲበደል እንደቆየ የሚገልጽ አንድም መጽሃፍ በኢትዮጵያ ታሪክ መጻህፍት ውስጥ የለም ታዲያ እንዴት አድርጎ ነው የህ ሁለት ተጻራሪ ጉዳይ አብሮ የሚሄደው ወይ ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ነበረች ያ ሃቅ ካልሆነ ደግሞ ኤርትራ ለ70 አመታት በቅኝ ስለዋለች የኢትዮጵያ አካል ላትሆን ነው ማለት ነው :: አይ አይሆንም ኤርትራ የኢትዮጵያ አካል ነው ብለን የምንካራከር ከሆነ እንግዲያውስ ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ውስጥ ቅይታለች ሊባል ያስችላል መቼም ይህ አባባል ብዙ ጉረኛ ኢትዮጵያውያንን ሊያስቆጣ ይችላል ይሁን እንጂ ሃቅ ከሚያንቀኝ እውነትን ማሳወቅና ማወቅ ያለብኝ ስለመሰለኝም ነው :: ይህ አባባል ምንም ጥቅም ላይኖረው ይችላል ምክንያቱም አሁን ኤርተራም አገር ስለሆነች ማለት ነው ቢሆንም ስህተት ከመሪዎች እንጂ ከህዝብ አይመጣም ከሚኒሊክ እስከ መለስ ኢትዮጵያ ምንም አኩሪ የመሪ ታሪክ የላትም የአድዋ ድልም የኢትዮጵያ ህዝብና አርበኞች ድል እንጂ የነሚኒሊክ ድል አይደለም በኔ አመለካከት ሚኒሊክ አሳፋሪ መሪ ነበሩም ባይ ነኝ በርግጥ ባለቤታቸው እቴጌ ጣይቱ አስተዋይና ብልህ እንደነበሩ ታሪክ ሁሌም ያወሳቸዋል :: በመጨረሻም ዛሬ የደረስንበት በኢትዮጵያ ህዝብና በኤርትራ ና በትግራይ ህዝብ ተለያይቶ መኖር ዋናው ተዋንያን ሚኒሊክ ለሱም ከጣሊያን ጋር ያደረጉት ውል ምስክር ነው :: እንዳውም ለዚህ ሁለት ወንድማማች ህዝብ ደም መፋሰስና ኢትዮጵያ አሁን ላለችበት ደረጃም በቅታለች::


በለስ ! ሚኒሊክ ለምን አልተዋጋም ለማለት አልነበረም አለመዋጋት በብዙ ጉዳይ ሊገለጽ ይቻላል ግን ህዝብንና አገርን የሚያክል ነገር ለ70አምት ትተህ በቅኝ ግዛት አልዋልኩም ነገር ግን የኤርትራን ህዝብ ኢትዮጵያዊ ስላልሆነ ለጣሊያን ፊርሞ ከመሽጥ ምን ይለየዋል, ለዚህም ነው በኢትዮጵያና ኤርተራ ህዝብ ያን ያህል ልዩነት ብሎም ደም መፋሰስ ያስከተለው መቼም ብዙ ኢትዮጵያዊ ሃቅን ስለማይወድ ሊከፉ ይችላሉ ኢትዮጵያ በጣልያን ተገዝታለች የአድዋ ድል አኩሪ ታሪክም ነው ለህዝቡ እንጂ ለመሪ ሳይሆን::



Re: ምኒሊክና ኣድዋ

Postby yoha » 03 Mar 2012, 16:38


Beles wrote:ዮሃ
በድጋሚ ኢትዮጵያ ለኤርትራ መዋጋት ነበረባት የሚለው ጥያቄህ ተገቢነት ያለው ነው:: ነገር ግን በሚኒሊክም ሆነ በኢትዮጵያ ላይ የምታወርደው ፍርድ ፍትህ የጎደለው ነው:: ሚኒሊክ ተጠያቂነት አለበት, ግን እሱ ብቻ አይደለም ተጠያቂነት ያለበት:: በወቅቱ ከጣላያን ጋር የተሰለፉ የኤርትራ አስካሪዎችና ለጣሊያን ያደሩ የትግራይ መኳንንት ለምሳሌ ከሚኒሊክ የበለጠ ተጠያቂነት ይኖርባቸዋል:: በኋይለስላሴም ሆነ በደርግም ጊዜ እንዲሁ:: ግን ኤርትራዊያኑና ትግሬዎቹ ተጠያቂነትን ለሌላው ማከናነብና እራሳቸውን ከተጠያቂነት ነፃ ማድረግ እንደሚያዋጣ ነገር አድርገው ይዘውታል:: ይህም ዛሬ በሌላው ህዝብ አመኔታን ከማሳጣቱም በላይ ለወደፊት ፍጥቻና ጦርነት መሰረት እየጣለ ይገኛል:: ምኒሊክ የሚጠየቀው በወቅቱ ራሱ በሰራው ነው እንጂ ሻቢያና ወያኔን በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ለከፈቱት ጦርነት ተጠያቂ አይሆንም:: ወደፊትም ለማይቀረው በባሕር በሩ ምክንያት ለሚነሳው ጦርነት ማለት ነው:: ሰው ለራሱ የፈለገውን ጊዜ ሊዋሽ ይችላል:: ለሌላ ሰው ግን ከአንድ ወይ ከሁለት ጊዜ በላይ በላይ ዋሽቶ ውጤት አያገኝበትም:: እንደ ዋሾና ቀጣፊ ተቆጥሮ, አመኔታ አጥቶ ከዚያ በኋላ ሁሉም ነገር ወደቁልቁል ይሆናል ማለት ነው:: አሁን ኤርትራ እንዳለው ማለት ነው::


yoha wrote:
Beles wrote:ዮሃ
ምኒሊክ ለኤርትራ ለምን አልተዋጋም የሚል ስሞታ አቅርበህ የሚመስለኝን ለማለት ስሞክር ተሰርዞ ደረስኩበት:: ለማንኛውም ሰሞኑን በዚህ ጉዳይ እያሰብኩ ነበርና ከሞራል ግዴታና ወቅታዊ ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር (practical) ብለን ብንከፋፍላቸው ምናልባት የተሻለ መልስ እናገኝ ይሆናል:: ኢትዮጵያ በኤርtra ላይ የይገባኛል ጥያቄ ካላት ያ መብት ከግዴታ ጋርም የተያያዘ መሆን ይገባዋል:: ከግዴታው አንዱ ከባዕድ አገዛዝ መከላከል ነው:: ይህ አስተሳሰብ በተለይ በዛሬ ጊዜ ላይ ሆነን ስንመለከተው የበለጠ ትክክል ነው የሚል ግምት አለኝ:: ይህ እንግዲህ በኢኮኖሚም ሆነ ቤእውቀት በከፍተኛ ደረጃ የሰለጠነ አስተሳሰብና አመለካከትን ይጠይቃል:: ኢኮኖሚ ከፍተኛ የሆነ አስተዋጽዖ አለው:: በቀላሉ በግለሰብ ደረጃ እንኳን ኪስህ ሞላ ሲልና ሲጎል ከአንደበትህ የሚወጣው ድምጽ ይለያያል:: አንደኛው የሚለማመጥ ሲሆን ሌላኛው በራስ መተማመን ያለበት ጎርነን ያለ ነው:: ለአብዛናው ሰው ማለት ነው:: አንዳንድ ግን አሉ በድህነታቸውም ቢሆን ክብራቸውን አቅማቸው እስከቻለ ድረስ ለማስከበር ወደኋላ የማይሉ::
እንግዲህ ከዚ አንጻር ምንም እንኳን ምኒሊክ ጣሊያንን ባህር ውስጥ ገፍቶ በጣላቸው ብለን ብንመኝም አቅሙን ስናገናዝበው ግን የሰራው ስራ ምን ያህል ጀግንነት የተሞላበት እንደሆነ መጋንዘብ እንችላለን:: በየትኛውም መለኪያ ላይ የወቅቱን ጣሊያንና ኢትዮጵያን ብንመዝን ምኒሊክ ተሸንፎ እንደ ቴዎድሮስ ራሱን መግደል ነበረበት:: ምርኮኛ እንደማይሆን ጥርጥር የለውም:: ለዚህም ተዘጋጅቶ እንደሄደ ከአዋጁ ማንበብ ይቻላል:: የተገኘው ድል በሚኒሊክና በጦሩ የሂሊና ጥንካሬ የተገኘ (እምነት ካለህ እግዚአብሄር ታክሎበት) እንጂ ሰው በሚመካበት በገንዘብ, በዕውቀት, በጉልበት የተገኘ አይደለም:: ለዚህ ነው ይህ ድልና ለዚህ ድል ያበቁት ጀግኖች በታሪክ ወደር የማይገኝላቸው ድንቅ መባል የሚገባቸው::
አንድ ደጋግመው ኤርትራዊያን (ከየት እንዳመጡት አላውቅም) ኢትዮጵያውያን የኤርትራን መሬት እንጂ ህዝቡን አይፈልጉትም የሚባለው ነገር ነው:: ምንም እንኳን የኤርትራ መሬት በጣሊያን እጅ ቢወድቅም ኤርትራዊያን በኢትዮጵያ ውስጥ ያላቸውን ክብርና መብት ተነፍገው እንደማያውቁ በኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ ውስጥ የነበራቸውን ድርሻ በማየት መረዳት ይቻላል:: እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ እንዲያውም በኢትዮጵያ ላይ ከሌላው ኢትዮጵያዊ የበለጠ ሃብት, ስልጣንና ከዚያም ጋር ተያይዞ የሚመጣው መብት እንደነበራቸው ምስክር ሆነን ያየነው ነገር ነው:: በጣም የሚገርመው ኤርትራዊያን ይህንን መብት የተነጠቁት በነጻ አውጪዎቻቸው መሆኑ ነው::



Beles !

ልጽፍ ጀምሬ የነበርው በኔ አመለካከት ሚኒሊክን እንደ ጀግና ሳይሆን እንደ አንድ ተራ መሃይም መሪ ነው የማያቸው ምክንያቱም ምንም ዛሬ ኤርትራና ትግራይ ህዝብ መቃቃር ቢኖርም የሁለት ህዝብ የዘር ግንድ አንድ ከመሆን አልፎም አንድ አገርም የነበረ ሲሆን በሚኒሊክ አማካኝንት ከጣሊያን ጋ ሶስት ግዜ መዋዋል ኢትዮጵያ ኤርትራን አጥታለች በሌላ መልኩ የአድዋ ድል ለየኢትዮጵያ ህዝብ እንደአኩሪነት የጠቀሳል በሌላው መልኩ ደግሞ ኤርትራ የኢትዮጵያ አካል ነበረች ካልንና የኤርትራ ህዝብ ለ70አመታት በጣሊያን ሲበደል እንደቆየ የሚገልጽ አንድም መጽሃፍ በኢትዮጵያ ታሪክ መጻህፍት ውስጥ የለም ታዲያ እንዴት አድርጎ ነው የህ ሁለት ተጻራሪ ጉዳይ አብሮ የሚሄደው ወይ ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ነበረች ያ ሃቅ ካልሆነ ደግሞ ኤርትራ ለ70 አመታት በቅኝ ስለዋለች የኢትዮጵያ አካል ላትሆን ነው ማለት ነው :: አይ አይሆንም ኤርትራ የኢትዮጵያ አካል ነው ብለን የምንካራከር ከሆነ እንግዲያውስ ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ውስጥ ቅይታለች ሊባል ያስችላል መቼም ይህ አባባል ብዙ ጉረኛ ኢትዮጵያውያንን ሊያስቆጣ ይችላል ይሁን እንጂ ሃቅ ከሚያንቀኝ እውነትን ማሳወቅና ማወቅ ያለብኝ ስለመሰለኝም ነው :: ይህ አባባል ምንም ጥቅም ላይኖረው ይችላል ምክንያቱም አሁን ኤርተራም አገር ስለሆነች ማለት ነው ቢሆንም ስህተት ከመሪዎች እንጂ ከህዝብ አይመጣም ከሚኒሊክ እስከ መለስ ኢትዮጵያ ምንም አኩሪ የመሪ ታሪክ የላትም የአድዋ ድልም የኢትዮጵያ ህዝብና አርበኞች ድል እንጂ የነሚኒሊክ ድል አይደለም በኔ አመለካከት ሚኒሊክ አሳፋሪ መሪ ነበሩም ባይ ነኝ በርግጥ ባለቤታቸው እቴጌ ጣይቱ አስተዋይና ብልህ እንደነበሩ ታሪክ ሁሌም ያወሳቸዋል :: በመጨረሻም ዛሬ የደረስንበት በኢትዮጵያ ህዝብና በኤርትራ ና በትግራይ ህዝብ ተለያይቶ መኖር ዋናው ተዋንያን ሚኒሊክ ለሱም ከጣሊያን ጋር ያደረጉት ውል ምስክር ነው :: እንዳውም ለዚህ ሁለት ወንድማማች ህዝብ ደም መፋሰስና ኢትዮጵያ አሁን ላለችበት ደረጃም በቅታለች::


በለስ ! ሚኒሊክ ለምን አልተዋጋም ለማለት አልነበረም አለመዋጋት በብዙ ጉዳይ ሊገለጽ ይቻላል ግን ህዝብንና አገርን የሚያክል ነገር ለ70አምት ትተህ በቅኝ ግዛት አልዋልኩም ነገር ግን የኤርትራን ህዝብ ኢትዮጵያዊ ስላልሆነ ለጣሊያን ፊርሞ ከመሽጥ ምን ይለየዋል, ለዚህም ነው በኢትዮጵያና ኤርተራ ህዝብ ያን ያህል ልዩነት ብሎም ደም መፋሰስ ያስከተለው መቼም ብዙ ኢትዮጵያዊ ሃቅን ስለማይወድ ሊከፉ ይችላሉ ኢትዮጵያ በጣልያን ተገዝታለች የአድዋ ድል አኩሪ ታሪክም ነው ለህዝቡ እንጂ ለመሪ ሳይሆን::


ታሪክ ሁለት አይነት ገጽታ አለው ክፉና ደግ ደጉን ብቻ መርጠን ልንጠቀምበት አንችልም አሁንም የኔ አባባል ብዙ ኢትዮጵያውያን በኤርትራውያን ላይ የሚሰጡት አመለካከት እናንተ ባንዶች ከጣሊያን ጋር አብራችሁ ተሰለፋችሁ የሚል ሌላው ደግሞ ሚኒልክ የጣሊያንን ጦር አሽንፎ ድል በድል ተቀዳጅቶ ግን ኤርትራ ሲደርስ ሰራዊቱ ስለታመመ መዋጋት አልቻለም ስለዚህ ያለው አማራጭ በኤርትራ ህዝብ ባርነት ግዞት መፈራረም ያውም ለ70 አመታት ያህል , የትግራይ መኻንንት ልትከስ አትሞክር የሚቻላቸውን ያህል አዋግተዋል ማለት ስንቅና ትጥቅ በማቅረብም አንጻር ሚኒሊክም የሸዋ ንጉስ ነው የነበረው ብዙ ግዜ ኢትዮጵያውያን ሃቅን ለመስማት ስለማንፈልግ የተጣመመ ታሪክን ነው ምንወደው ሚኒሊክ ጣሊያን መቀሌ ሊደርስ ሲል ነው ሰራዊት የላከው ለማንኛውም አሁን በሱ መከራከር አያስፈልገንም :: በሌላው መልኩ ሃይለስላሴ ይህ ጣሊያን ለሁለተኛ ሲመጣ ነው በአምስት አመቱ የኢትዮጵያ ቆይታው ማለት ነው እናም ሃይለስላሴ ሸሽቶ ውጭ አገር ነው የነበረው ከዛም በእንግሊዞች አመካኝነት ጣሊያን ኢትዮጵያን ሲለቅ እንደገና ለሁለትኛ ግዜ የኤርትራን ህዝብ ቁማር ተጫወተበት በመፈራረም ማለት ነው ደግሞስ ሃይለስላሴ እንደመሪ መቆጠር አለባቸው ግን ታሪክ ሃይለስላሴን የወቅቱ ጀግና አድርጎ ያወሳቸዋል ሳይዋጉና ሳያዋጉ ትተውት ለሄዱት ህዝብ ስለዚህ በኔ አባባል ጀግናው አርበኛውና በአጠቃላይ ህዝቡ ነበር :: አሁንም ምንም እንኻን ኤርትራ አብራን ባትሆንም ህዝቡ ግን ወንድማችን ለመሆኑ አጠያያቂ አይደለም በኔ አስተሳሰብ ወደፊት አብረን እንኖራለንም ባይ ነኝ ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ ታሪክ የኤርተራ ህዝብን ከመበደል አልፎም ይቅርታ እንኻን ባግባቡ አልጠየቀም ምክንያቱም የኤርትራ ህዝብ በደል ደርሶበታል በመሪዎች የተነሳ አሁን ላለው መለያየትም አብቅቶናልና
Last edited by yoha on 03 Mar 2012, 16:46, edited 1 time in total.



Re: ምኒሊክና ኣድዋ

Postby Semira » 03 Mar 2012, 16:43


Yoha/yohanes,

ከአጻጻፍህና ከውንጀላህ: ትግርኛ ተናጋሪ እንደሆንክ ለመገመት አያዳግትም:: ታላቁና አስተዋዩ ንጉስ ምኒሊከ አንተ ከበቀልክበት ቦታ ካልሆነ በስተቀር የትም ሲሰደብ አይተን አናውቅም:: በምኒሊክ ላይ ያወረድከው የስድብ ናዳ እና ውንጀላ: ታሪክ ካለማወቅህና በውስጥህ ባደረው ታላቅ ቅናት ሊሆን ይችላል:: ይህን ያልኩበት ምክንያት በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የምኒሊክን ያህል ታላቅ ድል: ኩራት: ተስፋ እና ብልጽግና ያስመዘገብ ኖሮም ሊኖርም አይችልም:: ይህንን ወደሃላ ልመለስበትና በምኒሊክ ግዜ የነበረውን የፖለቲካ ገጽታ ከነዚህ ሁለቱ የ ራስ አሉላ አረፍተ ነገሮች እንድትረዳ እፍልጋለሁ:: ራስ አሉላ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስት ምንም የተከበሩ ሰው ቢሆኑም: ከእጼ ዮሃንስ የማይለዩበት አንድ ባህርይ አላቸው: ይሀውም: የውጭ ሃይልን በመጋበዝ የሃገር ውስጥ ተፎካካሪን ማንበርከክ ነው:: የራስ አሉላ ደብዳቤ ለኢጣልይ ወራሪዎች ከተጻፉት መሃከል እነዚህ ሁለቱን አንብብና በግዜው የነበረውን የፓለቲካ ሽኩቻ ተረዻ:: ኤርትራን ለሽያጭ ያቀረቡት ራስ አሉላና የትግራይ ገዢዎች እንጂ አጼ ምኒሊክ አልነባሩም

But if he [Menilek] gives as a present what is out of his door [the Marab Mellash] the present is of no value.You want the country to the Mareb (Eritrean highlands) to cultitivate your gardens, to build your houses, to construct your churches....? We can give it to you. [And not menilek.] Let the Italian soldiers come to Adwa, I shall come to meet them like a friend. (1996, Ḥagai Erlikh, p. 164)


"And you (Italians), why do you need to look for distant friends? We are neighbors (meaning Medri Bahri and Tigray) and can serve each other. You want the road to be open and I want the road to be open. You should guard to the Mereb River and I will guard it to Gondar and even beyond Gondar. We must be able to go to the coast to trade in order that our country (meaning Tigray) would flourish, with the help of God, Menelik is too far to be of any use to you. Let us make friendship between us. (1996, Ḥagai Erlikh, 164)"


ከላይ እንዳየሀው ራስ አሉላ ሃገር በመስሽጥ ድርድር ላይ እንደነበሩ:: ይህን የመሰል ከውጭ ሀይል ጋር የማበር ክህደት ራስ አሉላ ብቻ ስይሆኑ: አጼ ዮሃንስም ከእንግሊዞች ጋር በማበር ያደራጉት ነው:: ይህ ብቻ ሳይሆን ከጣልያን ጋር በማበር ብዙ የትግራይ ራሶችና የራያ ሽፍቶች አጼ ምኒሊክ ላይ ብዙ ጉዳት አድርሰዋል:: ከ40 አመት በሓላም በፋሽስት ኢጣልያ ወረራ ግዜ እነ ሃይለስላሴ ጉግሳ እና ራስ ስዩም መንገሻ : ሌሎቹም ከውጭ ወራሪ ጋር በማበር ብዙ ጉዳት አድርሰዋል:: የነሱም የልጅ ልጆች እነመለስ ዜናዊ: በሽዋ አማራ ላይ ባላቸው ጥላቻ ብቻ ኢትዮጵያ የባህር በር እንዳኖራት ሽንጣቸውን ገትረው ተዋግተዋል:: እንግዲህ የኢትዮጵያ የውስጥ ችግር ይህን ይመስላል:: ይህ ሆኖ ሳለ:: ሃገርን አሰባስቦ: አውሮፕላንና ተሽከርካሪ በሌለበት ዘመን ከ1000 ኪሎ ሜትር በላይ ለስድስት ወር ያህል ተጉዞ አውሮፓዊ ሃይልን ድባቅ የመታ መሪና አመራርን በተራ ቑንቓ ማጥላላት የአጥላዩን ግላሰብ ተራ እና የዘቀጠ እንዲሁም ደሃ የሆነ ባዶ አእምሮውን ያሳያል:: Unlike the leadership after him, Menlik played the game right well and managed to defeat colonial power and stay in it till he dies. when ras alula and his budies were negotiating to sell mereb milash for Italia, Minilik said to them so bit and went ahead on his business than calling ሃገር አትገነጠልም: አንገት አትቆረጥም:: Hundred years latter, the illitrate mengistu wasn't smart enough to figure out who he has to deal first. when the children of Tigray bandas say the question of Eritrea is colonialism, mengistu could have said, "yes you are right, so be it" than pouring his meagre resources there and lose unceremonously to give the bandas the arat-killo palace they dreamt for more than 150 years
Last edited by Semira on 03 Mar 2012, 17:20, edited 1 time in total.



Re: ምኒሊክና ኣድዋ

Postby yoha » 03 Mar 2012, 17:20


Semira wrote:Yoha/yohanes,

ከአጻጻፍህና ከውንጀላህ: ትግርኛ ተናጋሪ እንደሆንክ ለመገመት አያዳግትም:: ታላቁና አስተዋዩ ንጉስ ምኒሊከ አንተ ከበቀልክበት ቦታ ካልሆነ በስተቀር የትም ሲሰደብ አይተን አናውቅም:: በምኒሊክ ላይ ያወረድከው የስድብ ናዳ እና ውንጀላ: ታሪክ ካለማወቅህና በውስጥህ ባደረው ታላቅ ቅናት ሊሆን ይችላል:: ይህን ያልኩበት ምክንያት በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የምኒሊክን ያህል ታላቅ ድል: ኩራት: ተስፋ እና ብልጽግና ያስመዘገብ ኖሮም ሊኖርም አይችልም:: ይህንን ወደሃላ ልመለስበትና በምኒሊክ ግዜ የነበረውን የፖለቲካ ገጽታ ከነዚህ ሁለቱ የ ራስ አሉላ አረፍተ ነገሮች እንድትረዳ እፍልጋለሁ:: ራስ አሉላ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስት ምንም የተከበሩ ሰው ቢሆኑም: ከእጼ ዮሃንስ የማይለዩበት አንድ ባህርይ አላቸው: ይሀውም: የውጭ ሃይልን በመጋበዝ የሃገር ውስጥ ተፎካካሪን ማንበርከክ ነው:: የራስ አሉላ ደብዳቤ ለኢጣልይ ወራሪዎች ከተጻፉት መሃከል እነዚህ ሁለቱን አንብብና በግዜው የነበረውን የፓለቲካ ሽኩቻ ተረዻ:: ኤርትራን ለሽያጭ ያቀረቡት ራስ አሉላና የትግራይ ገዢዎች እንጂ አጼ ምኒሊክ አልነባሩም

But if he [Menilek] gives as a present what is out of his door [the Marab Mellash] the present is of no value.You want the country to the Mareb (Eritrean highlands) to cultitivate your gardens, to build your houses, to construct your churches....? We can give it to you. [And not menilek.] Let the Italian soldiers come to Adwa, I shall come to meet them like a friend. (1996, Ḥagai Erlikh, p. 164)


"And you (Italians), why do you need to look for distant friends? We are neighbors (meaning Medri Bahri and Tigray) and can serve each other. You want the road to be open and I want the road to be open. You should guard to the Mereb River and I will guard it to Gondar and even beyond Gondar. We must be able to go to the coast to trade in order that our country (meaning Tigray) would flourish, with the help of God, Menelik is too far to be of any use to you. Let us make friendship between us. (1996, Ḥagai Erlikh, 164)"


ከላይ እንዳየሀው ራስ አሉላ ሃገር በመስሽጥ ድርድር ላይ እንደነበሩ:: ይህን የመሰል ከውጭ ሀይል ጋር የማበር ክህደት ራስ አሉላ ብቻ ስይሆኑ: አጼ ዮሃንስም ከእንግሊዞች ጋር በማበር ያደራጉት ነው:: ይህ ብቻ ሳይሆን ከጣልያን ጋር በማበር ብዙ የትግራይ ራሶችና የራያ ሽፍቶች አጼ ምኒሊክ ላይ ብዙ ጉዳት አድርሰዋል:: ከ40 አመት በሓላም በፋሽስት ኢጣልያ ወረራ ግዜ እነ ሃይለስላሴ ጉግሳ እና ራስ ስዩም መንገሻ : ሌሎቹም ከውጭ ወራሪ ጋር በማበር ብዙ ጉዳት አድርሰዋል:: የነሱም የልጅ ልጆች እነመለስ ዜናዊ: በሽዋ አማራ ላይ ባላቸው ጥላቻ ብቻ ኢትዮጵያ የባህር በር እንዳኖራት ሽንጣቸውን ገትረው ተዋግተዋል:: እንግዲህ የኢትዮጵያ የውስጥ ችግር ይህን ይመስላል:: ይህ ሆኖ ሳለ:: ሃገርን አሰባስቦ: አውሮፕላንና ተሽከርካሪ በሌለበት ዘመን ከ1000 ኪሎ ሜትር በላይ ለስድስት ወር ያህል ተጉዞ አውሮፓዊ ሃይልን ድባቅ የመታ መሪና አመራርን በተራ ቑንቓ ማጥላላት የአጥላዩን ግላሰብ ተራ እና የዘቀጠ እንዲሁም ደሃ የሆነ ባዶ አእምሮውን ያሳያል:: for the record, this is what minilik said about highland Eritrea


አንተ ምታወራው በዮሃንስ ግዜ የነበረውን ነው በአድዋ ጦርነት ዮሃንስ በህይወት የለም 1900 , 1902, 1906 ሶስት ውልና ድርድር በሚኒሊክ እንጂ በዮሃንስና አሉላ አልነበረም ሲጀመር አሉላ የዮሃንስ ጦር አዛዥ እንጂ ንጉስ አልነበረም ቀደም ብዬም ያሳሰብኩት ኢትዮጵያውያን መጥፎውን ታሪክ ሽፋፍነንና አድበስብሰን ማለፍ ነው ምርጫችን አንተም ይህንን ነው የመረጠከው ቶሎ ብልህ እኔን አንተ ትግርኛ ተናጋሪ ስለሆንክ በማለት ለተሰራው ጥፋት ማባበያ ነው የመረጥከው እንግዲያውማ ለነዚህ ሚኒሊክ ለፈረመባቸው ሶስት ፊርማዎች ማለት ኤርትራውያንን አሳልፎ በመስጠት ይቅርታ የሌለው ጥፋትን ከመፈጸም አልፎ የኤርትራ ህዝብ የኢትዮጵያ አካል ለመሆኑም አይገልጽም ያድዋን ድል ግን ሲሞገስበት ይኖራል እረ ተወው የጅቡቲንስ ህዝብ በመሸጥስ ማን ጠየቀው ያንን ሁሉ ጥፋት የሰራው ሚኒሊክ አይደለም ሌላ መሪ በአገር መሸጥ የሚጠየቅ ምናልባት መለስ ሊሆን ይችላል ያም የኢትዮጵያ ታሪክ ኤርትራን የሚያካልል ከሆነ ማለት ነው በኔ በኩል ግን ከአጼ ቴድሮስ አስከ ቀዳማዊ ሃይለስላሴ የሚለው ታሪክ ላይ እንኻን የኤርትራ ማንነት አልተጠቀሰም የኔ ወንድም ሰውን በማንነቱ ከመክሰስ የተሳሳተ ታሪክን ማረም ተገቢ ይመስላኛል ምክንያቱም ያ በወቅቱ ያልታረመ ታሪክ ብዙ ሰብአዊና ንዋታዊ ሃብትን አሳጥቶ አገርንና ህዝብን ያክል አሳጥቶናል አሁንም ካልታረመ ሌላም ሳያሳጣን አይቀርም ማለት አንደነ ኦጋዴን የመሳሰሉትን ::



Re: ምኒሊክና ኣድዋ

Postby Semira » 03 Mar 2012, 17:31


ወዳጄ : ምኒሊክን ምን አድርግ እንደምትለው አይገባኝም:: መጀመርያውኑ ጣልያን ምጽዋ እንዲረግጥ እና እንዲደራጅ የፋቀዱት እኮ እነ አጸ ዮሃንስ እና ራስ አሉላ ናቸው:: ሁዋላ ጣልያን የኤርትራ ሃማሴኖችን እያስታጠቀ ሲያስቸግራቸው ዶጋሊ እና ሌላም ቦታ ላይ ጣልያንን ወጉት እንጂ ጣልያን ሲመጣ እንደ እንግሊዝ የሚረዳቸው መስሎኧቸው ነበር:: ለምሳሌ: እጤ ዮሃንስ መቶ ሺህ የሚያህል የጎንደርና የትግራይን ጦር ኣሰልፈው ጣልያንን አስመራ ላይ ከበውት እንዳልነበረ ማድረግ ሲችሉ ባልታወቀ ሁኔታ ለቀውት ዘመቻቸውን ሰረዙት:: በኣጼ ምኒሊክ ግዜ እኮ እንኩአን ኤርትራ ሰስው: የትግራይም ስው እኮ ከጣልያን ጋር እየደነስ ነበር:: ይህንን የታጠቀ እኤርትራ አዝካሪ ደስ ብሎት ፎቶ ሲነሳ ተመልከተው:: ይህንን ነው ምኒሊክ ነጻ እንዲያወጣው የምትፋልገው?
Attachments
askaris.JPG
askaris.JPG (37.78 KiB) Viewed 544 times



Re: ምኒሊክና ኣድዋ

Postby yoha » 03 Mar 2012, 18:44


Semira wrote:ወዳጄ : ምኒሊክን ምን አድርግ እንደምትለው አይገባኝም:: መጀመርያውኑ ጣልያን ምጽዋ እንዲረግጥ እና እንዲደራጅ የፋቀዱት እኮ እነ አጸ ዮሃንስ እና ራስ አሉላ ናቸው:: ሁዋላ ጣልያን የኤርትራ ሃማሴኖችን እያስታጠቀ ሲያስቸግራቸው ዶጋሊ እና ሌላም ቦታ ላይ ጣልያንን ወጉት እንጂ ጣልያን ሲመጣ እንደ እንግሊዝ የሚረዳቸው መስሎኧቸው ነበር:: ለምሳሌ: እጤ ዮሃንስ መቶ ሺህ የሚያህል የጎንደርና የትግራይን ጦር ኣሰልፈው ጣልያንን አስመራ ላይ ከበውት እንዳልነበረ ማድረግ ሲችሉ ባልታወቀ ሁኔታ ለቀውት ዘመቻቸውን ሰረዙት:: በኣጼ ምኒሊክ ግዜ እኮ እንኩአን ኤርትራ ሰስው: የትግራይም ስው እኮ ከጣልያን ጋር እየደነስ ነበር:: ይህንን የታጠቀ እኤርትራ አዝካሪ ደስ ብሎት ፎቶ ሲነሳ ተመልከተው:: ይህንን ነው ምኒሊክ ነጻ እንዲያወጣው የምትፋልገው?




ይህ 5000 የታጠቀ ጦር ተገልብጦ ለዛ ድል እንዳበቃ ግን ታሪክ አይገልጸውም ምክንያቱም የተሰራውን ጥፋት ለመሸፋፈን ሲባል ነው ይህ ፎቶ ነጮች የተረኩት እንጂ እኛማ ያኔ ብዙም የተማረ አካልም አልነበረን ሚኒሊክም መሃይም ነበሩ ያ መሃይምነታቸው ነበር ሳይውቁ ዝም ብለው በመፈረም አገር ሲሸጡ የኖሩት " ለምልክት እንዲሆን" የባሻ አዋሎምን ታሪክ ተመልከት ለጣሊያን መሸነፍ እነዚ ፎቶ ላይ ያሉት ምን ያህል ጥቅም እንዳበረከቱ ታውቃለህ ባይ ንኝ :: አሁንም ኤርትራውያን ላይ ላደረስነው የ70 አመታት ውርደት ምንከሰው እነሱን ከሆነ መገንጠላቸው ተገቢ ሳይሆን አይቀርም ደግሞስ ባገር ላይ ከባእድ ጋር ውልና ድርድር ማደረግስ መለኪያው ምን ሊሆን ነው ባንተ አስተሳሰብ ሚኒሊክ ተዋጋላቸው ልትለኝ እንዳይሆን ፈርቻለሁ አሉላማ ሚቻለውን ሞክሮ ነበር ጣላት በዝቶበት ካልሆነ አንዱም ጠላት ሚኒሊክ ነበር ምክንያቱም ሚኒሊክ የዮሃንስ ገባሪ ሆኖ ዮሃንስ ደርቡሽን ሲዋጋ ሚኒሊክ በአፈር መሬት የጦር መሳሪያ ሲያከማች ነበር ይህም ታሪክ ነው ሚኒሊክ ይህንን ሁለት ትግርኛ ተናጋሪ ህዝብ ለመነጣጠል ያላረገው የለም ለዚም ነው ሁለት ትግርኛ ክፍለ ሃገር የነበረው ሃይለስላሴም ኤርትራን በስጦታ ተረክበው ያንኑ መከፋፈል ነበር ስራቸው በዛው መጠንም ያመጣባቸውን ጦስ አይተናል ለኛም ለዛሬው ትውልድ ሞልቶ ተርፎናል::


አንድ ጥያቄ አለኝ ኤርትራም ሆነች ህዝቡ አካላችን ከነበረ ለምን አልተዋጋንለትም ? ጭራሹንስ የኢትዮጵያ ታሪክ ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ሳር ያልዋለች ብሎ ያአምስት አመት የጣሊያን ኢትዮጵያ ውስጥ ቆይታን እንጂ የ70 አመት ኤርትራ ቆይታው ማናቸውም የኢዮጵያ መጻህፍት አይገልጹትም ታዲያ በዚህ ብቻ ኤርትራውያን ከኛ ለመለየት የሚያስችል ስህተት የተሰራስ አይመስልሀም?



Re: ምኒሊክና ኣድዋ

Postby Semira » 03 Mar 2012, 23:38


yoha wrote:አሉላማ ሚቻለውን ሞክሮ ነበር ጣላት በዝቶበት ካልሆነ አንዱም ጠላት ሚኒሊክ ነበር ምክንያቱም ሚኒሊክ የዮሃንስ ገባሪ ሆኖ ዮሃንስ ደርቡሽን ሲዋጋ ሚኒሊክ በአፈር መሬት የጦር መሳሪያ ሲያከማች ነበር ይህም ታሪክ ነው ሚኒሊክ ይህንን ሁለት ትግርኛ ተናጋሪ ህዝብ ለመነጣጠል ያላረገው የለም ለዚም ነው ሁለት ትግርኛ ክፍለ ሃገር የነበረው ሃይለስላሴም ኤርትራን በስጦታ ተረክበው ያንኑ መከፋፈል ነበር ስራቸው በዛው መጠንም ያመጣባቸውን ጦስ አይተናል ለኛም ለዛሬው ትውልድ ሞልቶ ተርፎናል::


ወዳጄ: ሳታውቀው ማንነትህን ገልጽህ:: ከወያኔ ድንጋይ ማምረቻ ኮሌጀ(civil service college) እንደተመረቅህ ራስን አጋለጥህ:: ምክንያቱም: ይህ አንተ የምታወራው : ምኒሊክ ሁለቱን ትግርኛ ተናጋሪዎች ለመለየት ያደረገው ነው የምትለው የህጻን ወሬ መለስ ዜናዊና ስብሃት ነጋ የጻፉልህ ነው:: ሃቁ ግን በትግራይና በትግርኛ ተናጋሪ ኤርትራውያን መሃከል የነበረው ጸብ ምኒሊክ የፈጠረው ሳይሆን ስር ሰዶ የነበረና ልክ እንደአሁኑ ግዜ የትግራይ ገዚዎች ለማስገበር ብዙ ግዜ የዘመቱበትና በኤርትራ የምይወደድ ጉዳይ ነበር:: ለምሳሌ ራስ አሉላ በዮሃንስ ትዛዝ ምድረ ኤርትራን እየወራሩ ሕዝቡን ያሽብሩት እንደነበር ታሪክ ይነግረናል:: እንድያውም: በአድዋ ውጋያ የተማረኩትን ኤርትራውያን አስካሪዎችን ምኒሊክ ምህረት ለማድረግ ባሰቡ ግዜ ከወገኖችህ ከትግራይ ገዚዎች ብዙ ተቃውሞ ደርሶባቸዋል:: እውነት ምኒሊክ እናንተ እንደምትሉት ከፋፋይ ቢሆን: እስካሪዎችን በ40 ግርፋት ብቻ ነጻ ሊያወጣቸው ነበር:: ወገኖችህ ግን እናዚያን ማስኪን ኤርትራውያን ነፍሳቸውን ካላጠፋን ወይ ፍንክች ስለማለታቸው ታሪክ ዘግቦታል:: ነገሩ ይህ ሆኖ ሳለ ያንተው ወገኖች የኤርትራውያን ጠላት ሆነው ሳሉ ምንሊክን የኤርትራውያን ጠላት እድርገህ ማቅረብህ የመለስ ዜናዊ ምሩቅ ካድሬ መሆንህን ይገልጻል::

ሌላው ደግሞ: ምኒሊክን በመተማ ዘመቻ ከዮሃንስ ጋር ባለመዝመቱ ከምትወነጅል: ለቴዎድሮስ ሞት ዋና ምክንያት የሆነውን ዮሃንስን ከመውቀስ ለምን እንደተቆጠብክ ሰው ሊጠይቅህ እንደሚችል ልብ አድርግ:: እነ ራስ አሉላና የትግራይ ራሶች ምኒሊክን ለማቃት ለጣልያን ምድረ ኤርትራን እንደገጸ በረከት ያሰጡበትን የታሪክ ማስረጃ ለጥፌልህ ነበር:: ነገር ግን መልስ ስለሌለህ ዝምብለህ ዘለልከው:: ለኤርትራውያን አዝካሪዋች ከጣልያን : ከቱርክ ከዝያም በፊት ከግብጾች ጋር መተባበር ዋናው ተጠያቂዎች የወገኖችህ የትግራይ ገዢዎች ጭካኔ የተሞላበት የማያቅዋርጥ ወረራ እንጂ አንተ እንደዘባረቅከው ምኒሊክ አይደለም::



Re: ምኒሊክና ኣድዋ

Postby yoha » 04 Mar 2012, 02:27


Semira wrote:Yoha/yohanes,

ከአጻጻፍህና ከውንጀላህ: ትግርኛ ተናጋሪ እንደሆንክ ለመገመት አያዳግትም:: ታላቁና አስተዋዩ ንጉስ ምኒሊከ አንተ ከበቀልክበት ቦታ ካልሆነ በስተቀር የትም ሲሰደብ አይተን አናውቅም:: በምኒሊክ ላይ ያወረድከው የስድብ ናዳ እና ውንጀላ: ታሪክ ካለማወቅህና በውስጥህ ባደረው ታላቅ ቅናት ሊሆን ይችላል:: ይህን ያልኩበት ምክንያት በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የምኒሊክን ያህል ታላቅ ድል: ኩራት: ተስፋ እና ብልጽግና ያስመዘገብ ኖሮም ሊኖርም አይችልም:: ይህንን ወደሃላ ልመለስበትና በምኒሊክ ግዜ የነበረውን የፖለቲካ ገጽታ ከነዚህ ሁለቱ የ ራስ አሉላ አረፍተ ነገሮች እንድትረዳ እፍልጋለሁ:: ራስ አሉላ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስት ምንም የተከበሩ ሰው ቢሆኑም: ከእጼ ዮሃንስ የማይለዩበት አንድ ባህርይ አላቸው: ይሀውም: የውጭ ሃይልን በመጋበዝ የሃገር ውስጥ ተፎካካሪን ማንበርከክ ነው:: የራስ አሉላ ደብዳቤ ለኢጣልይ ወራሪዎች ከተጻፉት መሃከል እነዚህ ሁለቱን አንብብና በግዜው የነበረውን የፓለቲካ ሽኩቻ ተረዻ:: ኤርትራን ለሽያጭ ያቀረቡት ራስ አሉላና የትግራይ ገዢዎች እንጂ አጼ ምኒሊክ አልነባሩም

But if he [Menilek] gives as a present what is out of his door [the Marab Mellash] the present is of no value.You want the country to the Mareb (Eritrean highlands) to cultitivate your gardens, to build your houses, to construct your churches....? We can give it to you. [And not menilek.] Let the Italian soldiers come to Adwa, I shall come to meet them like a friend. (1996, Ḥagai Erlikh, p. 164)


"And you (Italians), why do you need to look for distant friends? We are neighbors (meaning Medri Bahri and Tigray) and can serve each other. You want the road to be open and I want the road to be open. You should guard to the Mereb River and I will guard it to Gondar and even beyond Gondar. We must be able to go to the coast to trade in order that our country (meaning Tigray) would flourish, with the help of God, Menelik is too far to be of any use to you. Let us make friendship between us. (1996, Ḥagai Erlikh, 164)"


ከላይ እንዳየሀው ራስ አሉላ ሃገር በመስሽጥ ድርድር ላይ እንደነበሩ:: ይህን የመሰል ከውጭ ሀይል ጋር የማበር ክህደት ራስ አሉላ ብቻ ስይሆኑ: አጼ ዮሃንስም ከእንግሊዞች ጋር በማበር ያደራጉት ነው:: ይህ ብቻ ሳይሆን ከጣልያን ጋር በማበር ብዙ የትግራይ ራሶችና የራያ ሽፍቶች አጼ ምኒሊክ ላይ ብዙ ጉዳት አድርሰዋል:: ከ40 አመት በሓላም በፋሽስት ኢጣልያ ወረራ ግዜ እነ ሃይለስላሴ ጉግሳ እና ራስ ስዩም መንገሻ : ሌሎቹም ከውጭ ወራሪ ጋር በማበር ብዙ ጉዳት አድርሰዋል:: የነሱም የልጅ ልጆች እነመለስ ዜናዊ: በሽዋ አማራ ላይ ባላቸው ጥላቻ ብቻ ኢትዮጵያ የባህር በር እንዳኖራት ሽንጣቸውን ገትረው ተዋግተዋል:: እንግዲህ የኢትዮጵያ የውስጥ ችግር ይህን ይመስላል:: ይህ ሆኖ ሳለ:: ሃገርን አሰባስቦ: አውሮፕላንና ተሽከርካሪ በሌለበት ዘመን ከ1000 ኪሎ ሜትር በላይ ለስድስት ወር ያህል ተጉዞ አውሮፓዊ ሃይልን ድባቅ የመታ መሪና አመራርን በተራ ቑንቓ ማጥላላት የአጥላዩን ግላሰብ ተራ እና የዘቀጠ እንዲሁም ደሃ የሆነ ባዶ አእምሮውን ያሳያል:: Unlike the leadership after him, Menlik played the game right well and managed to defeat colonial power and stay in it till he dies. when ras alula and his budies were negotiating to sell mereb milash for Italia, Minilik said to them so bit and went ahead on his business than calling ሃገር አትገነጠልም: አንገት አትቆረጥም:: Hundred years latter, the illitrate mengistu wasn't smart enough to figure out who he has to deal first. when the children of Tigray bandas say the question of Eritrea is colonialism, mengistu could have said, "yes you are right, so be it" than pouring his meagre resources there and lose unceremonously to give the bandas the arat-killo palace they dreamt for more than 150 years


[color=#800000]አሁንም ደገመከው ቅናት ሲጀመር ቅናትን እዚ ምን አመጣው ታሪክን ለመቃወም ዘርን አይጠይቅም በርግጥ አንዳንድ ትግርኛ ተናጋሪ ግለሰቦች ለሚኒሊክ ያላቸው አስተያየት ለየት ሊል ይችላል በደፈናው ሁሉንም መፈረጅ ግን ከዘረኝነት አይለይም በግምት ሁለታችንም በሚኒሊክ ግዜ የነበርን አልመሰለአኝም ከተሳሳትኩ ይቅርታ ይህ በጽሁፍ የተደገፈ ነጭ ለንጉሶች እንዲመች የጻፈውን ለኔ ማሳየቱ እኔን እንደ ባዕድ ከማሰብ አይለይም እንዳልኩትም ታሪክ ሁለት ግጽታ አለው የተለያየ ሰውም የተለያየ ሃሳብ ሊኖረው ባህሪያዊም ነው እንኻን እኔና አንተ መፅሃፍ ቅዱስ ላይም የደቀመዛሙርቱ ሃሳብ አንዱ ካንዱ ልዩነት ነበረው ምንም እንኻን ማን ያናገር የነብረ ቢባል በቦታው የነበረም የሃሳብ ልዩነት ሊኖረው ይችላል እንደማውቀው ግን የሁለተኛው ጣሊያን ወረራ ንጉስ ሃይለስላሴ ለመሸሻቸው በብዛት አርበኛው የሚናገርበት ጉዳይ ሆኖ ሳለ የኢትዮጵያ ታሪክ ግን እንደተዋጉ ነው የሚያሳየው እረ ፎቶም አለው ሃቁ ግን ሌላ ነበር ይህንን ብዙ ሰዎች ይከፉበታል ምክንያቱም ሃቅን መቀበል ከባድ ስለሆነ :: Look I am Amharic speaking person originally and I also speaking Tigrigna but my parents are from semen shoa Ankoner and menez, would that make any difference . አሁንም ልድገመው ውል የተፈጻመው በሚኒሊክ እንጂ አሉላ የዮሃንስ አገልጋይ እንጂ ወሳኝነት ተራ አልነበረውም ለምን ጥፋትን ልንሸፋፍን አንሞክራል ይቅርታ ማለት ሽንፈት አይደለም እንዳውም የጥፋትን ክብደት ያቀለዋል መንግስቱ መጥፎ መሪ ነበር አዎ ይሁን እንጂ እኛም ከሱ የተሻለን አልነበርም {በኤርትራ ጉዳይ} ማለቴ ነው ወያኔም ላደረገው ስንት ተቃውሞ ነበር የገጠመው ምክንያቱም ህዝብና መንግስት ስለማይተዋወቅ የፈለጉትን በማን አለብኝነት ሰለሚፈጽሙ መጪው ትውልድ የክፉም ሆነ ደግ ታሪክ ተረካቢ ሲሆን አይተናል ለዚህም ነው የኤርትራ ሲገርመን የኦሮሞ ጥያቄ መጣ ያም ችግር መሪዎች የፈጸሙት አይደለም ኦሮሞስ ማንን ነው የሚከሰው ሚኒሊክን አይደለም አሁን ደግሞ ኦሮምኛ ተናጋሪ ነህ እንዳትለኝ ስንቱ ተወርቶ ባጠቃላይ የኢትዮጵያ ችግር ዘር ሃይማኖት አልነበረም በወቅቱ በጥያቄና መልሰ ወይም በይቅርታ ተዘግተው ቢሆን ኖሮ የዛሬው ትውልድ የነጻ ዜጋ ትውልድ ሊሆን በቻለ የወያኔ ትግል ትክክለኛ ነበር አልነበረም ለሚለው በኔ በኩል የበደልና መብትን ለማስከበር ስለነበር ትክክል ነው ባይ ነኝ ነገር ግን ይዞታውና ውስጠ ሚስጥሩ ትክክል አይደለም አራት ኪሎ ገብተው በትክክል ቢመሩን ማን አስተዳደረ ትርጉም አይሰጥም ነበር እነሱም መንግስቱን መስለው እንዳውም ሳይብሱ ይቀራል ብለህ ነው ግን ትግሬ ስለሆኑ አይደለም እንደዛ ቢሆንማ ስንት ደሃ ትግሬ አለ አይደል ባልሰራው ሃጢአት ሲሰደብ የሚውል ይቅርታ በዘር አላምንም መለስ በሰራው {ወያኔ} ሁሉም ትግሬ ተጠያቂ መሆን የለበትም ወያኔ ዘረኛ ነው አይደለም ምንም አያጠያይቅም ለማጠናቀቅ እንዲሆነኝ የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኝነት ታሪክ አኩሪ ቅርስ ነው ይሁን እንጂ አርበኛውና ህዝቡ ብቻ ነው ሊመሰገን ሚገባው ሚኒሊክ,ሃይለስላሴም,መንግስቱ አሁን ደግሞ መለስ ያገር ጠንቅና ለትውልድ እርግማን ነቸው :: ላንተ ማሳስብህ ቶሎ ውሳኔ ላይ አትድረስ በዘሩ የሚኮራ እንጂ የሚያፍር ካለ ሰው መሆኑ አጠራጣሪ ነው ይህ አባባሌ ትግሬም ብሆን ሱማሌ ደስተኛ ባደረገኝ ግን አይደለሁም ዘርኝነት እንጂ የዘር መጥፎ የለውም ::



Re: ምኒሊክና ኣድዋ

Postby Beles » 04 Mar 2012, 02:42


የሃ
ከምትለው አንድ የምስማማው ነገር አለ::ታርክን የምንማርበት ምክንያት አለው:: ከስህተቱ እንድንማርበት ነው:: ለዚህ ደግሞ ደጉም ክፉውም አብሮ መስተማር አለበት:: በዚህ በኩል የኢትዮጵያ ታሪክ አስተማሪዎች የታሪክ ትምህርት ጥቅሙን አልተረዱትም ማለት እንችላለን:: የታሪክ ደግ ደጉን ብቻ ተነግሮ በአዲሱ ትውልድ ላይ በራስ መኩራትንና መተማመንን ማምጣትን ብቻ እንደግብ ያዩ ይመስለኛል:: የዮሃንስን ከሃዲነት, የሚኒሊክን ስህተት, የቴዎድሮስን ጨካኝነት ሳይዘግቡ የሚያልፉት ለዚህ ይመስለኛል:: በተለይ በተለይ አንድ ያላደረጉት ነገር ከአንድ ጎሳ የመጣን መሪ ኮንነው ከአንድ ጎሳ የመጣን አሞግሰው አልስተማሩንም::
አሁን አንት የተማርከውና ለማስተማር የምትፈልገው ታሪክ ደግሞ ሰይጣናዊ ነው:: የአንድን ዘር ክፉ ክፉውን ብቻ አስተምሮ ካልበቃም ጨምሮ, ሌላውን አሞግሶ, የሌላቸውን ጀግንነት ማስተማር ዛሬ ኤርትራውያንን ባጭር ጊዜ ካደረሰው ውጤት በተማርክ:: ካገር አገር, ከስልጣን ስልጣን, ከሃብት ሃብት አማርጠው ከሚኖሩበት በአንድ ጀምበር መሬት ከስራቸው የሸሸው, ሰማይ የተገለበጠባቸው ይሉኝታ የሌለው የታሪክ ቅጥፈት በማካሄዳቸው ነው:: ታሪክ ላይ ቅጥፈት ሰርቶ ያሚያመልጥ የለም:: የጊዜ ጉዳይ እንጂ ትበቀላለች::



Re: ምኒሊክና ኣድዋ

Postby yoha » 04 Mar 2012, 05:20


Beles wrote:የሃ
ከምትለው አንድ የምስማማው ነገር አለ::ታርክን የምንማርበት ምክንያት አለው:: ከስህተቱ እንድንማርበት ነው:: ለዚህ ደግሞ ደጉም ክፉውም አብሮ መስተማር አለበት:: በዚህ በኩል የኢትዮጵያ ታሪክ አስተማሪዎች የታሪክ ትምህርት ጥቅሙን አልተረዱትም ማለት እንችላለን:: የታሪክ ደግ ደጉን ብቻ ተነግሮ በአዲሱ ትውልድ ላይ በራስ መኩራትንና መተማመንን ማምጣትን ብቻ እንደግብ ያዩ ይመስለኛል:: የዮሃንስን ከሃዲነት, የሚኒሊክን ስህተት, የቴዎድሮስን ጨካኝነት ሳይዘግቡ የሚያልፉት ለዚህ ይመስለኛል:: በተለይ በተለይ አንድ ያላደረጉት ነገር ከአንድ ጎሳ የመጣን መሪ ኮንነው ከአንድ ጎሳ የመጣን አሞግሰው አልስተማሩንም::
አሁን አንት የተማርከውና ለማስተማር የምትፈልገው ታሪክ ደግሞ ሰይጣናዊ ነው:: የአንድን ዘር [color=#FF0000]ክፉ ክፉውን ብቻ አስተምሮ ካልበቃም ጨምሮ, ሌላውን አሞግሶ, የሌላቸውን ጀግንነት ማስተማር ዛሬ ኤርትራውያንን ባጭር ጊዜ ካደረሰው ውጤት በተማርክ:: ካገር አገር, ከስልጣን ስልጣን, ከሃብት ሃብት አማርጠው ከሚኖሩበት በአንድ ጀምበር መሬት ከስራቸው የሸሸው, ሰማይ የተገለበጠባቸው ይሉኝታ የሌለው የታሪክ ቅጥፈት በማካሄዳቸው ነው:: ታሪክ ላይ ቅጥፈት ሰርቶ ያሚያመልጥ የለም:: የጊዜ ጉዳይ እንጂ ትበቀላለች::



በለስ ! የኤርትራ ህዝብ ችግር እንዳንተ አባባል ሳይሆን የኢትዮጵያውያን የ70 አመት ቸልተኝነት ነበር ግን ብዙ ኢትዮጵያውያን ያንን ሸፍነው ከጣሊያን ጋር አብረው ስለወጉን ነው የሚል አባባል ሰምተሃል እስኪ አስበው ጣሊያን ኤርትራን ሲያስተዳድር ህዝቡን በምን መልኩ ይይዘው እንደነበር ግልጽ ነው ቤኩልነት ትምህርት መማር, መስራት በማይቻል ሁኔታ ባጠቃላይ ግዞት ነበር ታዲያ ይህንን መርጠው ነው ከጣሊያን ጎን ቆመው ኢትዮጵያን የሚወጉት ግድየለህም ወንድሜ ይቺ የነሚኒሊክና ሃይለስላሴ ስህተትን ለመሸፋፈን ሆን ተብሎ የተጻፈ ታሪክ እንጂ በቅኝ መገዛትን የሚመርጥ ማንም የለም እንዳንተ አባባል ከሆነም እስኪ አስበው በጣሊያን እየተረገጡ ለጣሊያን ተከላከሉ ካልን ባንጻሩ ደግሞ ኢትዮጵያ ውስጥ ጥሩ ከነበሩ ለምን የመገንጠል ጥያቄን ያነሳሉ ብለህ ታስባለህ ወንድሜ እመንኝ ኢትዮጵያ ብዙ ያመራር ችግር ያለባት አገር ናት አሁንም መለስ እራሱ ባወጣው constitution መሰረት ከኦነግጋ ምንም መዋጋት ባላስፈለገ ምክንያቱም እራሱ ወያኔ ትናንትና ተመሳሳይ ጥያቄ አንስቶ ስለነብር ማለቴ ነው ታዲታ ይህ የሚያመላክተው መሪዎቹ ሁሉም የህብን ጥያቄ መመለስ አይችሉም ከመለሱም እስራትና ሞት ነው መልሳቸው አሁንም ሌላ ጥፈት ሳይመጣ ያለው መንግስት ለኦነግም ሆነ ኦብነግ ይቅርታ መጠየቅ ያለበት ይመስለኛል ያ ግን ወያኔ በወያኔ በኩል ሊደረግ የሚችል አይደለም ምክንያቱም እራሱ ወያኔ ዴማጎጂ ስለሆነ ::

Previous Page Next Page


Return to News & Opinion

Who is online

Registered users: Asmarino, Bing [Bot], elias, Google [Bot], Google Adsense [Bot], Google Feedfetcher, MatiT, MSN [Bot], rastaman4ever