በድጋሚ ኢትዮጵያ ለኤርትራ መዋጋት ነበረባት የሚለው ጥያቄህ ተገቢነት ያለው ነው:: ነገር ግን በሚኒሊክም ሆነ በኢትዮጵያ ላይ የምታወርደው ፍርድ ፍትህ የጎደለው ነው:: ሚኒሊክ ተጠያቂነት አለበት, ግን እሱ ብቻ አይደለም ተጠያቂነት ያለበት:: በወቅቱ ከጣላያን ጋር የተሰለፉ የኤርትራ አስካሪዎችና ለጣሊያን ያደሩ የትግራይ መኳንንት ለምሳሌ ከሚኒሊክ የበለጠ ተጠያቂነት ይኖርባቸዋል:: በኋይለስላሴም ሆነ በደርግም ጊዜ እንዲሁ:: ግን ኤርትራዊያኑና ትግሬዎቹ ተጠያቂነትን ለሌላው ማከናነብና እራሳቸውን ከተጠያቂነት ነፃ ማድረግ እንደሚያዋጣ ነገር አድርገው ይዘውታል:: ይህም ዛሬ በሌላው ህዝብ አመኔታን ከማሳጣቱም በላይ ለወደፊት ፍጥቻና ጦርነት መሰረት እየጣለ ይገኛል:: ምኒሊክ የሚጠየቀው በወቅቱ ራሱ በሰራው ነው እንጂ ሻቢያና ወያኔን በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ለከፈቱት ጦርነት ተጠያቂ አይሆንም:: ወደፊትም ለማይቀረው በባሕር በሩ ምክንያት ለሚነሳው ጦርነት ማለት ነው:: ሰው ለራሱ የፈለገውን ጊዜ ሊዋሽ ይችላል:: ለሌላ ሰው ግን ከአንድ ወይ ከሁለት ጊዜ በላይ በላይ ዋሽቶ ውጤት አያገኝበትም:: እንደ ዋሾና ቀጣፊ ተቆጥሮ, አመኔታ አጥቶ ከዚያ በኋላ ሁሉም ነገር ወደቁልቁል ይሆናል ማለት ነው:: አሁን ኤርትራ እንዳለው ማለት ነው::
yoha wrote:Beles wrote:ዮሃ
ምኒሊክ ለኤርትራ ለምን አልተዋጋም የሚል ስሞታ አቅርበህ የሚመስለኝን ለማለት ስሞክር ተሰርዞ ደረስኩበት:: ለማንኛውም ሰሞኑን በዚህ ጉዳይ እያሰብኩ ነበርና ከሞራል ግዴታና ወቅታዊ ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር (practical) ብለን ብንከፋፍላቸው ምናልባት የተሻለ መልስ እናገኝ ይሆናል:: ኢትዮጵያ በኤርtra ላይ የይገባኛል ጥያቄ ካላት ያ መብት ከግዴታ ጋርም የተያያዘ መሆን ይገባዋል:: ከግዴታው አንዱ ከባዕድ አገዛዝ መከላከል ነው:: ይህ አስተሳሰብ በተለይ በዛሬ ጊዜ ላይ ሆነን ስንመለከተው የበለጠ ትክክል ነው የሚል ግምት አለኝ:: ይህ እንግዲህ በኢኮኖሚም ሆነ ቤእውቀት በከፍተኛ ደረጃ የሰለጠነ አስተሳሰብና አመለካከትን ይጠይቃል:: ኢኮኖሚ ከፍተኛ የሆነ አስተዋጽዖ አለው:: በቀላሉ በግለሰብ ደረጃ እንኳን ኪስህ ሞላ ሲልና ሲጎል ከአንደበትህ የሚወጣው ድምጽ ይለያያል:: አንደኛው የሚለማመጥ ሲሆን ሌላኛው በራስ መተማመን ያለበት ጎርነን ያለ ነው:: ለአብዛናው ሰው ማለት ነው:: አንዳንድ ግን አሉ በድህነታቸውም ቢሆን ክብራቸውን አቅማቸው እስከቻለ ድረስ ለማስከበር ወደኋላ የማይሉ::
እንግዲህ ከዚ አንጻር ምንም እንኳን ምኒሊክ ጣሊያንን ባህር ውስጥ ገፍቶ በጣላቸው ብለን ብንመኝም አቅሙን ስናገናዝበው ግን የሰራው ስራ ምን ያህል ጀግንነት የተሞላበት እንደሆነ መጋንዘብ እንችላለን:: በየትኛውም መለኪያ ላይ የወቅቱን ጣሊያንና ኢትዮጵያን ብንመዝን ምኒሊክ ተሸንፎ እንደ ቴዎድሮስ ራሱን መግደል ነበረበት:: ምርኮኛ እንደማይሆን ጥርጥር የለውም:: ለዚህም ተዘጋጅቶ እንደሄደ ከአዋጁ ማንበብ ይቻላል:: የተገኘው ድል በሚኒሊክና በጦሩ የሂሊና ጥንካሬ የተገኘ (እምነት ካለህ እግዚአብሄር ታክሎበት) እንጂ ሰው በሚመካበት በገንዘብ, በዕውቀት, በጉልበት የተገኘ አይደለም:: ለዚህ ነው ይህ ድልና ለዚህ ድል ያበቁት ጀግኖች በታሪክ ወደር የማይገኝላቸው ድንቅ መባል የሚገባቸው::
አንድ ደጋግመው ኤርትራዊያን (ከየት እንዳመጡት አላውቅም) ኢትዮጵያውያን የኤርትራን መሬት እንጂ ህዝቡን አይፈልጉትም የሚባለው ነገር ነው:: ምንም እንኳን የኤርትራ መሬት በጣሊያን እጅ ቢወድቅም ኤርትራዊያን በኢትዮጵያ ውስጥ ያላቸውን ክብርና መብት ተነፍገው እንደማያውቁ በኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ ውስጥ የነበራቸውን ድርሻ በማየት መረዳት ይቻላል:: እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ እንዲያውም በኢትዮጵያ ላይ ከሌላው ኢትዮጵያዊ የበለጠ ሃብት, ስልጣንና ከዚያም ጋር ተያይዞ የሚመጣው መብት እንደነበራቸው ምስክር ሆነን ያየነው ነገር ነው:: በጣም የሚገርመው ኤርትራዊያን ይህንን መብት የተነጠቁት በነጻ አውጪዎቻቸው መሆኑ ነው::
Beles !
ልጽፍ ጀምሬ የነበርው በኔ አመለካከት ሚኒሊክን እንደ ጀግና ሳይሆን እንደ አንድ ተራ መሃይም መሪ ነው የማያቸው ምክንያቱም ምንም ዛሬ ኤርትራና ትግራይ ህዝብ መቃቃር ቢኖርም የሁለት ህዝብ የዘር ግንድ አንድ ከመሆን አልፎም አንድ አገርም የነበረ ሲሆን በሚኒሊክ አማካኝንት ከጣሊያን ጋ ሶስት ግዜ መዋዋል ኢትዮጵያ ኤርትራን አጥታለች በሌላ መልኩ የአድዋ ድል ለየኢትዮጵያ ህዝብ እንደአኩሪነት የጠቀሳል በሌላው መልኩ ደግሞ ኤርትራ የኢትዮጵያ አካል ነበረች ካልንና የኤርትራ ህዝብ ለ70አመታት በጣሊያን ሲበደል እንደቆየ የሚገልጽ አንድም መጽሃፍ በኢትዮጵያ ታሪክ መጻህፍት ውስጥ የለም ታዲያ እንዴት አድርጎ ነው የህ ሁለት ተጻራሪ ጉዳይ አብሮ የሚሄደው ወይ ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ነበረች ያ ሃቅ ካልሆነ ደግሞ ኤርትራ ለ70 አመታት በቅኝ ስለዋለች የኢትዮጵያ አካል ላትሆን ነው ማለት ነው :: አይ አይሆንም ኤርትራ የኢትዮጵያ አካል ነው ብለን የምንካራከር ከሆነ እንግዲያውስ ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ውስጥ ቅይታለች ሊባል ያስችላል መቼም ይህ አባባል ብዙ ጉረኛ ኢትዮጵያውያንን ሊያስቆጣ ይችላል ይሁን እንጂ ሃቅ ከሚያንቀኝ እውነትን ማሳወቅና ማወቅ ያለብኝ ስለመሰለኝም ነው :: ይህ አባባል ምንም ጥቅም ላይኖረው ይችላል ምክንያቱም አሁን ኤርተራም አገር ስለሆነች ማለት ነው ቢሆንም ስህተት ከመሪዎች እንጂ ከህዝብ አይመጣም ከሚኒሊክ እስከ መለስ ኢትዮጵያ ምንም አኩሪ የመሪ ታሪክ የላትም የአድዋ ድልም የኢትዮጵያ ህዝብና አርበኞች ድል እንጂ የነሚኒሊክ ድል አይደለም በኔ አመለካከት ሚኒሊክ አሳፋሪ መሪ ነበሩም ባይ ነኝ በርግጥ ባለቤታቸው እቴጌ ጣይቱ አስተዋይና ብልህ እንደነበሩ ታሪክ ሁሌም ያወሳቸዋል :: በመጨረሻም ዛሬ የደረስንበት በኢትዮጵያ ህዝብና በኤርትራ ና በትግራይ ህዝብ ተለያይቶ መኖር ዋናው ተዋንያን ሚኒሊክ ለሱም ከጣሊያን ጋር ያደረጉት ውል ምስክር ነው :: እንዳውም ለዚህ ሁለት ወንድማማች ህዝብ ደም መፋሰስና ኢትዮጵያ አሁን ላለችበት ደረጃም በቅታለች::
በለስ ! ሚኒሊክ ለምን አልተዋጋም ለማለት አልነበረም አለመዋጋት በብዙ ጉዳይ ሊገለጽ ይቻላል ግን ህዝብንና አገርን የሚያክል ነገር ለ70አምት ትተህ በቅኝ ግዛት አልዋልኩም ነገር ግን የኤርትራን ህዝብ ኢትዮጵያዊ ስላልሆነ ለጣሊያን ፊርሞ ከመሽጥ ምን ይለየዋል, ለዚህም ነው በኢትዮጵያና ኤርተራ ህዝብ ያን ያህል ልዩነት ብሎም ደም መፋሰስ ያስከተለው መቼም ብዙ ኢትዮጵያዊ ሃቅን ስለማይወድ ሊከፉ ይችላሉ ኢትዮጵያ በጣልያን ተገዝታለች የአድዋ ድል አኩሪ ታሪክም ነው ለህዝቡ እንጂ ለመሪ ሳይሆን::



