Ethiopian News and Opinion Forum


የወያኔ ጃንጥላ ተቀዶአል

Postby ተስፋዬ ገ/አብ » 11 Sep 2012, 23:04


ተስፋዬ ገ/አብ

የወያኔ ስርአት በታሪኩ እንዲህ ያለ የተምታታ ሁኔታ ላይ የደረሰበት የታሪክ አጋጣሚ ነበር ለማለት አይቻልም። የባንክ ሰራተኞች የስራ ማቆም አድማ፣ የኦነግ ከመሸጋገሪያው መውጣት፣ የኤርትራ ጦርነት፣ የህወሃት መከፋፈል፣ ምርጫ 97 የመሳሰሉ አጋጣሚዎች ለኢህአዴግ ፈታኝ የነበሩ መሆናቸው ይታወቃል።

ከፍተኛ ትርምስ የነበረባቸውም ናቸው። ቢሆንም በነዚያ ጊዜያት ድርጅቱ ድርጅታዊ አቅሙን ባለማጣቱ አንሰራርቶ መቀጠል ችሎአል። የመለስ ዜናዊን እረፍት ተከትሎ የመጣው ቀውስ ግን የድርጅቱን መሰረት እያናጋው ይገኛል።

መለስን ተከትሎ አብሮ ለመሞት በጣም እየተጣደፈ ያለው ኦህዴድ ሆኖአል። ኦህዴድ መሪ የለውም። የህወሃት አንጋፋዎች የራሳቸው ችግር ቢኖርባቸውም ኦህዴድን ከመሞት ለማዳን ቅድሚያ ትኩረት ሰጥተው እየተሯሯጡ ይገኛሉ። መተካካት የሚለውን ነጠላ ዜማ ደምስሰው፣ ገራባ እየፈለጉ ነው። መገረብ ጀምረዋል። ኩማ ደመቅሳን የኦህዴድ ሊቀመንበር፣ አባ ዱላን በኦሮሚያ ፕሬዚዳንትነት ለማስቀመጥ፣ በካድሬዎቻቸው በኩል ቅስቀሳ ይዘዋል። ይህ ሩጫ ጊዚያዊ ጥገና ይባላል። እንደ አሸዋ ግድብ ከነገ ወዲያ መልሶ ይፈርሳል።

“የሃይለማርያም ደሳለኝ ምክትል ማን ይሁን?” የሚለው እንዳከራከረ ሲሆን፣ በአንድ በኩል ሶስት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮችን ለማስቀመጥ አሳብ ሲቀርብ፣ በሌላ በኩል የህወሃት እና የብአዴንን ፉክክር ለማስቀረት፣ ኩማ ደመቅሳን በምክትልነት ለማስቀመጥ መምረጣቸው ይሰማል። መፍትሄ አይሆንም። በዚህ አካሄድ ማንኛውም ነገር ወደሁዋላ በፍጥነት ይጓዛል።

ሁኔታዎች በፍጥነት ሲለዋወጡ ሰንብተዋል። ለዚህ ሲለዋወጥ ለሰነበተ ውዥንብር መቁዋጠሪያ ለማበጀት የኢህአዴግ ምክርቤት ከመስከረም 3 እስከ 5 ስብሰባ ጠርቶአል። ርግጥ ነው፣ ውዥንብሩን ለመቀነስ የሚረዳ፣ ከሃሜት የሚያድናቸውን አንድ ደካማ መዋቅር በመፍጠር፣ “ችግሩ ተፈትቶአል” ብለው ሊውጁ ይችላሉ።

ሊቀጥሉ ግን አይችሉም። ኢህአዴግ ማእከል አጥቶአል። ቀደም ሲል ኢህአዴግ አንድ መቋጠሪያ ነበረው። አንድ የሚፈሩት ሰው ነበራቸው። ሁሉም ልዩነቱን፣ ቅሬታውን ብሶቱን ይዞ የሚሮጥበት አንድ ቢሮ ነበር። አሁን ያ የለም። ጃንጥላው ተቀዶአል። ከጥቂት በላይ ምሰሶዎች በያቅጣጫው እየተተከሉ ነው። በራቸውን መክፈት ካልቻሉ፣ አፍጦ የመጣባቸውን እውነት ማየት ካልቻሉ እጣ ፈንታቸው ደጃፋቸው ላይ ከተቀመጠው መልአከ ውድቀት እጅ ላይ መውደቅ ይሆናል።



Re: የወያኔ ጃንጥላ ተቀዶአል

Postby sema2 » 12 Sep 2012, 02:12


Yes, the parachute has been punctured. But the TPLF does not seem to have come to grips with the reality. TPLF is still in the state of denial but at its own peril. One of the reasons they are choosing to stay in the state of denial is empty bravado emanating from simple stupidity. The second and may be the major reason is they are dumbfounded and do not know what to do. Meles rendered the TPLF useless without him. As Sebhat said recently Meles died after buring the TPLF. They do not have any clue, none whatsoever, how to get out of this mess they find themselves in. They have just chosen to freeze the time in their head and stay in the state of denial while they are in a free fall because the parachute has already been punctured. They will soon find themselves hitting the ground breaking down into irredeemable fine pieces. The damage has already been done and no number of DPMs can save them. HD, Girma, Abba Dula, Kuma, Addisu, Demeke, Bereket, Arkebe, Abay, Seyoum, Sebhat, Berhane, Tewdros, Azeb, Samora, Getachew, none of them can save the TPLF from its final resting grave it is heading to. Did you think all that wailing of the TPLF a couple of weeks ago was for Meles? No, it was for themselves. In the heart of their hearts they know the game is over.



Re: የወያኔ ጃንጥላ ተቀዶአል

Postby Guest1 » 12 Sep 2012, 03:10


TGA

you said nothing. There is no analysis, usual uselss gossip


RUBBISBH!!!!



Re: የወያኔ ጃንጥላ ተቀዶአል

Postby revolutions » 12 Sep 2012, 20:02



The end of woyane has come !



Re: የወያኔ ጃንጥላ ተቀዶአል

Postby Goba » 12 Sep 2012, 22:33


The end of Woyane and Shabia has come!
revolutions wrote:
The end of woyane has come !



Re: የወያኔ ጃንጥላ ተቀዶአል

Postby wubela » 15 Sep 2012, 00:52


In your dream," your dream has come true." Wayne's children are waiting to repeat their fathers' and mothers' history. They are even better trained both militarily and politically. Where? In the mountains of Tigrai, where they always come out with victory. YOU!!!! I don't think so.



Return to News & Opinion

Who is online

Registered users: Bing [Bot], DAnnni, Exabot [Bot], Google [Bot], Google Adsense [Bot], Hawileyto, Hawzen, Medien13, netsanet, New Guy, psbot [Picsearch], rastaman4ever, richard, Somali-Ethio, Tit for Tat