Ethiopian News and Opinion Forum


አቶ ኃይለማርያም፤ “ሜዳውም ፈረሱም ያው…” ታድያ በቅጡ ይጋልቡ!?

Postby Aragaw » 18 Sep 2012, 10:27


አቤ ቶኪቻው

Image

ኃይለማርያም ደሳለኝ በጠቅላይ ሚኒስቴሩ ወንበር ላይ ለመቀመጥ ቤተመንግስቱ በራፍ ላይ ቆመዋል። ለነገሩ እንኳ ሰውየው ደጃፍ ላይ ከቆሙ ቆይተዋል። ነገር ግን የኢህአዴግ ሰዎች “አናስገባም ሰርገኛ እደጅ ይቆይ…” ብለው ደጅ ሲያስጠኗቸው ሰነባበቱ። ይገበሉ ተብሎ ሲጠበቅ የነበረው ቢያንስ ኢቲቪ እና የመንግስት “ባሉካዎች” የጠቅላይ ሚኒስሩን ሞት በሰሙ በሁለት እና ሶስት ቀናት ውስጥ ነበር። ነገር ግን ይኸው ዛሬም ገና ፓርላማው ጠቅላይነታቸውን እስኪያፀድቅላቸው እንደ ቆሎ ተማሪ ደጅ መቆም ግዴታቸው ሆኗል።

አቶ ሀይለማሪያም የኢህአዴግ ሊቀመንበርነትን ስልጣን ከያዙ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ “ሲሲቲቪ” ለተበለ ቴሌቪዥን ጣቢያ በሰጡት ቃል “የእኔ አመራር የጋራ አመራር መርህን የተከተለ ነው” ካሉ በኋላ፤ “እንደሚታወቀው የመለስም አመራር ለግለሰብ የበላይነት ቦታ የማይሰጥ የቡድን ስራ የጎላበት አመራር ነበር” ብለው የማናውቀውን ነገር ነግረውናል። እውነቱን ለመናገር እኛ የምናውቀው አቶ መለስ “ሁሉን ቻይ” የነበሩና ሁልገዜም ብቻቸውን እንጂ በጋራ ሲሰሩ አላየንም። እርግጥ ደንብ ነውና ሙትን ሲያነሱ ደግ ደጉን ነው። ስለዚህ ስለ መለስ የሚያወሩት በሙሉ ፅቡቅ ፅቡቁን ቢሆን ግድ የለም…

መምህር ኃይለማሪያም ሆይ መለስን ለአሁኑ እንተዋቸው እና በእርስዎ ጉዳይ እናውጋ… እናልዎ… አሁን ሜዳው ሜዳውም ፈረሱም በእጅዎ ነው። እንግዲህ በቅጡ መጋለብ የእርስዎ ፈንታ ነው።

መምህር ሆይ ይቅርታ አንድ ጊዜ ወደ መለስ መለስ እንበልና አንድ ነገር ሹክ ልበልዎትማ ባለፈው ጊዜ የመለስ ለቅሶ ላይ ጥቁር በጥቁር ለብሶ “እንባ የተራጨው” ህዝቡ ሁላ ከኢህአዴግ ጎን ነው ስለዚህ እንዳሻኝ እሆናለሁ ብለው እንዳይሸወዱ… ልብ ያድርጉልኝ “እንባ የተራጨው” የምትለዋ ቃል ራሱ ያለችው በትምህርተ ጥቅስ ውስጥ ነው። ለምን ትምህርተ ጥቅስ ውስጥ እንደገባች በአዲስ መስመር ላይ ልንገርዎት…

በጉለሌ ክፍለከተማ በሆነው ቀበሌ ውስጥ የቀበሌው አስተዳደር ለመለስ ለቅሶ ድንኳን ደኩኖ ነበር። ታድያልዎ… አስለቃሹ የቀበሌ አስተዳደር በየቤቱ እየዞረ “በዛሬው ዕለት ጋዜጠኞች ስለሚመጡ ሁሉም ነዋሪ በነቂስ ወጥቶ በድንኳን ውስጥ እንዲያለቅስ” ሲል አዘዘልዎ። የቀበሌው ሰውም ታዛዥ ነውና እሺ ብሎ ጥቁር ልብስ ያለው ልብሱን ልብስ የሌለው ደግሞ ፊቱን አጥቁሮ ወደ ለቅሶው ድንኳን አመራልዎ። ምን ዋጋ አለው አንድ ሁለት ሶስት ተብሎ ለቅሶ ሲጀመርልዎ ከአስለቃሽ ኮሚቴ አባላት አንዱ “እባካችሁ አሁን ጋዜጠኞቹ ደውለው መምጣት አንችልም ስላሉ አታልቅሱ፤ ነገ ሲመጡ እናለቅሳለን አሁን ካሜራ በሌለበት ብናለቅስ ዋጋ የለውም” ብለው አስቆሙልዎ…! ለዚህ ነው “በእንባ ሲራጩ” የምትለዋን ቃል ለማንኛውም ብዬ ትምህርተ ጥቅስ ውስጥ ያስገባኋት። እናም አቶ ኃይለማሪያም ሆይ እንዳይሸወዱ…

የእርስዎ ነገር የሚወሰነው ድጋፍም ሆነ ተቃውሞ የሚያመጣብዎም ሆነ የሚያመጣልዎ ቀጥሎ በፈረስዎ እና በሜዳዎ ላይ በሚያሳዩት ትዕንት ነው።

ለምሳሌ ከመለስ በኋላ በነበረው “የአስከሬኑ” አስተዳደር ጊዜ ከማተሚያ ቤት ደጃፍ እንዲጠፉ የተደረጉት እና ድሮውንም ትንሽ ጭል ጭል ሲሉ የነበሩ ነፃ ፕሬሶች ቢያንስ ወደ ቀድሞ ይዞታቸው እንዲመለሱ ማድረግ አለብዎ…

ሌላ ደግሞ የታሰሩ ጋዜጠኞች እና ፖለቲከኞችን መፍታትም ምንም ሳይጨነቁ ሊያደርጉት የሚገባ ነገር ነው። ዳሩ ትዳርን መፍታት እንጂ ምስኪን እስረኛን ለመፍታት ምን ያስጨንቅዎታል? ዝም ብለው ዛሬ ነገ ብለው ቀጠሮ ሳይሰጡ፤ ሽማግሌ ገለመሌ ሳይሉ ይፍቱዋቸው።

በነገራችን ላይ የስዊድን ጋዜጠኞች ተፈቱ አሉ እሰይ እንዲህ ነው እንጂ… ግን ያኔ አቶ መለስ “የነጭ ደምም የጥቁር ደምም አንድ ነው” ብለው ደስኩረውልን አልነበር እንዴ..!? እንዴት ነው ነገሩ ለመታሰር ጊዜ ነው አንድ የምንሆነው?

ለማንኛውም ቢያንስ እነዚህን ሁለት ነገሮች ካደረጉ ሌላውን ደግሞ ቀስ ብለው ይሰሩታል። አደራ የኑሮ ውድነቱን ነገር ለመግታት የተቻሎትን ሁሉ ያድርጉ። ካልተቻሎት ደግሞ ተቃዋሚዎችም ሆኑ ገለልተኞች ብቻ ግን ለዚህ መፍትሄ ያላቸውን ባለሞያዎች እገዛ ይጠይቁ…!

እንደ እርሳቸው ሁሉን ነገር እኔ ብቻ እና እኛ ብቻ አይበሉ። ሁሉም ኢትዮጵያዊ በሀገሩ ጉዳይ ላይ እንዲሳተፍ ይጥሩ ይጣሩም።

አለበለዛ ሀበሻ ይተርትብዎታል “ጉልቻ ቢቀያየር ወጥ አያጣፍጥም” ይሎታል። እውነት እውነት እልዎታለሁ ተርቶ ብቻ የሚተዎት አይመስለኝም። ወጡን ለማጣፈጥ የራሳቸውን ቅመም ማበጀት የጀመሩ ብዙ ጎበዛዞች አሉ (ይሄ ሚስጥር ነው።) አራዳ ከሆኑ ግን የቀማሚዎችንም ድጋፍ ማግኘት ይችላሉ።

እንግዲህ ይበርቱ! እንጂ ሌላ ምን እላለሁ…!



Re: አቶ ኃይለማርያም፤ “ሜዳውም ፈረሱም ያው…” ታድያ በቅጡ ይጋልቡ!?

Postby Aragaw » 18 Sep 2012, 10:33


በጉለሌ ክፍለከተማ በሆነው ቀበሌ ውስጥ የቀበሌው አስተዳደር ለመለስ ለቅሶ ድንኳን ደኩኖ ነበር። ታድያልዎ… አስለቃሹ የቀበሌ አስተዳደር በየቤቱ እየዞረ “በዛሬው ዕለት ጋዜጠኞች ስለሚመጡ ሁሉም ነዋሪ በነቂስ ወጥቶ በድንኳን ውስጥ እንዲያለቅስ” ሲል አዘዘልዎ። የቀበሌው ሰውም ታዛዥ ነውና እሺ ብሎ ጥቁር ልብስ ያለው ልብሱን ልብስ የሌለው ደግሞ ፊቱን አጥቁሮ ወደ ለቅሶው ድንኳን አመራልዎ። ምን ዋጋ አለው አንድ ሁለት ሶስት ተብሎ ለቅሶ ሲጀመርልዎ ከአስለቃሽ ኮሚቴ አባላት አንዱ “እባካችሁ አሁን ጋዜጠኞቹ ደውለው መምጣት አንችልም ስላሉ አታልቅሱ፤ ነገ ሲመጡ እናለቅሳለን አሁን ካሜራ በሌለበት ብናለቅስ ዋጋ የለውም” ብለው አስቆሙልዎ…!
:lol: :lol: :lol: :lol: :lol:




Re: አቶ ኃይለማርያም፤ “ሜዳውም ፈረሱም ያው…” ታድያ በቅጡ ይጋልቡ!?

Postby EPRDF » 18 Sep 2012, 11:44


Ethiopian oppositions political analysis

ALu, Tebale, eyaLu, SeLaLu, LiLu,SibaL, eYetebaLe, SeLemibaL ...

Nothing scored in the last two decades but the HayaLU ALuBalta



Re: አቶ ኃይለማርያም፤ “ሜዳውም ፈረሱም ያው…” ታድያ በቅጡ ይጋልቡ!?

Postby Aragaw » 18 Sep 2012, 11:53


Halafi Mengedi wrote:Lugamu Klela Sew Ej New yalow Feresun Befelegut Liyagalbut Aychlum.


You might be right."Lugamu Klela Sew Ej New yalow" One think for sure is things will never be the same going forward.



Re: አቶ ኃይለማርያም፤ “ሜዳውም ፈረሱም ያው…” ታድያ በቅጡ ይጋልቡ!?

Postby Fenql » 18 Sep 2012, 20:19


Where is the big black man with black eye glass who was sitting behind the late Meles Z.? I cannot see him Behind "Pm" H/Mariam? I think H/mariam will not need to have TPLF guard :lol: :P :roll: :roll: :arrow:



Re: አቶ ኃይለማርያም፤ “ሜዳውም ፈረሱም ያው…” ታድያ በቅጡ ይጋልቡ!?

Postby Dandew » 18 Sep 2012, 20:59


HD has challenges and opportunities to prove himself. If he chooses to serve the interest of Ethiopia, despite the daunting challenges, can achieve a lot better than Meles and Co. For one thing, Hailemariam and his deputy are educated and serve as educators. They are university graduates and in most probability have respect for education, the educated, science and wisdom. Meles and company were high school graduates and their first action was to discredit education and the educated. And yet they were shopping for fake certificate from around the world.

Hailemariam should walk deliberately and carefully in this hate infested political environment. If he shows he is truely serving the interest of Ethiopia and all Ethiopians, he has what it takes to achieve alot. Good luck.



Return to News & Opinion

Who is online

Registered users: Analyst, Bing [Bot], Google [Bot], Google Adsense [Bot], Google Feedfetcher, Halafi Mengedi, Halyeyga, Shewit, Shonemann, Thomas H