Ethiopian News and Opinion Forum


በመለስ ዜናዊ ሞት መሪር ሀዘን የተሰማው ወጣት ከ10ኛ ፎቅ ተወርውሮ ሞተ

Postby ግሩም » 25 Sep 2012, 00:48


በታምሩ ጽጌ

የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሕልፈተ ሕይወትን ከሰማበት ዕለት ጀምሮ መሪር ሐዘን ውስጥ ገብቶ የነበረው ወንድወሰን ተስፋዬ የተባለ የ30 ዓመት ወጣት ከአሥረኛ ፎቅ ላይ ተከስክሶ ሕይወቱ ማለፉ ታወቀ፡፡

ወጣቱ ራሱ ተወርውሮ ሕይወቱ ያለፈው ነሐሴ 24 ቀን 2004 ዓ.ም. በቂርቆስ ክፍለ ከተማ በቀድሞው ቀበሌ 02/03 በተለምዶ ወሎ ሰፈር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከሚገኘው ሚና ሕንፃ ላይ መሆኑን፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የሰው መግደል ወንጀል ምርመራ ዲቪዚዮን ለሪፖርተር አረጋግጧል፡፡

ወጣቱ አሰፋ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር በሚባል ድርጅት ውስጥ በሹፌርነት ተቀጥሮ የታሸጉ ምግቦችን እያዞረ ለሱፐር ማርኬቶችና ለተለያዩ የንግድ ተቋሞች ያከፋፍል ነበር፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ሕልፈተ ሕይወት ከተሰማበት ነሐሴ 15 ቀን 2004 ዓ.ም. ጀምሮ “መኖር ምን ያደርጋል” በማለት ከሥራ ባልደረቦቹ ተለይቶና ለብቻው በመሆን አንዳንድ ጊዜም ያለቅስ እንደነበር ይሠራበት ከነበረው ድርጅት ባለቤት መስማቱን የገለጸው ፖሊስ፣ አሠሪውም የወጣቱ ሁኔታ ስላላማራቸው ለአራት ቀናት ዕረፍት ወስዶና ተረጋግቶ እንዲመለስ በመፍቀድ፣ የመኪና ቁልፍ ተረክበውት ወደ ቤቱ መሄዱንና በመጨረሻም ሕይወቱ ማለፉን መስማታቸውን ተናግሯል፡፡

ወጣቱ የማንኛውም የፖለቲካ ድርጅት አባል አለመሆኑን፣ ነገር ግን የጠቅላይ ሚኒስትሩ አፍቃሪ እንደነበርና እሳቸው በፓርላማም ይሁን በማንኛውም ቦታ ሆነው ንግግር ያደርጋሉ ከተባለ፣ ሥራውን ሁሉ ትቶ ሲያዳምጥ እንደሚቆይ ባደረገው ምርመራ ማረጋገጡን የተናገረው ፖሊስ፣ ከሚና ሕንፃ አሥረኛ ፎቅ ላይ ተፈጥፍጦ ሕይወቱ ባለፈበት ዕለትም፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩን ሦስት ሃያ በሰላሳ የሚሆኑና አራት ትናንሽ ፎቶግራፎች ይዞ እንደነበር ጠቁሞ፣ ምስላቸው የታተመበት ቲሸርትም ለብሶ እንደነበር ገልጿል፡፡

ከፎቅ ላይ ተከስክሶ ሕይወቱ ማለፉ ለፖሊስ እንደተነገረ በአካባቢው የነበረ የፖሊስ ኃይል በደረሰበት ወቅት በወጣቱ ኪስ ውስጥ ከደብተር ላይ የተገነጠለችና እጥፍጥፍ ብላ ከተቀመጠች ወረቀት በስተቀር ምንም ዓይነት ማስረጃ እንዳልነበር የገለጸው ፖሊስ፣ ተጣጥፋ በተገኘችው ወረቀት ላይ ወጣቱ ኑዛዜውን አሳርፎ ማግኘቱን ተናግሯል፡፡

ራሱን ለማጥፋቱ ተጠያቂው ራሱ ብቻ መሆኑን፣ ከማንም ጋር ፀብም ሆነ ሌላ ችግር የሌለው መሆኑን፣ ከአለቃው ጋርም ፍቅር መሆኑን፣ በጣም ጥሩ ሰው መሆናቸውንና ሌሎችንም አድንቆ በጻፈባት በዚያች ወረቀት ላይ፣ ለሕይወቱ መጥፋት ምክንያትም ባለራዕዩ፣ ለወጣቱ በተለይ ሥራ ሌለው ትኩስ ኃይል እንዴት ሥራ መፍጠር እንደሚችል በተግባር ያሳዩ፣ ሁሉም የሰው ልጆች እኩል መሆናቸውንና በረሀብና በእርዛት የምትታወቅን አገር መካከለኛ ገቢ ካላቸው አገሮች ተርታ ለማሰለፍ ባደረጉት ጥረት ከፍተኛ እመርታ ያሳዩት ጠቅላይ ሚኒስትር ከሞቱ፣ “መኖር ለምን ያስፈልጋል” በማለት ራሱን በራሱ ለማጥፋት ወስኖ እንዳደረገው በዝርዝር በኑዛዜው ወረቀት ላይ ሰፍሮ ማግኘቱን ዲቪዚዮኑ አስረድቷል፡፡ ደብዳቤውንም እንድንመለከተው አድርጓል፡፡

ፖሊስ ወጣቱ ከጻፈው ደብዳቤ በስተቀር ስለ ወጣቱ ማንነት የሚያስረዳ ምንም ዓይነት መረጃ ስላላገኘ፣ የነበረው አማራጭ ደብዳቤውን ደጋግሞ ማንበብ ብቻ ነበር፡፡ ደብዳቤውን ደጋግሞ ያነበበው ፖሊስ “ባለውለታዬ ለሆነችው ሕይወት ሽፈራው” በሚል ስም ካሳንችስ አካባቢ ካለው አዋሽ ባንክ ከራሱ ሒሳብ 46‚100 ብር በማውጣት አየር ጤና በሚገኘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በመሄድ የልጅቷ ሒሳብ ውስጥ ማስገባቱንና በድምሩ 54,980 ብር እንዳለ መጥቀሱን ተመለከተ፡፡ ፖሊስ ከደብዳቤው ላይ ያገኘውን ጠቋሚ መረጃ በመያዝ ወደ ፍርድ ቤት ሄዶ የባንኮች ሒሳብ መዝገብ ለማየት የሚያስችለውን ፈቃድ ከፍርድ ቤት በማውጣት፣ ወደ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (አየር ጤና ቅርንጫፍ) ሄዶ ሲያረጋግጥ፣ ወጣቱ ባለበት ቀን ሒሳብ ማስገባቱንና የጠቀሰውም የገንዘብ መጠን ትክክል መሆኑን ቢያረጋግጥም፣ ወጣቱ ሒሳብ ሲያስገባ የእሷን ስም፣ መለያ ቁጥርና የእሱን ፊርማ ከማስፈር ውጭ ምንም ማስረጃ እንዳልጻፈ ተረዳ፡፡

ፖሊስ ከባንኩ ያገኘውን የሕይወት ሽፈራውን አድራሻ ይዞ በባንክ ሒሳብ መዝገብ ላይ ያስመዘገባቸውን ቀበሌና የቤት ቁጥር ፍለጋ ሲሄድ ልጅቷ በተባለው ቤት ውስጥ ነዋሪ ሳትሆን፣ ወደ ውጭ (ዓረብ አገር) ስትሄድ የባንክ ሒሳብ ለመክፈት መታወቂያ ስለሚያስፈልጋት፣ በዚያ ቤት ቁጥር ማውጣቷንና በወቅቱ እንደሌለች ከቤቱ ባለቤቶች ተረዳ፡፡ ወንድወሰን ስለሚባል ልጅ የሚያውቁት ወይም የሰሙት ነገር እንዳለ ሲጠይቅ እንደሚያውቁትና ጓደኛዋ (እጮኛዋ) እንደሆነ አስረድተው ቤቱን እንዳሳዩት አስረድቷል፡፡

ፖሊስ ከረጅም ልፋት በኋላ የወጣቱን ቤት ሲያገኘው ሟች ከሦስት ወንድሞቹና አንድ እህቱ ጋር እንደሚኖር እናቱም በሕይወት እንዳሉ ካረጋገጠ በኋላ፣ የያዘውን ፎቶግራፍ ሲያሳያቸው ወንድማቸው መሆኑን ያረጋግጡለታል፡፡ የት እንዳለ ሲጠይቃቸው፣ ከአንድ ቀን በፊት እንደወጣና እንዳልተመለሰ ይገልጹለታል፡፡ ለግል ጉዳይ እንደሚፈለግ በመንገር ቤተሰቡን አረጋግቶ ነገር ግን ለጐረቤት በአደጋ ምክንያት ሕይወቱ ማለፉን በማስረዳት እንዲያረዷቸው አድርጐ መመለሱን ዲቪዚዮኑ አብራርቷል፡፡

የወጣቱ ቤተሰቦች አስከሬኑን ከዳግማዊ ምኒልክ ሆስፒታል በማውጣት የቀብር ሥርዓቱን ከፈጸሙ በኋላ፣ የሟች ወንድም ወደ ፖሊስ ጣቢያ መጥቶ እንደነበር የገለጸው ፖሊስ፣ ወጣቱ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ፍፁም የሆነ ፍቅር እንደነበረው፣ የመኝታ ቤቱ ሙሉ ግድግዳ በእሳቸው ፎቶግራፍ የተሸፈነ መሆኑን፣ ከፎቅ ራሱን ወርውሮ ሞተ በተባለበት ዕለት ጠዋት ከደብተር ላይ ወረቀት ገንጥሎ ሲጽፍ እንደነበር የገነጠለበትን ደብተር ይዞ በመምጣት ማረጋገጡን ፖሊስ ገልጿል፡፡

የወጣቱ ሕይወት ማለፍ ለምን እስከዛሬ እንደተደበቀ ፖሊስን ተጠይቆ የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ድንገተኛ ሕልፈት ብዙዎችን ለመሪር ሐዘን የዳረገበት ወቅት እንደነበርና በዚህ ወቅት (ነሐሴ 24 ቀን 2004 ዓ.ም.) እንደዚህ ያለ ክስተት ይፋ ማድረግ ምናልባትም ሌሎችን ወደማይሆን መንገድ ሊመራ ይችላል በሚል ዝምታ መምረጡን አስረድቷል፡፡


http://www.ethiopianreporter.com/news/2 ... --10-.html




Re: በመለስ ዜናዊ ሞት መሪር ሀዘን የተሰማው ወጣት ከ10ኛ ፎቅ ተወርውሮ ሞተ

Postby revolutions » 25 Sep 2012, 01:17



This is not even funny. Woyanes pushed the young man from a 10-story building to his death in order to spice up their dramatic propaganda lionizing the dead frog by underestimating the intelligence of the Ethiopian people. R.I.P.



Re: በመለስ ዜናዊ ሞት መሪር ሀዘን የተሰማው ወጣት ከ10ኛ ፎቅ ተወርውሮ ሞተ

Postby Gurezza » 25 Sep 2012, 01:29


Late the entire Bai!gamidos woyane children jump from high building. For one dead A!Igame, we will have a shoot of vodka to cheers. :mrgreen:




Re: በመለስ ዜናዊ ሞት መሪር ሀዘን የተሰማው ወጣት ከ10ኛ ፎቅ ተወርውሮ ሞተ

Postby Guest » 25 Sep 2012, 05:09


It is a made up story, whatever the purpose. The deceased young man's family reported that he left home a day before. Considering this it is not possible for the police to complete the said investigation process including getting authorization from the court, looking into the Banks' record and tracing addresses of the two individuals and gathering information and making determination just in a couple of days. The investigating officers need atleast time to analyze the information they have gathered and report to their comander.

Furthermore, the incident happened at a time the police and the military were at high alert following the anouncement of the death of their 'Head Master', not to protect the piublic but out of fear for their own security. Therefore, it couldn't be possible for the police to follow up the case of the deceased in such extraordinary urgency. Even, under normal condition the police doesn't have the organization, system, technology, and skill to complete such investigations within acceptable time frame; let alone to complete it in just two days, which is not possible even in America.

If the death of the named young man is true, I think, further investigation is required; and the story might have been written to cover up a crime.



Re: በመለስ ዜናዊ ሞት መሪር ሀዘን የተሰማው ወጣት ከ10ኛ ፎቅ ተወርውሮ ሞተ

Postby Guest » 25 Sep 2012, 06:01


If Meles was a person who deserved to be adore, his children would have been seen saddened. I have not seen any tear shed by them.
I have to confess that I felt sorry for him for one minute as a human, the next minutes what comes to my mind was the picture of those he murder and shot in the 2005 election.
The embarsing thing was that he said these people were unemplyed as if he created jobs for the millions.
Trust me if he came to Europe or USA, he would have either become unemplyed or work in a factory like most of our citizen.
He become a prime minister for life by gun. He should have known other citizens went to become unemplyed becuase they did not abuse or rob their nation.
Meles and his TPLF members, they robbed the people of ethiopia, they sold our fertile lands, they sold our minerals. They become self emplyed and millioners. It is a wealth taken from the Ethiopian people. His wife and his daughter went to study in Englan by public money. and a job is created for them.
To get back to story this poor man probably needed medical care. But the problem is that it is so expensive to go to private or public hospital, he was left without medical care. There are many citizens with similar problem thanks to the failing policy of the EPRDF.
When Meles or the Prisedant need treatment, they go to middle east or europe. When the Ethiopian people are sick, they stay home or through themselves from building.
I have heard also all the building in Addis are owned by TPLF caderi and all rooms are empty over the second floor. Finally these room and building found a purpose- for throwing people or for faciltating euthonisia (committing suicide).



Re: በመለስ ዜናዊ ሞት መሪር ሀዘን የተሰማው ወጣት ከ10ኛ ፎቅ ተወርውሮ ሞተ

Postby walelgnemekonenn » 25 Sep 2012, 06:41


ግሩም wrote:በታምሩ ጽጌ

የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሕልፈተ ሕይወትን ከሰማበት ዕለት ጀምሮ መሪር ሐዘን ውስጥ ገብቶ የነበረው ወንድወሰን ተስፋዬ የተባለ የ30 ዓመት ወጣት ከአሥረኛ ፎቅ ላይ ተከስክሶ ሕይወቱ ማለፉ ታወቀ፡፡

ወጣቱ ራሱ ተወርውሮ ሕይወቱ ያለፈው ነሐሴ 24 ቀን 2004 ዓ.ም. በቂርቆስ ክፍለ ከተማ በቀድሞው ቀበሌ 02/03 በተለምዶ ወሎ ሰፈር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከሚገኘው ሚና ሕንፃ ላይ መሆኑን፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የሰው መግደል ወንጀል ምርመራ ዲቪዚዮን ለሪፖርተር አረጋግጧል፡፡

ወጣቱ አሰፋ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር በሚባል ድርጅት ውስጥ በሹፌርነት ተቀጥሮ የታሸጉ ምግቦችን እያዞረ ለሱፐር ማርኬቶችና ለተለያዩ የንግድ ተቋሞች ያከፋፍል ነበር፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ሕልፈተ ሕይወት ከተሰማበት ነሐሴ 15 ቀን 2004 ዓ.ም. ጀምሮ “መኖር ምን ያደርጋል” በማለት ከሥራ ባልደረቦቹ ተለይቶና ለብቻው በመሆን አንዳንድ ጊዜም ያለቅስ እንደነበር ይሠራበት ከነበረው ድርጅት ባለቤት መስማቱን የገለጸው ፖሊስ፣ አሠሪውም የወጣቱ ሁኔታ ስላላማራቸው ለአራት ቀናት ዕረፍት ወስዶና ተረጋግቶ እንዲመለስ በመፍቀድ፣ የመኪና ቁልፍ ተረክበውት ወደ ቤቱ መሄዱንና በመጨረሻም ሕይወቱ ማለፉን መስማታቸውን ተናግሯል፡፡

ወጣቱ የማንኛውም የፖለቲካ ድርጅት አባል አለመሆኑን፣ ነገር ግን የጠቅላይ ሚኒስትሩ አፍቃሪ እንደነበርና እሳቸው በፓርላማም ይሁን በማንኛውም ቦታ ሆነው ንግግር ያደርጋሉ ከተባለ፣ ሥራውን ሁሉ ትቶ ሲያዳምጥ እንደሚቆይ ባደረገው ምርመራ ማረጋገጡን የተናገረው ፖሊስ፣ ከሚና ሕንፃ አሥረኛ ፎቅ ላይ ተፈጥፍጦ ሕይወቱ ባለፈበት ዕለትም፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩን ሦስት ሃያ በሰላሳ የሚሆኑና አራት ትናንሽ ፎቶግራፎች ይዞ እንደነበር ጠቁሞ፣ ምስላቸው የታተመበት ቲሸርትም ለብሶ እንደነበር ገልጿል፡፡

ከፎቅ ላይ ተከስክሶ ሕይወቱ ማለፉ ለፖሊስ እንደተነገረ በአካባቢው የነበረ የፖሊስ ኃይል በደረሰበት ወቅት በወጣቱ ኪስ ውስጥ ከደብተር ላይ የተገነጠለችና እጥፍጥፍ ብላ ከተቀመጠች ወረቀት በስተቀር ምንም ዓይነት ማስረጃ እንዳልነበር የገለጸው ፖሊስ፣ ተጣጥፋ በተገኘችው ወረቀት ላይ ወጣቱ ኑዛዜውን አሳርፎ ማግኘቱን ተናግሯል፡፡

ራሱን ለማጥፋቱ ተጠያቂው ራሱ ብቻ መሆኑን፣ ከማንም ጋር ፀብም ሆነ ሌላ ችግር የሌለው መሆኑን፣ ከአለቃው ጋርም ፍቅር መሆኑን፣ በጣም ጥሩ ሰው መሆናቸውንና ሌሎችንም አድንቆ በጻፈባት በዚያች ወረቀት ላይ፣ ለሕይወቱ መጥፋት ምክንያትም ባለራዕዩ፣ ለወጣቱ በተለይ ሥራ ሌለው ትኩስ ኃይል እንዴት ሥራ መፍጠር እንደሚችል በተግባር ያሳዩ፣ ሁሉም የሰው ልጆች እኩል መሆናቸውንና በረሀብና በእርዛት የምትታወቅን አገር መካከለኛ ገቢ ካላቸው አገሮች ተርታ ለማሰለፍ ባደረጉት ጥረት ከፍተኛ እመርታ ያሳዩት ጠቅላይ ሚኒስትር ከሞቱ፣ “መኖር ለምን ያስፈልጋል” በማለት ራሱን በራሱ ለማጥፋት ወስኖ እንዳደረገው በዝርዝር በኑዛዜው ወረቀት ላይ ሰፍሮ ማግኘቱን ዲቪዚዮኑ አስረድቷል፡፡ ደብዳቤውንም እንድንመለከተው አድርጓል፡፡

ፖሊስ ወጣቱ ከጻፈው ደብዳቤ በስተቀር ስለ ወጣቱ ማንነት የሚያስረዳ ምንም ዓይነት መረጃ ስላላገኘ፣ የነበረው አማራጭ ደብዳቤውን ደጋግሞ ማንበብ ብቻ ነበር፡፡ ደብዳቤውን ደጋግሞ ያነበበው ፖሊስ “ባለውለታዬ ለሆነችው ሕይወት ሽፈራው” በሚል ስም ካሳንችስ አካባቢ ካለው አዋሽ ባንክ ከራሱ ሒሳብ 46‚100 ብር በማውጣት አየር ጤና በሚገኘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በመሄድ የልጅቷ ሒሳብ ውስጥ ማስገባቱንና በድምሩ 54,980 ብር እንዳለ መጥቀሱን ተመለከተ፡፡ ፖሊስ ከደብዳቤው ላይ ያገኘውን ጠቋሚ መረጃ በመያዝ ወደ ፍርድ ቤት ሄዶ የባንኮች ሒሳብ መዝገብ ለማየት የሚያስችለውን ፈቃድ ከፍርድ ቤት በማውጣት፣ ወደ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (አየር ጤና ቅርንጫፍ) ሄዶ ሲያረጋግጥ፣ ወጣቱ ባለበት ቀን ሒሳብ ማስገባቱንና የጠቀሰውም የገንዘብ መጠን ትክክል መሆኑን ቢያረጋግጥም፣ ወጣቱ ሒሳብ ሲያስገባ የእሷን ስም፣ መለያ ቁጥርና የእሱን ፊርማ ከማስፈር ውጭ ምንም ማስረጃ እንዳልጻፈ ተረዳ፡፡

ፖሊስ ከባንኩ ያገኘውን የሕይወት ሽፈራውን አድራሻ ይዞ በባንክ ሒሳብ መዝገብ ላይ ያስመዘገባቸውን ቀበሌና የቤት ቁጥር ፍለጋ ሲሄድ ልጅቷ በተባለው ቤት ውስጥ ነዋሪ ሳትሆን፣ ወደ ውጭ (ዓረብ አገር) ስትሄድ የባንክ ሒሳብ ለመክፈት መታወቂያ ስለሚያስፈልጋት፣ በዚያ ቤት ቁጥር ማውጣቷንና በወቅቱ እንደሌለች ከቤቱ ባለቤቶች ተረዳ፡፡ ወንድወሰን ስለሚባል ልጅ የሚያውቁት ወይም የሰሙት ነገር እንዳለ ሲጠይቅ እንደሚያውቁትና ጓደኛዋ (እጮኛዋ) እንደሆነ አስረድተው ቤቱን እንዳሳዩት አስረድቷል፡፡
Guest1 wrote:yichi nat chewata 8)
Guest1 wrote:yichi nat chewata 8)
Guest1 wrote:yichi nat chewata 8)
:cry: I know, woyane/TPLF is fantastic script writer for everything and they have been living the last two decades just like this. soon they will change it to movie with director of Serawt Fiqre and rest big stomachs.

ፖሊስ ከረጅም ልፋት በኋላ የወጣቱን ቤት ሲያገኘው ሟች ከሦስት ወንድሞቹና አንድ እህቱ ጋር እንደሚኖር እናቱም በሕይወት እንዳሉ ካረጋገጠ በኋላ፣ የያዘውን ፎቶግራፍ ሲያሳያቸው ወንድማቸው መሆኑን ያረጋግጡለታል፡፡ የት እንዳለ ሲጠይቃቸው፣ ከአንድ ቀን በፊት እንደወጣና እንዳልተመለሰ ይገልጹለታል፡፡ ለግል ጉዳይ እንደሚፈለግ በመንገር ቤተሰቡን አረጋግቶ ነገር ግን ለጐረቤት በአደጋ ምክንያት ሕይወቱ ማለፉን በማስረዳት እንዲያረዷቸው አድርጐ መመለሱን ዲቪዚዮኑ አብራርቷል፡፡

የወጣቱ ቤተሰቦች አስከሬኑን ከዳግማዊ ምኒልክ ሆስፒታል በማውጣት የቀብር ሥርዓቱን ከፈጸሙ በኋላ፣ የሟች ወንድም ወደ ፖሊስ ጣቢያ መጥቶ እንደነበር የገለጸው ፖሊስ፣ ወጣቱ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ፍፁም የሆነ ፍቅር እንደነበረው፣ የመኝታ ቤቱ ሙሉ ግድግዳ በእሳቸው ፎቶግራፍ የተሸፈነ መሆኑን፣ ከፎቅ ራሱን ወርውሮ ሞተ በተባለበት ዕለት ጠዋት ከደብተር ላይ ወረቀት ገንጥሎ ሲጽፍ እንደነበር የገነጠለበትን ደብተር ይዞ በመምጣት ማረጋገጡን ፖሊስ ገልጿል፡፡

የወጣቱ ሕይወት ማለፍ ለምን እስከዛሬ እንደተደበቀ ፖሊስን ተጠይቆ የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ድንገተኛ ሕልፈት ብዙዎችን ለመሪር ሐዘን የዳረገበት ወቅት እንደነበርና በዚህ ወቅት (ነሐሴ 24 ቀን 2004 ዓ.ም.) እንደዚህ ያለ ክስተት ይፋ ማድረግ ምናልባትም ሌሎችን ወደማይሆን መንገድ ሊመራ ይችላል በሚል ዝምታ መምረጡን አስረድቷል፡፡

http://www.ethiopianreporter.com/news/2 ... --10-.html



Re: በመለስ ዜናዊ ሞት መሪር ሀዘን የተሰማው ወጣት ከ10ኛ ፎቅ ተወርውሮ ሞተ

Postby tassew » 25 Sep 2012, 07:04


If Meles was indeed a job creator, how come this paranoid's fiancee and tens of thousands of Ethiopian women go to Arab countries and face all the hardship?
I'm sorry for you brother. You bent over your adult life to weyane's propaganda which is, I have to admit is more effective than Goebbels. Someone in your family needed to take you to Kiadanemihret tsebel. Nefs yimar.



Re: በመለስ ዜናዊ ሞት መሪር ሀዘን የተሰማው ወጣት ከ10ኛ ፎቅ ተወርውሮ ሞተ

Postby kmf » 25 Sep 2012, 08:54


no evidence showing the man through himself form the building. Tplf can do such kinds of crazy propaganda. was there anyone who saw the man throughing himself from the building? why others people didn't see the man? why and how the police could manage to see the man? if others saw the dead man, why it was not reported earlier? So, it is TPLF propaganda.

Next Page


Return to News & Opinion

Who is online

Registered users: Bing [Bot], CYP450, Google [Bot], Google Adsense [Bot], Google Feedfetcher, Halyeyga, Hayet, Macaanto, MSN [Bot], TurnitinBot [Bot], whereisthefrog, Yahoo [Bot], Zack