5 opposition officials and activists defected to EPPF

Five officials and activists of Ethiopian opposition parties that operate inside the country have joined the armed resistance against the Woyanne genocidal regime, according to the Press Office of Ethiopian People’s Patriotic Front (EPPF).

One of them is Seid Ali Tegegn, an Ethiopian Democratic Party (EDP or Edepa, as commonly known) candidate in the town of Bahr Dar. Seid, who competed for the regional council, told the EPPF press office that Woyanne thugs had tried to convince him to support the ruling party during the May 23, 2010, elections. When that failed they attempted to kill him by throwing a hand grenade on his house.

Abera Kasse Zewdie is another member of EDP who has recently joined EPPF. Abera was assigned to observe the May 23 election in the town of Bahr Dar’s Kebele 17. Abera said people in his Kebele are convinced that the only alternative left for them is to wage armed struggle against the ruling Woyanne junta.

The following three opposition officials have also joined EPPF in the past few days:

* Demilew Yigzaw Fente, a representative of All Ethiopian Unity Party (AEUP), in Gonder, Dabat Woreda

* Tekle Takele Gezahegn, Chairman of AEUP’s Youth Association in Dabat Woreda of Gonder

* Dereje Woreta Kebede, Medrek representative in Metemha

All three have similar stories regarding the brutal repression in Ethiopia during last month’s elections.

Ato Tekle Takele further explained that many among the peasant population in rural areas of the country are joining EPPF.

More details in Amharic below.

For the latest information about EPPF visit ArbegnochGinbor.com or contact Demis Belete, Head of the EPPF Press Office, Email: [email protected]

የተቃዋሚ ፓርቲዎች እጩዎችና ተወካዮች የአርበኞች ግንባርን ተቀላቀሉ

በባህር ዳር ከተማ በ121 የምርጫ ጣቢያዎች ኢዴፓን ወክሎ ባለፈው ግንቦር ወር በተደረገው ምርጫ ላይ የተወዳደረው ስዒድ አሊ ተገኝ ሰሞኑን የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባርን (ኢህአግ) ተቀላቅለ።

የምርጫው ሂደት ሙሉ በሙሉ የታፈነ ነበር፣ ህዝቡም የፈለገውን መምረጥ በማይችልበት ደረጃ ላይ በተለያዩ ምክንያቶች አስፈራርቶ ይዞታል የሚለው አቶ ስዒድ አሊ የምርጫውን ሂደት ሲያስረዳ፣ ቅስቀሳ በምናደርግበት ወቅት ፖስተር ስንለጥፍ ወዲያውኑ የወያኔ ተላላኪዎች ይቀዱታል ወይም የራሳቸውን ፖስተር በእኛ ላይ ይለጥፉበታል። ይህን አይነት ድርጊት በሚፈፅሙበት ጊዜ የእኛ አባሎች ለመከላከል ሲሞክሩ አርፈህ ተቀመጥ የሚል ማስፈራሪያ ይሰጣል። ከዚያ ባለፈም እቤትህ ድረስ መጥተው አፍነው የፈለጉትን ያደርጉሃል ብሏል።

ሌላው የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባርን የተቀላቀለው በባህር ዳር ከተማ በቀበሌ 17 የኢዴፓ ታዛቢ የነበረው አቶ አበራ ካሴ ዘውዴ ሲሆን፣ ወያኔ ምርጫ አካሂጃለሁ ከሚል ግልፅ አፈና አካሂጃለሁ ቢል ይሻለዋል ሲል ገልፆታል። አቶ አበራ ካሴ በምርጫው ወቅት የነበረውን ሁኔታ ሲገልፅ እኔ በነበርኩበት የምርጫ ጣቢያ አብዛኛው ማለት ይቻላል ድምፅ ሊሰጡ የመጡት ፖሊሶች ሲሆኑ እግረ መንገዳቸውንም ከፍተኛ ማስፈራራትና ወከባ ሲፈጥሩ ነበር ሲል ገልጿል።

መምህር ደምለው ይግዛው ፈንቴ የሰሜን ጎንደር ዳባት ወረዳ የመኢአድ ተዘዋዋሪ ወኪል ሲሆን፣ ያለፈውን የምርጫ ሂደት ሲገልፅ፣ እኛ ምንም አይነት ቅስቀሳ ወደ ሕዝብ ገብተን ማድረግ አንችልም። ፖስተሮች ይገነጠላሉ፣ የእኛን መለያ ይዘው የተገኙ ሰዎች እንግልትና ወከባ ይደርስባቸዋል።

እኛ እንኳን ሕዝባችንን ሰብስበን ልንቀሳቀስ ይቅርና አባሎቻችንን በፅ/ቤት ተሰብስበን ስንበተን መንገድ ላይ በመጠበቅ ከፍተኛ እንግልት ነው ሲፈጥሩብን የነበረው የሚለው መምህር ደምለው ይግዛው አያልነህ ጌታነህ የተባለ አባላችንን ዳባት ወረዳ ቀበሌ 01 ቆልቶ በላ የተባለ ቦታ ላይ አፍነው አይኑን አስረው ከአሰቃዩት በኋላ በማግስቱ ለቀውታል ይልና፣ የዳባት ወረዳ ምርጫ ፅ/ቤት ሃላፊ ተስፋ ሹምባሽ የተባለው እኔን አስጠርቶ ነገሮችን በዝምታ ለማሳለፍ በመሞከርህ ህይውትህን አትርፈሃል ብሎኛል ሲል በአካባቢያቸው የምርጫው ሂደት ለማስመሰል ያህል እንኳ የተሰራበት እንዳልነበር በምሬት ገልፆ፤ ይህ ዘረኛና ፀረ-ህዝብ ቡድን በመሳሪያ ሃይል ካልሆነ ከህዝባችን ጫንቃ ላይ አይወርድም በመሆኑም የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ጎን ለመሰለፍ ወስነናል ብሏል።

የመኢአድ አባልና በሰሜን ጎንደር የዳባት ወረዳ መኢአድ ወጣቶች ሊቀመንበር የሆነው አቶ ተክሌ ታከለ ገዛኽኝ ሲሆን፣ ምርጫውን ወያኔ ብቻውን ሮጦ ብቻውን ያሸነፈበት ነው ይልና፤ በዳባት ወረዳ አጀሬ ፣ ደንከር ፣ ኮንፍየ ፣ ደቋ ፣ጭና፣ አረቡር የምርጫውን ሂደት እንዲታዘቡ የተላኩ የመኢአድ ታዛቢዎች እየተደበደቡ ከአካባቢው እንዲለቁ እንደተደረጉ ገልጿል። አያይዞም አርሶ አደሩን ሕዝብ ማንን እንደመረጣችሁ አሻራችሁ በኮምፒዩተር ስለሚታወቅ በስህተት ተቃዋሚዎችን እንዳትመርጡ፣ እነሱን መርጦ የተገኘ ሰው መሬቱንም ጭምር ሊቀማ እንደሚችል ማስፈራሪያ እንደደረሳቸው አስታውቋል።

በዚህና መሰል የወያኔ ግፈኛ አገዛዝ የተማረረው ሕዝብ አንገቱን የደፋ ቢመስልም ልቡ ግን እንደተነሳሳ ገልፆ አብዛኛው የአካባቢው አርሶ አደር በበረሃ ከኢህአግ ሠራዊት ጋር እየተቀላቀለ መሆኑን አቶ ተክሌ ገልጿል።

ሌላው ደረጀ ወረታ ከበደ የተባለው በመተማ የመድረክ አባልና አደራጅ የነበረ ሲሆን፣ በመተማ ሽኽዲ አካባቢ ያደርገው በነበረው እንቅስቃሴ የመተማ የማስታወቂያ ቢሮ ሃላፊ የሆነው ገዛኽኝ ሞገስ የተባለ ወያኔ ለመቶ አለቃ ሞገስ የተባለ ፖሊስ ትዕዛዝ ሰጥቶ ምርጫው እስኪጠናቀቅ የቁም እስረኛ እንደነበረ ገልጿል።

በመተማ አካባቢ ወያኔን በሚቃወሙ ሰዎች ላይ ከፍተኛ እንግልት እየተፈፀመ ሲሆን፣ ሙሉ ጌታ አበጀ የተባለ የሽኽዲ ነዋሪ አፍነው ወስደውት የት እንዳደረሱት አይታወቅም፣ አንድ መላኩ የተባለ የ10ኛ ክፍል ተማሪም እነሱን ስላልደገፈ ብቻ ፈተና ላይ እንዳይቀመጥ በመከልከልና ከፍተኛ ስቃይ ስላደረሱበት አዕምሮውን ስቶ የት እንደገባ አይታወቅም የሚለው አቶ ደረጀ ወረታ ወያኔን ሁላችንም በአንድነት ስለአንድነት ልንፋለመው ይገባል ብሏል።