Boycott Al Amoudi’s festival in Washington DC

Boycott Al Amoudi

የአላሙዲ አሽከሮች በዋሽንግተን ዲሲ ባዘጋጁት የወያኔ ፌስቲቫል ላይ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን እንዳይሳተፉ የቀረበ ጥሪ

[PDF]

የኢትዮጵያ ስፖርት ፌዴሬሽን ዓመታዊ ዝግጅት በዳላስ ቴክሳስ ከጁላይ 1 – 7፥ እንዲሁም የኢትዮጵያ ሄሪቴጅ በዋሽንግተን ዲሲ ከጁላይ 27 – 29 ይካሄዳሉ። እነዚህን የኢትዮጵያውያን ዝግጅቶች ለማፍረስ ወያኔያዊ ተልዕኮ ያላቸውና በገንዘብ የተገዙ ግለሰቦች ያደረጉት ሙከራ ይታወሳል። ይሁን እንጂ ተልእኮአቸው ከሽፎ በሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያ ስፖርት ፌዴሬሽን (ESFNA) የበለጠ ተጠናክሮ፥ ራሱን ከወያኔ ካድሬዎችና ከአላሙዲ አሽከሮች አጽድቶ እየወጣ ይገኛል።

ሆኖም የአላሙዲ አሽከሮች ዛሬም ቢሆን እርኩስ ተልእኮዋቸውን ለመወጣት ከመሞከር አልታቀቡም። በአንጋፋዉ ESFNA ስም ላይ (ONE) በመቀጠል ድርጅቱን ለመከፋፈልና ህብረተሰባችን ውስጥ ውዥንብር ለመፍጠር የሞከሩት እኩይ ተግባር ፍርድቤት ቀርበው እንዲታቀቡ ተደርጓል።

በዚህም ሳያበቃ፣ ሆዳደሮቹ የሁሉም ኢትዮጵያዊያን የስፖርት ማሕበር አንድ (AESAONE) በሚል ስያሜ በዋሽንግተን ዲሲ ከጁላይ 1 እስከ ጁላይ 7 ድረስ የስፖርት ፌስቲቫል አዘጋጃለሁ ብለው ተነስተዋል። ይህ ዝግጅት በዳላስ ከሚካሄደዉ የESFNA ታላቅ የስፖርትና የባሕል ፌስቲቫል ዝግጅት ቀናት ጋር ተመሳሳይ እንዲሆን በማድረግ ያሰራጩት የእነሱን መሰሪ ተልእኮ በግልጽ የሚያስረዳ ነው።

ይህ የእነዚህ ጥቂት ሆድ አደሮች ጥርቅም ከአላሙዲ በሚቸራቸዉ ገንዘብ ከርሳቸውን ከመሙላት ባሻገር፤ ከነርሱና ከአላሙዲ ጀርባ የወያኔ አገዛዝ እንዳለበትና ዓላማውም ኢትዮጵያውያንን የመከፋፈል አጀንዳ ቅጥያ መሆኑን ማስገንዘብ እንፈልጋለን።

ውድ ወገኖች!

በመስጠም ላይ ያለ ሰው፣ አድኖ ላያድነዉ አረፋም ቢሆን ይጨብጣል እንዲሉ፣ አንዴ በአባይ ስም፣ አሁን ደግሞ በስፖርት ሽፋን የተገመደው ተንኮል ለወያኔ የእግር እሳት የሆነበትን ዳያስፖራ ለማወናበድ የታለመ ነው። ታዲያ ይህን እየተካሄደ ያለውን ሴራ እንደወትሮው ሁሉ ዛሬም ለማክሸፍ ሃገርወዳድ ኢትዮጵያውያን ሁሉ በጋራ እንሰለፍ።

በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ተቋማት የተመሰረተዉ Boycott TPLF ግብረሃይል ይህን በስፖርት ሽፋን ኢትዮጵያውያንን ለማወናበድና ለመከፋፈል የተዶለተውን ሴራ በጋራ እንድናከሽፍ ጥሪውን ያቀርባል።

በዋሽንግተን ዲሲ የወያኔ መልእክተኞች ትላንት ተቋቋምን ብለው ዛሬ በሚሊዮን የሚቆጠር ዶላር አውጥተው አዘጋጀን የሚሉትን ፌስቲቫል ሀገርወዳድ ኢትዮጵያውያን ሁሉ እንዳትተባበሩ ጥሪ እናደርጋለን። በሚሊዮን ዶላር የተከራዩት ስታዲዮም የሰዓት እላፊ የታወጀበት መንደር ሆኖ ጭር እንዲል እንድናደርገው እንጠይቃለን።

በአንጻሩ ወደ ዳላስ ቴክሳስ በማምራት ከጁላይ 1 እስከ ጁላይ 7 ቀን 2012 ድረስ በሚካሄደው የሁላችንም መገናኛ፣ መዝናኛና የኢትዮጵያዊነት መግለጫ በሆነው 29ኛው በESFNA ፌስቲቫል ላይ በመሳተፍ በዓሉን የደመቀ እንድናደርገው እናሳስባለን።

የወያኔ ሴራ በየፈርጁ ይከሽፋል!
Boycott TPLF ግብረሃይል

Email: [email protected]
Tel: 703 828 4821