Ethiopian News & Opinion Journal
  • HOME
  • Contact
  • Advertise
  • Subscribe
  • Ge'ez Fonts
  • FORUM
  • ALBUM
  • ARCHIVE
  • CLASSIFIEDS
  • Login

Wolqait-Tegede Ethiopians in Ohio resolution – Amharic

August 20th, 2007 |

The following is a resolution passed on Aug 18, 2007, by Ethiopians of the Wolqait-Tegede region currently residing in Ohio. 

የወልቃይት-ጠገዴ ተወላጅ ኢትዮጵያውያን ተቃውሞና የአቋም መግለጫ

በ 8/18/2007 በትግራይ ሕዝብ ነፃ አውጭ ግንባር ተውካዮች (ትውልዳቸው ወልቃይት የሆኑ) የትግራይ ክልል የፀጥታ/ደህንነት ሃላፊ አቶ ፀጋይ አስማማውና የወልቃይት ጠገዴ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ፈረደ የሺወንድም “ልማት ለወልቃይት” በሚል ስም በተጠራው ስብሰባ ላይ በርካታ የወልቃይት ጠገዴ ተወላጆች ተገኝተዋል።

የስብሰባው ተሳታፊ በወቅቱ የቀረበለትን ተአማኒነት የሌለው የወያኔ የፕሮፕጋንዳ ሪፖርት ካዳመጠ በኋላ እጅጉን ከሃቅ የራቀ ሆኖ በማግኘቱ በተጠቅሱት አክባቢዎች ያለው ተጨባጭ ችግሮች ፊት ለፊት አጋልጧል። በማስከተልም የሚከተሉትን የውሳኔ ሀሳቦችን አስተላልፏል።

1. የትግራይ ነፃ አውጭ ግንባር (ሕወሓት) ያለወልቃይት ጠገዴና ሁመራ ተወላጆች ፍላጎት መሬቱ ወደ ትግራይ ክልል ማስገባቱ አጥብቆ በመቃወምና ይህ ቋንቋን ብቻ መሰረት ያደረገው የማካለል ስርዓት ለኢትዮጵያችን ጎጂ መሆኑን በማስገንዘብ የጎንደር ታሪካው መሬቶች (ወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ሁመራና ጠለምት) ወደ ቀድሞው አስተዳደራቸው እንዲመለሱ በአፅንዖት ጠይቋል፤

2. ሕወሓት በወልቃይት ጠገዴ ተወላጅ ኢትዮጵያውያን ላይ ከሃያ አመታት በላይ ለፈፀመችውና በመፈፀም ላይ ያለችውን አሰቃቂ ግዲያዎችና እስራት በመቃውም ባልበቃቃ ምክንያት የታሰሩትን ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን በአስቸኳይ እንዲፈቱ አሳስቧል፤

3. ኢትዮጵያውያን የወልቃይት ጠገዴ ተወላጆች ሆን ብሎ ከለም መሬታቸው በማስለቀቅ በምትኩ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ የትግራይ ተወላጆች ብቻ አምጥቶ መሬቱን እንዲይዙ ማድረግ ከቅንነት የመነጨ ስላልሆነ ድርጊቱን በፅኑ አውግዟል፤

4. በሰበብ አስባቡ ያለ አግባብ ከአቅሙ በላይ ቅጣትና ግብር በነዚሁ ተወላጅ ኢትዮጵያውያን ላይ መጫኑና ከባድ የኢኮኖሚ ትፅዕኖ እንዲደርስበት መደረጉን በመቃወም ይህ አስከፊ ተግባር እንዲቆም ጠይቋል።

5. በነዚህ አካባቢዎች ተውላጅ ኢትዮጵያዊያን ላይ ከረጅም አመታት በፊት ጀምሮ በተለያዩ ኢ-ሰብዓዊ መንገዶች እየተደረገ ያለውን የስነ ልቦና ሰለባ በአስችኳይ እንዲቆም አሳስቧል፤

6. በሃገረ ሱዳን የሚኖሩትን ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን ባለፈው (ጁላይ) ወር በእጅ አዙር በሱዳን መንግሥት እንዲታሰሩ መደረጉን አጋልጦ፤ ሕወሓት በስደት በሚገኙት ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን ላይ የምታደርገውን ጣልቃ ገብነት እንድታቆም ጠይቋል፤

7. በጎንደርና በትግራይ ሕዝብ መካከል የነበረውን የረጅም ዘመናት ትስስር ወያኔ ስልጣን ከያዘችበት ጊዜ ጀምሮ የወልቃይት ጠገዴ እንዲሁም የጠለምት መሬቶችን በመውሰድና በወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ላይ ከፍተኛ በደል በመፈፀም በሁለቱ ህዝብ መካከል ስር የሰደደ ጥላቻ እንዲፈጠር መደረጉ እንዳሳስበው ገልጿል፤

8. በመጨረሻም በአያትና በቅድመ-አያቶች አጥንትና ደም ተከብሮ የኖረውን የኢትዮጵያ ዳር ድንበር እንዲከበርና ተቆርሶ ለሱዳን የተሰጡት መሬቶች እንዲመለሱ ለወደፊቱም እዲህ አይነቱ ተንኳሻና የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት የሚስደፍሩ ተግባራት እንዳይሞከሩ አጥብቆ በማሳሰብ ስብሰባው ተገባዷል።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!
በኮለምበስ ኦሃዮ የወልቃይት ጠገዴ ተወላጅ ኢትዮጵያውያን
ኦገስት 18፣ 2007





Related Posts

  1. Ethiopians in Dallas pass resolution in remembrance of May 15
  2. Ethiopians in Ohio give Woyanne delegates the boot
  3. Ethiopians for Obama volunteering in Ohio
  4. Ethiopians in Ohio to confront Meles Zenawi in Pittsburgh
  5. Is Siye a changed person? (Amharic)




Email This Post Email This Post | Add a comment Write a Comment

Leave a Comment

To write your comment in Amharic or download Amharic fonts click here. አስተያየትዎን በአማርኛ ለመጻፍ እዚህ ይጫኑ:: ጽፈው ከጨረሱ በኋላ የጻፉትን ኮፒ አድርገው ወደዚህ ተመልሰው አስተያየት መስጫ ቦክስ ውስጥ ፔስት ያድርጉ:: ወይም ከዚህ በታች ያለውን በመጫን መልእክትዎትን በድምጽ መቅዳት ይችላሉ::



Archive




Ethiopian News & Opinion Journal







Recent Posts
  • The missing 8.6 million Ethiopians, where art thou?
  • U.S. official gives lips service on repression in Ethiopia
  • Ethiopian ‘virgin land’ for sale
  • What do you expect from the coming elections in Ethiopia?
  • ONLF killed 985 Woyannes, burned 6 vehicles
  • Woyanne kangaroo court convicts alleged coup plotters
  • Yemen police detain 191 refugees from Ethiopia
  • Ethiopia is sliding deeper into authoritarian controls
  • Ethiopia’s regime tries to cover up a new famine
  • Memher Zebene, Ethiopia’s Jimmy Swaggart?
  • Hailu Shawel dines with Woyannes after surrender
  • EPPF strives to fill the leadership gap
  • Interview with EPPF Fighter (Part II)
  • Witness for the Future
  • ONLF killed 626 Woyanne troops in lastest fighting
  • Detainees accused of plotting coup brutally tortured by police
  • The U.S. and China in Africa: To compete or cooperate?
  • Be aware of Facebook risks
  • 5 soldiers defect complaining corruption
  • Why Hailu Shawel chose a shameful defeat


©2009 Ethiopian Review
Publisher & Editor-in-Chief: Elias Kifle
Powered by WordPress