Ethiopian News and Opinion Journal


  • HOME
  • SUBSCRIBE
  • CONTACT
  • FORUM
  • VIDEO
  • DIRECTORY
  • ADVERTISE
  • ALBUM
  • DICTIONARY
  • CLASSIFIEDS
  • EXERCISE
  • Login

ይፋ የሆነው የወያኔ እጩዎች ዝርዝር ውዝግብ አስነሳ

February 29th, 2008 |

በቀጣዩ ሚያዝያ ለአከባቢና ማሟያ ምርጫ በወያኔ ካድሬዎች በሚመለመሉበት ወቅት ፈቃደኛ ያለመሆናቸውን ገልጸው የነበሩ አንዳንድ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ይፋ በተደረገው የእጩዎች ዝርዝር ውስጥ ስማቸው በመገኘቱ በምርጫ ጣቢያዎች ውዝግብ በመነሳት ላይ ነው፡፡

ለቀጣዩ ምርጫ አራት ሚሊዮን እጩዎችን ያቀረበው ወያኔ ባልታሰበ መንገድ የተቀሰቀሰውን የቅሬታ ውዝግብ ለማብረድ በምርጫ አስፈጻሚዎች አማካይነት የማረጋጋት ስራ እየሰራ ይገኛል፡፡ እጩዎች በሚመለመሉበት ወቅት ምንም አይነት የፖለቲካ ተሳትፎ የሌላቸውን ግለሰቦች ሳይቀር በወያኔ እጩነት ለማጋበስ አሳፋሪ እንቅስቃሴ ሲካሄድ የነበረ ሲሆን በወቅቱ ‹‹ተቃዋሚዎች አይደለንም፤ ሆኖም በፖለቲካዊ ጉዳዮች በተለይም ፓርቲ ወክሎ እጩ ሆኖ ለመቅረብ ልምዱም ዝግጅቱም የለንም፡፡›› ያሉ ግለሰቦችን በዝምታ ካለፉ በኋላ የትም አይደርሱም በሚል እሳቤ ዝርዝራቸው ይፋ በመደረጉ ከምርጫ ጣቢያዎቹ ማስታወቂያ ሰሌዳዎች ላይ በአስቸኳይ ስማቸው እንዲሰረዝ ሲሟገቱ የተመለከቱት ዘጋቢዎቻችን ሪፖርት ያመለክታል፡፡

የምርጫ ጣቢያ ሃላፊዎቹ ውዝግቡ እንዳይባባስ በሚል የተፈጠረ ችግር ካለ በአስቸኳይ ይስተካከላል ከማለት አልፈው ስማችን ያላግባብ ይፋ ሆኗል የሚሉትን ቅሬታ አቅራቢዎች ስም ከሰሌዳው ላይ የመሰረዝ አስገራሚ ድራማ ሲሰሩ ተስተውሏል፡፡ ተመሳሳይ በደል የደረሰባቸው አንድ በጡረታ ላይ የሚገኙ ግለሰብ እንደገለጹልን በግድ እጩ የተደረጉት ሁሉ ይውጡ ቢባል ጉዱ ይታይ ነበር፤ ይሁንና በካድሬዎች ማስፈራርያ እየተሰጣቸው በዝምታ ሁኔታውን እየተከታተሉ ነው በማለት የሁኔታውን አስከፊነት አስቀምጠውታል፡፡

Email This Post | Add a comment FORUM



Related Posts

  1. የአዲስ አበባ እጩዎች ዝርዝር ይፋ ሆነ
  2. የወያኔ እጩዎች ህገ-መንግስታዊ መብታችን ተጥሷል እያሉ ነው
  3. የተቃዋሚ ፓርቲ እጩዎች ራሳቸውን እያገለሉ ነው
  4. የወያኔ ካድሬዎች የቤት ለቤት ቅስቀሳ ጀመሩ
  5. የሚያዝያው ምርጫ መመዝገቢያ ወቅት ለአንድ ወር ተራዘመ

Leave a Comment

To write your comment in Amharic click here. አስተያየትዎን በአማርኛ ለመጻፍ እዚህ ይጫኑ:: ጽፈው ከጨረሱ በኋላ የጻፉትን ኮፒ አድርገው ወደዚህ ተመልሰው አስተያየት መስጫ ቦክስ ውስጥ ፔስት ያድርጉ::



Click to cancel reply








Recent Posts
  • Ethiopian Youth Public Meeting in Dallas – Saturday, Feb. 11
  • DC area Ethiopian churches under attack
  • Saudi pressured to release detained Ethiopians
  • International Ethiopian Women Conference March 9-11
  • ALEJE and OLF Public Meeting in Washington DC – Feb. 19
  • Where the truth lies in Ethiopia
  • Transformative Reconciliation for Unity in a Nutshell
  • When we were the peacemakers
  • Cooperative Behavior for Transformatve Reconciliation & Unity
  • A resurgent Ethiopian opposition in a new form
  • African Beggars Union Hall?
  • Kilil system is an instrument of Ethiopian disenfrachisement – Part 4
  • Several Meles Zenawi bodyguards arrested
  • UN experts dismayed by growing repression in Ethiopia
  • Swedish journalists appeal to Ethiopia’s dictator
  • Another sign of worsening repression in Ethiopia – IFEX
  • Using Anti-Terror Laws to Terrorize Dissent
  • We’ve met the enemy and he is us
  • Essentials to Resolve Differences for Reconciliation
  • Ethiopian delegation delivers letter to Saudi Arabia embassy in DC


©2012 Ethiopian Review
Publisher & Editor-in-Chief: Elias Kifle
Powered by WordPress