Ethiopian News and Opinion Journal


  • HOME
  • SUBSCRIBE
  • CONTACT
  • FORUM
  • VIDEO
  • DIRECTORY
  • ADVERTISE
  • ALBUM
  • DICTIONARY
  • CLASSIFIEDS
  • EXERCISE
  • Login

Journalists reporting Teddy Afro’s trial in Ethiopia arrested

October 24th, 2008 |  |  2 Comments

ADDIS ABABA, ETHIOPIA – The publisher of Inbilta weekly newspaper in Addis Ababa, Wzt. Tsion Girma, and two journalists, Ato Habte Derese and Ato Atnafu Alemayehu, have been arrested yesterday for misidentifying the last name of the judge who is hearing Teddy Afro’s sham trial.

Inbilta newspaper wrote down the judge’s name as Mohammed Umer. His correct name is Mohammed Amin Sani.

The dumb judge took that as an insult and ordered the publisher and her two journalists to be arrested immediately.

More by ethiopiazare.com in Amharic:

(ኀሙስ ጥቅምት 13 ቀን 2001 ዓ.ም. October 23, 2008)፦ የቴዲ አፍሮን ክስ የሚያስችሉትን ዳኛ የአባት ሥም በስህተት ያተመው የእንቢልታ ጋዜጣ ሦስት አዘጋጆች በዛሬው ዕለት ችሎት ቀርበው አሣታሚና ዋና አዘጋጅዋ ጽዮን ግርማ እስከ ሦስት ዓመት ሊያስቀጣ በሚችል ክስ ተመስርቶባት በዋስ ስትለቀቅ፤ የሁለቱን አዘጋጆች ጉዳይ ዓቃቤ ሕግ ክሴን አላጠናቀቅሁም በማለቱ ታስረው እንዲያድሩ ተደረገ።

“የቴዲ አፍሮን ጉዳይ የሚያስችሉት ዳኛ ከችሎት ተነሱ” በሚል ርዕስ በመስከረም 23 ዕትሙ አዲስ የተተኩት ዳኛ መሐመድ ዑመር ቢሆኑም ጋዜጣው ዳኛ መሐመድ አሚን ሳኒ ናቸው በሚል የዳኛውን የአባት ስም በስህተት በመዘገቡ ሦስት የጋዜጣው አዘጋጆች ከረቡዕ ጀምሮ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን መዘገባችን አይዘነጋም።

በዛሬው ዕለት የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 14ኛ ወንጀል ችሎት ሦስቱም አዘጋጆች ቀርበው የነበረ ሲሆን፣ ዓቃቤ ሕግ በዋና አዘጋጅዋ ጽዮን ግርማ ላይ ብቻ “የወንጀለኛ ሕግ ቁጥር 431ሀ እና 486ለ”ን በመጥቀስ ክሱን መስርቶባታል። ፍርድ ቤቱ ለጊዜው በሁለት ሺህ ብር ዋስ እንድትፈታና የፊታችን ሰኞ ጥቅምት 18 ቀን 2001 ዓ.ም. እንድትቀርብ አዟል። ጋዜጠኛው ዋስትናዋን አሟልታ ዛሬ ማምሻውን ከእስር መለቀቋን ከአዲስ አበባ የደረሰን መረጃ ይጠቁማል።

በጋዜጣው ምክትል አዘጋጅ ሀብቴ ታደሰ እና በአዘጋጁ አጥናፉ አለማየሁ ላይ ግን ክሴን አለጠናቀቅሁም በማለቱ ሁለቱ ጋዜጠኞች በፖሊስ ታጅበውና በካቴና ታስረው በድጋሚ ወደ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ታስረው እንዲያድሩ ተደርጓል።

ጋዜጠኞች ሲከሰሱ ጉዳያቸው የሚታየው በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 10ኛ ወንጀል ችሎት የነበረ ቢሆንም፣ ዛሬ የጋዜጠኞቹን ጉዳይ ያየው 14ኛ ወንጀል ችሎት ነው። ይህ ችሎት “ፈጣን ችሎት በመባል የሚጠራ እንደሆነና እጅ ከፍንጅ የተያዙ የስርቆት ወንጀሎች እንደሚታዩበት በትናንትናው ዕለት መዘገባችን አይዘነጋም።

በዚህ ችሎት የሚቀርቡ ጉዳዮች ውሳኔ የሚጥባቸው የዕለቱ ዕለት ወይንም ከበዛ በአንድ ሣምንት ጊዜ ውስጥ ነው። ይህንን የጋዜጠኞቹን ክስ በዚህ ችሎት ለምን እንዲታይ ማድረግ እንዳስፈለገ በግልጽ የታወቀ ነገር ባይኖርም፤ ጉዳዩን እየተከታተሉ ባሉ ወገኖች ዘንድ ግን ጥርጣሬን እንዳሳደረ ለመረዳት ችለናል።

በዋና አዘጋጅዋ ክስ ላይ በተጠቀሰው አንቀጽ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የወንጀለኛ ሕግ ቁጥር 431ሀ እና 486ለ፤ “በማናቸውም አይነት ማሳጣት ወይም ሌላ ዘዴ ጥርጣሬን ያስፋፋ፣ ጥላቻን ያነሳሳ ወይም የኃይል ድርጊት ወይም የፖለቲካ የዘር ወይም የኃይማኖት ኹከት የቀሰቀሰ እንደሆነ፤ በቀላል እስራት ወይም በመቀጮ ወይም ወንጀሉ ከባድ በሆነ ጊዜ ከሦስት ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እስራት ይቀጣል” እንደሆነ ለማረጋገጥ ችለናል።

በዚህም መሠረት ፍርድ ቤቱ አዘጋጅዋን የፊታችን ሰኞ ጥፋተኛ ብሎ ከወሰነባት እስከ ሦስት ዓመት የእስራት ቅጣት ሊቀጣት እንደሚችል ታውቋል።

ጉዳዩን እየተከታተሉ ያሉ የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች በእስር እንዲያድሩ የተደረጉት ጋዜጠኛ ሀብቴ ታደሰ እና ጋዜጠኛ አጥናፉ አለማየሁ በነገው ዕለት ሊፈቱ እንደሚችሉ ያላቸውን ግምት ገልጸዋል።

ጋዜጠኛ አጥናፉ አለማየሁ በጦማር እና በጦቢያ ጋዜጦች ላይ በምክትል አዘጋጅነትና በዋና አዘጋጅነት ሠርቷል።

ምክትል አዘጋጁ ጋዜጠኛ ሀብቴ ታደሰ ደግሞ በሀገር ውስጥ በሚታተሙ ከስድስት በላይ ጋዜጦች ላይ እስከ አዘጋጅነት ሠርቷል። እንዲሁም “ኔቸር” የተሰኘ በኢንቫይሮመንት ላይ የሚያተኩር የራሱን ጋዜጣ ያሣትም ነበር።

Email This Post | Add a comment FORUM  |  2 Comments



Related Posts

  1. There Is No Justice In Ethiopia – The Teddy Afro show trial
  2. Woyanne revives 2005 treason trial against journalists
  3. Newspaper editor, unable to post bail, sent to prison
  4. Teddy Afro’s lawyer arrested
  5. Teddy Afro's lawyer arrested

2 Comments to “Journalists reporting Teddy Afro’s trial in Ethiopia arrested”

  1. Gabra says:

    Now this is very sad to see in this day and age a judge ordering the arrest of journalists for making an honest mistake of misidentifying him. Can you imagine what will happen to someone over there if she/he says: “Meles Negussie is palling around with a terrorist”? Notice there are two areas of ‘mistake’ here. His last name is ‘wrong’ and ‘palling around with a ‘terrorist’ is declared defamation. The verdict: Face an execution squad. Am I wrong? If I am wrong, please someone correct me with prevailing facts. It is a shame, totally, utterly and downright shame to see such regimes are still allowed to rule. These journalists should be allowed to write any thing they find factual without worrying about being persecuted. I hope an pray that soon and very, very soon all the ‘major players’ on both sides, more on the ruling side, will come to their senses and do away with such despotism. It can be done. Just look what happened in Chile in the late 90′s and now. Then Argentina, Brazil and Uruguay. This judge may have never thought in the past that one day he will be a judge. Now he got the job somehow and wants to assert himself a new sherrif in town by giving such unconscionable orders. It is wrongfully in a way: “it is my turn now”.

    [Reply]

    October 24th, 2008 at 12:34 PM

  2. Keros says:

    if you are Woyanne you can arrest any one any time that’s how it is in Ethiopia

    GOD Mercy /

    [Reply]

    October 25th, 2008 at 9:43 AM

Leave a Comment

To write your comment in Amharic click here. አስተያየትዎን በአማርኛ ለመጻፍ እዚህ ይጫኑ:: ጽፈው ከጨረሱ በኋላ የጻፉትን ኮፒ አድርገው ወደዚህ ተመልሰው አስተያየት መስጫ ቦክስ ውስጥ ፔስት ያድርጉ::



Click to cancel reply








Recent Posts
  • Ethiopian Youth Public Meeting in Dallas – Saturday, Feb. 11
  • DC area Ethiopian churches under attack
  • Saudi pressured to release detained Ethiopians
  • International Ethiopian Women Conference March 9-11
  • ALEJE and OLF Public Meeting in Washington DC – Feb. 19
  • Where the truth lies in Ethiopia
  • Transformative Reconciliation for Unity in a Nutshell
  • When we were the peacemakers
  • Cooperative Behavior for Transformatve Reconciliation & Unity
  • A resurgent Ethiopian opposition in a new form
  • African Beggars Union Hall?
  • Kilil system is an instrument of Ethiopian disenfrachisement – Part 4
  • Several Meles Zenawi bodyguards arrested
  • UN experts dismayed by growing repression in Ethiopia
  • Swedish journalists appeal to Ethiopia’s dictator
  • Another sign of worsening repression in Ethiopia – IFEX
  • Using Anti-Terror Laws to Terrorize Dissent
  • We’ve met the enemy and he is us
  • Essentials to Resolve Differences for Reconciliation
  • Ethiopian delegation delivers letter to Saudi Arabia embassy in DC


©2012 Ethiopian Review
Publisher & Editor-in-Chief: Elias Kifle
Powered by WordPress