የቅንጅት የላእላይ ም/ቤት በቀጣዩ ሳምንት ወሳኝ ስብሰባ ያደርጋል

እስካሁን በነበረውና ወደፊት ሊከናወኑ በሚገባቸው ወሳኝ የትግል እንቅስቃሴዎች ላይ አሳሪ ውሳኔዎችን ለማሳለፍ የቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ፓርቲ የላእላይ ም/ቤት በቀጣዩ ሳምንት ስብሰባ ያደርጋል፡፡

ምርጫ 97ትን ተከትሎ በተፈጠረው ቀውስ የታሰሩ የፓርቲው አባላትን በማስፈታት፤ አደጋ ላይ ወድቆ የነበረውንና በራሱ ሊቀመንበር የማፍረስ ሙከራ የተደረገበትን ህዝባዊ ፓርቲ በማዳን፤ በክልሎች ያሉ አባላትን በማነጋገር፤ በማደራጀትና በመሳሰሉት ግዜ የማይሰጡ ተግባራት ተጠምዶ የነበረው የአመራር አካል በቀጣዩ ሳምንት በሚያደርገው ስብሰባ ለህዝቡ በቀጣዩ ሂደት ላይ የሚያደርጋቸውን እንቅስቃሴዎችና የአካሄድ ስልቱ ምን ሊሆን እንደሚችል ይጠቁማል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

የስራ አስፈጻሚ አካሉ ለቀጣዩ ሳምንት ወሳኝ ስብሰባ ዝግጅት በማድረግ ላይ ሲሆን ስብሰባው በህዝቡ አእምሮ ለሚመላለሱት በርካታ ጥያቄዎች አጥጋቢ ምላሽ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል