አገር አቀፍ የጫት ሲምፖዚየም ሊካሄድ ነው

አገሪቱ አምና ከጫት ኤክስፖርት ከ5 ቢ. ብር በላይ አግኝታለች

By Metasebia Kasaye | addisadmassnews.com

December 29, 2014

 

A qat addict in Yemen

A qat addict in Yemen

ጫት በዜጐች ላይ እያስከተለ ያለውን የጤና ችግር ለመቅረፍ የሚያስችል የፖሊሲ አቅጣጫ ለመንደፍ ያለመ አገር አቀፍ የጫት ሲምፖዚየም በቅርቡ የሚካሄድ ሲሆን፣ የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝን ጨምሮ ታላላቅ የአገሪቱ ባለስልጣናት በሲምፖዚየሙ እንደሚሳተፉ ይጠበቃል፡፡
በአገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎችና በትምህርት ቤቶች አካባቢ የጫት መሸጫና ማስቃሚያ ቤቶች በመበራከታቸው ምክንያት የመማር ማስተማሩን ሂደት በአግባቡ ለማከናወን አለመቻሉን የገለፁት የኢትዮጵ የምግብ የመድኀኒትና የጤና ክብካቤ አስተዳደር ቁጥጥር ባለስልጣን አማካሪው አቶ መንግስተአብ ወልደአረጋይ፤ ሲምፖዚየሙ ጫት በዜጐች ላይ የሚያደርሰውን ጉዳት የሚያመላክቱ ጥናታዊ ጽሑፎች እንደሚቀርቡበትና ውይይት ተካሂዶ የፖሊሲ አቅጣጫ የሚነደፍበት ትልቅ ጉባዔ እንደሚሆን አመልክተዋል፡፡

ቀደም ሲል በህዝብ ተወካዮች አፈጉባዔ የሚመራና የክልል አፈጉባዔዎች የተሳተፉበት በአደገኛ መድሃኒቶችና ዕፆች ላይ ያተኮረ ሲምፖዚየም መካሄዱን ያስታወሱት አቶ መንግስተአብ፤ ጉባዔው በጫት ሳቢያ የሚደርሰውን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና የጤና ችግሮች ለመቅረፍና ዜጐችን ለመታደግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት ያደረገ እንደነበር ተናግረዋል፡፡

ጫት ወደ ውጪ አገር ተልከው የውጭ ምንዛሬ ከሚያስገኙ የአገሪቱ ምርቶች ተጠቃሽ መሆኑ አይካድም ያሉት አማካሪው፤ አገሪቱ ከዘርፉ የምታገኘውን ጥቅም በማሰብ ዜጐች ለከፋ ችግርና አደጋ ሲጋለጡ ዝም ብሎ ማየቱ ተገቢ ባለመሆኑ ሲሞፖዚየሙን ለማካሄድ እንደታቀደ ጨምረው ገልፀዋል፡፡
ኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአውሮፓና አሜሪካ ያላት የጫት ሽያጭ በእጅጉ በመቀዛቀዙ ምርቶቿን በአብዛኛው የምትልከው ለየመን፣ ሶማሊያና አረብ አገራት ሲሆን ባለፈው ዓመት ጫት ከአገሪቱ የኤክስፖርት ምርቶች በአራተኛነት ደረጃ ላይ ሆኖ 270 ሚሊዮን ዶላር ገቢ አስገኝቷል፡፡

 

ጫት በዜጐች ላይ እያስከተለ ያለውን የጤና ችግር ለመቅረፍ የሚያስችል የፖሊሲ አቅጣጫ ለመንደፍ ያለመ አገር አቀፍ የጫት ሲምፖዚየም በቅርቡ የሚካሄድ ሲሆን፣ የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝን ጨምሮ ታላላቅ የአገሪቱ ባለስልጣናት በሲምፖዚየሙ እንደሚሳተፉ ይጠበቃል፡፡
በአገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎችና በትምህርት ቤቶች አካባቢ የጫት መሸጫና ማስቃሚያ ቤቶች በመበራከታቸው ምክንያት የመማር ማስተማሩን ሂደት በአግባቡ ለማከናወን አለመቻሉን የገለፁት የኢትዮጵ የምግብ የመድኀኒትና የጤና ክብካቤ አስተዳደር ቁጥጥር ባለስልጣን አማካሪው አቶ መንግስተአብ ወልደአረጋይ፤ ሲምፖዚየሙ ጫት በዜጐች ላይ የሚያደርሰውን ጉዳት የሚያመላክቱ ጥናታዊ ጽሑፎች እንደሚቀርቡበትና ውይይት ተካሂዶ የፖሊሲ አቅጣጫ የሚነደፍበት ትልቅ ጉባዔ እንደሚሆን አመልክተዋል፡፡
ቀደም ሲል በህዝብ ተወካዮች አፈጉባዔ የሚመራና የክልል አፈጉባዔዎች የተሳተፉበት በአደገኛ መድሃኒቶችና ዕፆች ላይ ያተኮረ ሲምፖዚየም መካሄዱን ያስታወሱት አቶ መንግስተአብ፤ ጉባዔው በጫት ሳቢያ የሚደርሰውን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና የጤና ችግሮች ለመቅረፍና ዜጐችን ለመታደግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት ያደረገ እንደነበር ተናግረዋል፡፡

ጫት ወደ ውጪ አገር ተልከው የውጭ ምንዛሬ ከሚያስገኙ የአገሪቱ ምርቶች ተጠቃሽ መሆኑ አይካድም ያሉት አማካሪው፤ አገሪቱ ከዘርፉ የምታገኘውን ጥቅም በማሰብ ዜጐች ለከፋ ችግርና አደጋ ሲጋለጡ ዝም ብሎ ማየቱ ተገቢ ባለመሆኑ ሲሞፖዚየሙን ለማካሄድ እንደታቀደ ጨምረው ገልፀዋል፡፡
ኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአውሮፓና አሜሪካ ያላት የጫት ሽያጭ በእጅጉ በመቀዛቀዙ ምርቶቿን በአብዛኛው የምትልከው ለየመን፣ ሶማሊያና አረብ አገራት ሲሆን ባለፈው ዓመት ጫት ከአገሪቱ የኤክስፖርት ምርቶች በአራተኛነት ደረጃ ላይ ሆኖ 270 ሚሊዮን ዶላር ገቢ አስገኝቷል፡፡